• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ

January 26, 2021 10:32 am by Editor Leave a Comment

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰሞኑን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን ያላግባብ ተጠ ቅመው አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን በተመለከተ  ሃሰተኛ  መረጃዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው  በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለማደናገር ሲሞክሩ የነበሩ አንዳንድ የማህበራዊ ሚድያ አንቂዎች ከህገወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ ተቋሙ  አሳስቧል፡፡

ከዚህ በኋላ የሀሰት መረጃዎችንና አሉባልታዎችን  በማህበራዊ ትስስር ገጾች በማሰራጨት  የሀገርን ብሄራዊ ጥቅምና ህልውና ለመጉዳት እንዲሁም የህዝብን ሰላምና  ደህንነት ስጋት  ላይ ለመጣል  የሚንቀሳቀሱ  አካላት ላይ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ማስረጃዎችን በማጠናቀር በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እንደሚያደርግ ከወዲሁ ያሳውቃል። 

ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት  በሀገር ላይ የሚቃጡ  የፀጥታና የደህንነት  ስጋቶችን በማስቀረት  ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን  ከማንኛውም ጊዜ በላይ ከሁሉም  የጸጥታና የደህንነት  ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ እንደሚገኝ መግለጫው  አመልክቷል።

በተያያዘ  ዜና የብሔራዊ መረጃ  ዩኒቨርስቲ ኮሌጅን  በኢንተለጀንስና በደህንነት መስኮች የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የለውጥ ትግበራ ተጠናክሮ  እንደሚቀጥል  የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ። 

አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን በተመለከተ  ሃሰተኛ  መረጃዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው  በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለማደናገር ሲሞክሩ የነበሩ አንዳንድ የማህበራዊ ሚድያ አንቂዎች ከህገወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ ተቋሙ አሳስቧል፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች በአገልገሎት መሥሪያ ቤቱ ሥር  የሚገኘውን የብሄራዊ መረጃ ዩኒቨርሲቲ  ኮሌጅ የሥራ እንቅስቃሴን  በዛሬው  ዕለት ጎብኝተዋል።     

አገልገሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ የብሔራዊ  መረጃና ደህንነት አገልግሎት  ዳይሬክተር  ጀነራል  አቶ  ተመሰገን ጥሩነህ  በጉብኝታቸው ወቅት በሥልጠና ማዕከል ደረጃ የነበረው  ተቋም  ወደ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ደረጃ ማደጉ አስደሳች መሆኑን ገልፀው  ዩኒቨርስቲ  ኮሌጁ  ከዚህ በላይ  የመሥራት  እምቅ አቅም  እንዳለው ተናግረዋል።

ዩኒቨርስቲ ኮሌጁን በአፍሪካ በኢንተለጀንስና በደህንነት መስኮች የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የለውጥ ትግበራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የተቋሙ አመራሮች ድጋፍ እንደማይለየውም አመልክተዋል፡፡

አዲስ  አበባ  የአፍሪካና የዓለም አቀፍ ተቋማት የዲፕሎማሲ  መቀመጫ መሆኗን የጠቆሙት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ የብሔራዊ መረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሎጁ በዘርፉ የማሰልጠን አቅሙን ከፍ ወዳለ ደረጃ ካደረሰ አፍሪካውያንን  በማስልጠን በአፍሪካ የልህቅት  ማዕከል  መሆን እንደሚችልም  ጠቁመዋል።

የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁን አቅም ይበልጥ ለማሳደግ፣ ለ ማዘመንና በቴክኖሎጂ  ታግዞ  ዓለም አቀፍ ደረጃውን  ጠብቆ  ተልዕኮውን  እንዲወጣ  ለማስቻል  አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ  አስፈላጊውን  የፋይናንስና የሎጀስቲክስ ድጋፍ እያደረገ  መሆኑንና ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል  አስረድተዋል።

የብሄራዊ መረጃ ዩኒቨርሲቲ  ኮሌጅ  ባለፈው ዓመት ከከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ በደህንነት ፣ በኢንተለጀንስ፣ በስትራቴጂክ ጥናትና በቋንቋ የትምህርት መስኮች በዲግሪና በዲፕሎማ ስልጠና ለመስጠት እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል፡፡ (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: NISS, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule