• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሰሜን ኮሪያ የደናግላት ቁጥር መመናመን ፕሬዚዳንቱን አሳስቧል!

August 20, 2013 12:56 am by Editor 2 Comments

ወጣቱ የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ እን ለሚያካሂዱት የዳንስ ስኳድ በቂ ደናግልት ለማግኘት መቸገራቸውን የደቡብ ኮሪያ ዜና ቾሱን ኢልቦ ገለጸ፡፡

ሰሜን ኮሪያ ለፕሬዚዳንቷ ክብር የምትጠቀምባቸው ዳንሰኞች የሚውጣጡት ከደናግልት ሴቶች ነው፡፡ ለዚህ ፕሬዚዳንቱን ለማዝናናት የሚደረገው የዳንስና ሙዚቃ ሙያ አባል ለመሆን የሚችሉ ድንግል ሴቶች በአብዛኛው ወጣቶችና የኮሌጅ ተማሪዎች እንደሆኑ ተዘግቧል፡፡ ክብረንጽህናን መጠበቅም ዋንኛው ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡

ሆኖም ሰሜን ኮሪያ ካለባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር ባሻገር አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባውያን በጣሉባት የኢኮኖሚ ማዕቀብ የአገሪቱን ኢኮኖሚ አሽመድምዶታል፡፡ በመሆኑም ሴቶች የትምህርት ወጪያቸውን ለመደጎም እንዲሁም የኑሮውን ውድነት ለመቋቋም በሴተኛ አዳሪነት በመሰማራታቸው የደናግልቱ ቁጥር ባልተጠበቀ ሁኔታ ለማሽቆልቆሉ እንደ ምክንያት ተጠቅሷል፡፡

ሴቶቹን የመረመሩት ወታደራዊ ሃኪሞች እንደገለጹት ከተመረመሩት የ16 ዓመት ሴቶች መካከል 60በመቶው በወሲብ ግንኙነት ድንግልናቸውን ያጡ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ሁኔታው ለፕሬዚዳንቱ የዳንስና ሙዚቃ ቡድን አባልነት የሚመዘገቡት “ብቃት” ያላቸው ዳንሰኞች ቁጥር ችግር ላይ ጥሎታል፡፡

ለሴተኛ አዳሪነት ያጋለጣቸው የኑሮው ሁኔታ እንደሆነ ቢገለጽም አብዛኛዎቹ ደምበኞቻቸው ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሲሆኑ ሴቶቹ በሚያገኙትም ገንዘብ ለኑሮ ከሚያስፈልጋቸው ሌላ ለጌጣጌጥ፣ ለሞባይል ስልክ፣ የጋብቻ ወጪያቸውን ለመሸፈን፣ ወዘተ እንደሚጠቀሙበት ዜናው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡

በአገራችን እየተከሰተ ያለው ከህጻናት ጀምሮ እስከ አዋቂ አልፎተርፎ ደግሞ አሁን በተመሳሳይ ጾታ መካከል በሚደረግ ሰዶማዊነትና የዚህ ሰለባ የሆኑት ደግሞ ህጻናት ወንዶች ልጆች መሆናቸው፤ ከሰሜን ኮሪያው ሁኔታ ጋር ሲስተያይ በሰሜን ኮሪያ 40በመቶ ደናግልት መገኘታቸው “የጻድቃን አገር” ሊያስብላት የሚችል ነው፡፡

በፈረቃ የሚተኙ ልጆች ባሉበትና እናት ልጇን ለወሲብ ገፍታ የምትልክበት ሁኔታ ባለባት ኢትዮጵያ፤ ባለሥልጣናት “በዝግ ቤቶች” ወሲብ በሚታሙበት፤ የሴቶች አከፋፋይና መልማዮች ኢትዮጵያ ውስጥ ታላቅ ክብር እንደሚሰጣቸው በሚሰማበት፤ ዘመንና ጊዜ ገንዘብ ያርከፈከፈላቸው ማታ ለይምሰል በቤታቸው፣ ቀን ላይ ዱባይ ሄደው ወሲብ ፈጽመው ለመመለሳቸው መረጃዎች በሚወጡበት ባሁኑ ወቅት፤ በኢትዮጵያ የሰሜን ኮሪያ ዓይነት ተመሳሳይ ችግር አይኖርም ብሎ ማሰብ በሰማነው ዜና ለመቀለድ የሚያስችለን አይሆንም፤ ዜናውንም የመዝናኛ ዜና አያደርገውም፡፡

በሚያብረቀርቅ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠው ህጻናትን እንደ ዶሮ በሽሮ እያስፈተጉ ሲፈልጉ ለወሲብ ሲያሻቸው ደግሞ ለሽያጭ የሚያቀርቡ “የልማት አልኝታዎች” መኖራቸውን በምንሰማበት ባሁኑ ወቅት፣ ሴቶች ልጆቻችን ብቻ ሳይሆኑ የአስርና የ15ዓመት ህጻናት ወንዶች የዚሁ ልቅና መረን ያጣ የወሲብ ሰለባ መሆናቸው የመሪያችንና “የዕድገታችን ብቃት” ማሳያ ብለን እንውሰደው ይሆን?

ይህንን “ዓይነቱን ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እንዲሁም ህዳሴ” ለማንም አሳልፈው እንዳይሰጡ “በመስጋት ለትውልድ አውርሰው (“ሌጋሲ” ትተው)” ለሞት የበቁትን የኢትዮጵያ ሃፍረትና ውርደት የጡት አባት አቶ መለስ ዜናዊ አንደኛ ዓመት በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እየዘከረች መሆኗ “ምን እያደረግን ነው?” የሚያስብል ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አባተ says

    August 22, 2013 03:25 am at 3:25 am

    ጎልጉል፣ በጣም ጥሩ ማሳሰቢያ ያለበት ጽሑፍ ነው። በርቱ።

    Reply
  2. Aster says

    August 22, 2013 03:57 am at 3:57 am

    ይህን ጽሑፍ በመለጠፋችሁ ደስ ብሎኛል። ብዙ ወገኖቻችን ይህን እያዩና እየሰሙ ችላ ብለዋል። ያሳዝናል። በዚህ ከቀጠለ አገራችን ምን ላይ ልትወድ ነው? መንግሥት እንደ ሆነ ግድ የለውም። የናንተን አንብቤ ሳበቃ ከታች ባለው ድረገጽ ላይ ይህን አንብቤ ምናልባት በናንተው ላይ ተጨምሮ ሰውን ያነቃ እንደ ሆን ብዬ ላክሁላችሁ። አስቴር ነኝ ከዳላስ
    http://www.ethiopianchurch.org/editorial2/174-%E1%89%A3%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8C%88%E1%89%A3-%E1%8B%90%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%8B%88%E1%8C%A3.html

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule