• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ

January 26, 2021 10:32 am by Editor Leave a Comment

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰሞኑን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን ያላግባብ ተጠ ቅመው አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን በተመለከተ  ሃሰተኛ  መረጃዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው  በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለማደናገር ሲሞክሩ የነበሩ አንዳንድ የማህበራዊ ሚድያ አንቂዎች ከህገወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ ተቋሙ  አሳስቧል፡፡

ከዚህ በኋላ የሀሰት መረጃዎችንና አሉባልታዎችን  በማህበራዊ ትስስር ገጾች በማሰራጨት  የሀገርን ብሄራዊ ጥቅምና ህልውና ለመጉዳት እንዲሁም የህዝብን ሰላምና  ደህንነት ስጋት  ላይ ለመጣል  የሚንቀሳቀሱ  አካላት ላይ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ማስረጃዎችን በማጠናቀር በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እንደሚያደርግ ከወዲሁ ያሳውቃል። 

ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት  በሀገር ላይ የሚቃጡ  የፀጥታና የደህንነት  ስጋቶችን በማስቀረት  ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን  ከማንኛውም ጊዜ በላይ ከሁሉም  የጸጥታና የደህንነት  ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ እንደሚገኝ መግለጫው  አመልክቷል።

በተያያዘ  ዜና የብሔራዊ መረጃ  ዩኒቨርስቲ ኮሌጅን  በኢንተለጀንስና በደህንነት መስኮች የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የለውጥ ትግበራ ተጠናክሮ  እንደሚቀጥል  የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ። 

አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን በተመለከተ  ሃሰተኛ  መረጃዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው  በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለማደናገር ሲሞክሩ የነበሩ አንዳንድ የማህበራዊ ሚድያ አንቂዎች ከህገወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ ተቋሙ አሳስቧል፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች በአገልገሎት መሥሪያ ቤቱ ሥር  የሚገኘውን የብሄራዊ መረጃ ዩኒቨርሲቲ  ኮሌጅ የሥራ እንቅስቃሴን  በዛሬው  ዕለት ጎብኝተዋል።     

አገልገሎት መሥሪያ ቤቱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ የብሔራዊ  መረጃና ደህንነት አገልግሎት  ዳይሬክተር  ጀነራል  አቶ  ተመሰገን ጥሩነህ  በጉብኝታቸው ወቅት በሥልጠና ማዕከል ደረጃ የነበረው  ተቋም  ወደ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ደረጃ ማደጉ አስደሳች መሆኑን ገልፀው  ዩኒቨርስቲ  ኮሌጁ  ከዚህ በላይ  የመሥራት  እምቅ አቅም  እንዳለው ተናግረዋል።

ዩኒቨርስቲ ኮሌጁን በአፍሪካ በኢንተለጀንስና በደህንነት መስኮች የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የለውጥ ትግበራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የተቋሙ አመራሮች ድጋፍ እንደማይለየውም አመልክተዋል፡፡

አዲስ  አበባ  የአፍሪካና የዓለም አቀፍ ተቋማት የዲፕሎማሲ  መቀመጫ መሆኗን የጠቆሙት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ የብሔራዊ መረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሎጁ በዘርፉ የማሰልጠን አቅሙን ከፍ ወዳለ ደረጃ ካደረሰ አፍሪካውያንን  በማስልጠን በአፍሪካ የልህቅት  ማዕከል  መሆን እንደሚችልም  ጠቁመዋል።

የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁን አቅም ይበልጥ ለማሳደግ፣ ለ ማዘመንና በቴክኖሎጂ  ታግዞ  ዓለም አቀፍ ደረጃውን  ጠብቆ  ተልዕኮውን  እንዲወጣ  ለማስቻል  አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ  አስፈላጊውን  የፋይናንስና የሎጀስቲክስ ድጋፍ እያደረገ  መሆኑንና ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል  አስረድተዋል።

የብሄራዊ መረጃ ዩኒቨርሲቲ  ኮሌጅ  ባለፈው ዓመት ከከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ በደህንነት ፣ በኢንተለጀንስ፣ በስትራቴጂክ ጥናትና በቋንቋ የትምህርት መስኮች በዲግሪና በዲፕሎማ ስልጠና ለመስጠት እውቅና ማግኘቱ ይታወሳል፡፡ (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: NISS, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule