• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሰሜን ኮሪያ የደናግላት ቁጥር መመናመን ፕሬዚዳንቱን አሳስቧል!

August 20, 2013 12:56 am by Editor 2 Comments

ወጣቱ የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ እን ለሚያካሂዱት የዳንስ ስኳድ በቂ ደናግልት ለማግኘት መቸገራቸውን የደቡብ ኮሪያ ዜና ቾሱን ኢልቦ ገለጸ፡፡

ሰሜን ኮሪያ ለፕሬዚዳንቷ ክብር የምትጠቀምባቸው ዳንሰኞች የሚውጣጡት ከደናግልት ሴቶች ነው፡፡ ለዚህ ፕሬዚዳንቱን ለማዝናናት የሚደረገው የዳንስና ሙዚቃ ሙያ አባል ለመሆን የሚችሉ ድንግል ሴቶች በአብዛኛው ወጣቶችና የኮሌጅ ተማሪዎች እንደሆኑ ተዘግቧል፡፡ ክብረንጽህናን መጠበቅም ዋንኛው ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡

ሆኖም ሰሜን ኮሪያ ካለባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር ባሻገር አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባውያን በጣሉባት የኢኮኖሚ ማዕቀብ የአገሪቱን ኢኮኖሚ አሽመድምዶታል፡፡ በመሆኑም ሴቶች የትምህርት ወጪያቸውን ለመደጎም እንዲሁም የኑሮውን ውድነት ለመቋቋም በሴተኛ አዳሪነት በመሰማራታቸው የደናግልቱ ቁጥር ባልተጠበቀ ሁኔታ ለማሽቆልቆሉ እንደ ምክንያት ተጠቅሷል፡፡

ሴቶቹን የመረመሩት ወታደራዊ ሃኪሞች እንደገለጹት ከተመረመሩት የ16 ዓመት ሴቶች መካከል 60በመቶው በወሲብ ግንኙነት ድንግልናቸውን ያጡ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ሁኔታው ለፕሬዚዳንቱ የዳንስና ሙዚቃ ቡድን አባልነት የሚመዘገቡት “ብቃት” ያላቸው ዳንሰኞች ቁጥር ችግር ላይ ጥሎታል፡፡

ለሴተኛ አዳሪነት ያጋለጣቸው የኑሮው ሁኔታ እንደሆነ ቢገለጽም አብዛኛዎቹ ደምበኞቻቸው ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሲሆኑ ሴቶቹ በሚያገኙትም ገንዘብ ለኑሮ ከሚያስፈልጋቸው ሌላ ለጌጣጌጥ፣ ለሞባይል ስልክ፣ የጋብቻ ወጪያቸውን ለመሸፈን፣ ወዘተ እንደሚጠቀሙበት ዜናው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡

በአገራችን እየተከሰተ ያለው ከህጻናት ጀምሮ እስከ አዋቂ አልፎተርፎ ደግሞ አሁን በተመሳሳይ ጾታ መካከል በሚደረግ ሰዶማዊነትና የዚህ ሰለባ የሆኑት ደግሞ ህጻናት ወንዶች ልጆች መሆናቸው፤ ከሰሜን ኮሪያው ሁኔታ ጋር ሲስተያይ በሰሜን ኮሪያ 40በመቶ ደናግልት መገኘታቸው “የጻድቃን አገር” ሊያስብላት የሚችል ነው፡፡

በፈረቃ የሚተኙ ልጆች ባሉበትና እናት ልጇን ለወሲብ ገፍታ የምትልክበት ሁኔታ ባለባት ኢትዮጵያ፤ ባለሥልጣናት “በዝግ ቤቶች” ወሲብ በሚታሙበት፤ የሴቶች አከፋፋይና መልማዮች ኢትዮጵያ ውስጥ ታላቅ ክብር እንደሚሰጣቸው በሚሰማበት፤ ዘመንና ጊዜ ገንዘብ ያርከፈከፈላቸው ማታ ለይምሰል በቤታቸው፣ ቀን ላይ ዱባይ ሄደው ወሲብ ፈጽመው ለመመለሳቸው መረጃዎች በሚወጡበት ባሁኑ ወቅት፤ በኢትዮጵያ የሰሜን ኮሪያ ዓይነት ተመሳሳይ ችግር አይኖርም ብሎ ማሰብ በሰማነው ዜና ለመቀለድ የሚያስችለን አይሆንም፤ ዜናውንም የመዝናኛ ዜና አያደርገውም፡፡

በሚያብረቀርቅ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠው ህጻናትን እንደ ዶሮ በሽሮ እያስፈተጉ ሲፈልጉ ለወሲብ ሲያሻቸው ደግሞ ለሽያጭ የሚያቀርቡ “የልማት አልኝታዎች” መኖራቸውን በምንሰማበት ባሁኑ ወቅት፣ ሴቶች ልጆቻችን ብቻ ሳይሆኑ የአስርና የ15ዓመት ህጻናት ወንዶች የዚሁ ልቅና መረን ያጣ የወሲብ ሰለባ መሆናቸው የመሪያችንና “የዕድገታችን ብቃት” ማሳያ ብለን እንውሰደው ይሆን?

ይህንን “ዓይነቱን ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እንዲሁም ህዳሴ” ለማንም አሳልፈው እንዳይሰጡ “በመስጋት ለትውልድ አውርሰው (“ሌጋሲ” ትተው)” ለሞት የበቁትን የኢትዮጵያ ሃፍረትና ውርደት የጡት አባት አቶ መለስ ዜናዊ አንደኛ ዓመት በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እየዘከረች መሆኗ “ምን እያደረግን ነው?” የሚያስብል ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አባተ says

    August 22, 2013 03:25 am at 3:25 am

    ጎልጉል፣ በጣም ጥሩ ማሳሰቢያ ያለበት ጽሑፍ ነው። በርቱ።

    Reply
  2. Aster says

    August 22, 2013 03:57 am at 3:57 am

    ይህን ጽሑፍ በመለጠፋችሁ ደስ ብሎኛል። ብዙ ወገኖቻችን ይህን እያዩና እየሰሙ ችላ ብለዋል። ያሳዝናል። በዚህ ከቀጠለ አገራችን ምን ላይ ልትወድ ነው? መንግሥት እንደ ሆነ ግድ የለውም። የናንተን አንብቤ ሳበቃ ከታች ባለው ድረገጽ ላይ ይህን አንብቤ ምናልባት በናንተው ላይ ተጨምሮ ሰውን ያነቃ እንደ ሆን ብዬ ላክሁላችሁ። አስቴር ነኝ ከዳላስ
    http://www.ethiopianchurch.org/editorial2/174-%E1%89%A3%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8C%88%E1%89%A3-%E1%8B%90%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%8B%88%E1%8C%A3.html

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule