• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኢትዮጵያ ችግር የዕርዳታ ስንዴ ነው”

October 15, 2021 05:04 pm by Editor 1 Comment

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 18, 2021 01:38 pm at 1:38 pm

    የቢቢሲ ኦንላይነ ዜና የቀኑን የፈጠራ ዜናውን ሲያናፍስ የኢትዮጵያው መሪ የእርዳታ እህልን እንደ ጦር ሊጠቀምበት ነው ይላል። ጠ/ሚሩ ራሳችን ስለመቻል ነበር የተናገሩት። ሌሎች ደግሞ እንዴት ሃገሪቱ ጦርነት ላይ እያለች ማሳ ጉብኝት ይሄዳል በማለት ይወርፋሉ። እንዝፈን ሲሉ የሚያለቅ፤ እናልቅስ ሲሉት የሚዘፍን የደነዘዘ ትውልድ የኢትዮጵያ ችግር የእርዳታ ምግብ መሆኑን መረዳት ይከብደው ይሆናል። የጠ/ሚሩ አባባል ግን ሃቅ ነው። የስንት ሃገሮች ሃገር በቀል የእህል ዝሪያ በመጤው ተውጦ ቀርቷል። ስንቶች ናቸው ይህን ካልታዘዛችሁ እህል አንሰጥም የተባሉት? ሁቱና ቱትሲ በሩዋንዳ ሲተላለቁ ምንም አያገባንም በማለት ቆመው የተመለከቱት የነጭ ወታደሮች አፋቸውን ሞልተው ጥቁር በጥቁር ላይ ስላለው ጭካኔ ያወራሉ። ግን እንዲህ ያለ ከሰው ባህሪ ውጭ የሆነ ጭካኔን እንዲያረጉ መንገድ የከፈተላቸው ራሱ ነጩ ህዝብ ነው። ከአውራ ጣት አመልካች ጣት ትበልጣለች እያሉ አንድ ከሌላው ጋር እንዲላተም በማድረግ። ነገሩ ሲከፋ ደግሞ የዜና አውታሮችን በማምጣት የአለም ህዝብ የእኛን ገመና እያየ ከንፈሩን እንዲመጥና ብሎም የእርዳታው ስንዴ ሲሰፈርለት ሃገራቸው የእርዳታ እጇን መዘርጋቷን ሲመለከቱ የፓለቲካ አሻሮአቸውን ቅመው እርፍ ይላሉ። ውስጠ ሚስጢሩን ግን የሚረዳ የለም። ለዚያ ነው እኛም እነርሱ በያዙልኝ ጅራፍ እየተነዳን ሃገር የምናፈርሰው፤ የምንገዳደለው አልፎ ተርፎም በዘርና በቋንቋ ተጠልለን ሰላቢዎችን የሆነው። የነቃ የበቃ አርቆ የሚያስብ ጭንቅላት ያለው ማንም ቢሆን የዘር ፓለቲካ የቆሻሻ ክምር መሆኑ ሊገባው ይገባል። ግን የውስልትናው ፓለቲካ የነጻነት ጮራ አስመስሎ ጽልመት ሲያለብሰው ሰው የክልል ባንዲራ ይዞ በጅምላ አስተሳሰብ አብሮ ይነጉዳል።
    አሁን እንሆ ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር መባሉ ምን ያህል ወያኔ እየገፋ እንደመጣ ያመላክታል። አዲስ አበባ ላይ ተቀምጦ ዲስኩር መደስኮርና መለኮታዊ ሃይልን መማጸን ቅድመ አያቶቻችን በጣሊያ የጋዝ ጭስ ከመታፈን አላዳናቸውም። መቀሌ ላይ ቁጭ ብለው እየመከሩና እየዘከሩ ጦርነቱን አፋር ምድር አድርሰውት ዝም ብሎ መመልከት መደንዘዝ ነው። የሚፎክሩት መሪዎቻቸው የት ናቸው? እነርሱ ታድነው እንዲገደሉ ወይም እንዲያዙ የሚከለክለው ህግ የቱ ነው? ይመስለኛል ሰራዊቱ እዚህም እዚያም የያዛቸውን ስፍራዎች እየለቀቀ አንዴ የፓለቲካ ውሳኔ ነው ስንባል፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ታክቲካዊ ማፈግፈግ ነው ሲሉን አዲስ አበባ ሲደርሱ ምን ሊሉን ፈልገው ይሆን? ግራ የሚያጋባ ነገር ነው እየሆነ ያለው። ይህ ጦርነት በረዘመ ቁጥር ህዝባችን አሁን ካለው በባሰ ሁኔታ ይራባል፤ ይፈናቀላል፤ ይሰደዳል፤ ይሞታል። አሁንም በቋፍ ላይ ያለ ህዝብ ነው። ኑሮ ጣራ ላይ ደርሷል። በጦርነቱ ቦታዎች ሰው የሚበላው የለም። ይህ መንግስ ነኝ ለሚለው የውድቀት ዋዜማ ይመስላል። የስንዴ ማሳው ማለፊያ ነው። ግን የኦሮሞ ጽንፈኞች እንደ ሽዋው የጤፍ ክምር እሳት እንዳሰድበት ጥንቃቄ ይደረግ። ጠ/ሚሩም ለምን የማሳ ጉብኝት አረጉ ብሎ የሚያጉረመርም ያው እሳቸውንም እንደ ስብሃት ነጋ እስረኛ ለማድረግ የፈለጉ ብቻ ናቸው። እየተዋጉም/እያዋጉም/እያቀድም/የተጀመሩ ፕሮጄክቶችንና የሰብል ማሳዎችን መጎብኘት ይቻላል። ችግሩ እሱ አይደለም። ችግሩ መቼ ነው የሰሜኑ ጦርነት የሚያከትመው ነው። በጻድቃንና በጌታቸው ረዳ ስሌት በሳምንታት ውስጥ ነው። ጠብቀን እናያለን። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule