• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ “ጽናት” የቀረበ ተጨማሪ መረጃ

September 3, 2015 08:18 am by Editor Leave a Comment

ማሳሰቢያ፡- ከዚህ በፊት ኢንጂነር መሃመድ አባስ በጽናት ዙሪያ ባቀረቡት ዘገባ ከብዙ አንባቢዎቻችን ብዙ ተብለናል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ እንደመሆኑ ሕዝብ መረጃ ከማቅረብ ጀምሮ መጦመርና ዜና መሥራት ይችላል፡፡ በዘመናዊው ጋዜጠኝነት የተለመደ አሠራር ነው፡፡ በመሆኑም ባለፈው ከቀረበው መረጃ አኳያ አሁን ደግሞ ደጋፊ የሚሆን የድምጽ መረጃ ከአጭር መግቢያ ጽሁፍ ጋር ልከውልናል፤ እንዲህ ይነበባል፡-

“እራሱን ጽናት እያለ በሚጠራው ጀሌ ላይ ላቀረብኩት ጽሁፍና ማስተባበያ ለቀረበበት “ዘረፋ” ግልጽ የሆነ ማስረጃ!”

ድምጻችን ይሰማን ለሁለት በመስንጠቅ የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት ለመናድ ሀወሃት/ኢህአዴግ እንቅልፍ አጥቶ ማደር የጀመረው ዛሬ እንዳልሆነ ይታወቃል።

ህወሃት/ኢህአዴግ የሃይማኖት ነጻነት ትግሉ በተጀመረ ማግስት መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ዘብጥያ በማውረድ ለይስሙላ ያፀደቀውን ህገመንግስታዊ መብት በመተላለፍ የህዝቦችን መብት በጠመንጃ አፈሙዝ ጨፍልቆ ለጸሎት አደባባይ የወጣውን አዛውንት፣ ሴት፣ ወጣት ሳይል ያገኘውን ሁሉ በደም በጨቀዩ ልዩ ኮማንዶዎቹ በጥይት ረሽኗል፡፡ ከሞት የተረፈውን በቆመጥ ደብድቦ የተረፈውን በማጋዝ ወዳልታወቀ ስፍራ ወስዶ አስሮ  በማሰቃየት ላይ ይገኛል።

ታዲያ ይህን ሁሉ ግፍና ስቆቃ የተቀበለው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም አንድነቱን ጠብቆ ሰላማዊ ተቃውሞውን የበለጠ በማጠናከር ሳይገድል እየሞተ ለአምባገነኖች የአላማ ጽናቱን በተግባር አሳይቷል፤ በማሳየትም ላይ ይገኛል። ይህ የህዝበ ሙስሊሙ አንድነትና ለሃይማኖቱ ነጻነት ያለው ቁርጠኝነት እንቅልፍ የነሳው ህወሃት፤ የበግ ልምድ ለብሶ ውሎና አዳሩን ህዝበ ሙስሊሙ ጉያ ውስጥ በማድረግ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን ዑለማዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች በኃይል አሊያም በጊዜያዊ ጥቅም በማግባባት ለዚህ እርኩስ ሰይጣናዊ ተግባሩ ማስፈፀሚያ ግበአት እንዲሆኑ ሃገር ውስጥ ያልበጠሰው ቅጠል ያልቧጠጠው ተራራ የለም።

ለአብነት ያህል የፖለቲከኛውን ጃዋር መሃመድ አሳዛኝ ታሪክ ወደ ጎን ትተን በዑስቷዝ ሃስን ታጁ ስም አዲስ አበባ ላይ ቀደም ሲል የተበተነውን ከፋፋይ የሆነ ባለ10 ገጽ ጽሁፍ ማስታወስ ከበቂም በላይ ማስረጃ ነው። በዑስቷዝ ሃስን ታጁ ጽሁፉ ላይ «ሰላማዊ ትግሉን የተቀላቀሉ ወጣቶች አላዋቂ፣ ስሜተኛ፣ ጃሂል አድርጎ ለማቅረብ ከተደረገው ጥረት ባሻገር የተቃውሞ አካሔድ ሌላ መንገድ ቢፈለግለት በሚል አሳፍሪ አቋም በተለይም የጁሙዓ ተቃውሞዎች መቋረጥ እንዳለባቸውና ኮሚቴዎቻችን ይቅርታ ጠይቀው እንዲወጡ» ህወሃት/ኢህአዴግ ህዝበ ሙስሊሙን ተመስሎ በዑለማዎቻችን አንደበት ያሻውን መልዕክት በድፈረት ይስተላለፈበት ያ ፈታኝ የትግል ዘመን የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው።

ዛሬ ከዚህ አፍራሽ ተዕልኮ ባልተለየ የኢህአዴግ ካድሬዎች አይናቸውን በጨው ታጥበው ሳውዲ አረቢያ ጅዳና ሪያድ ከተማ ውስጥ ብዙሃኑ ተመስለው ሊያሰሙን በሞከሩት ጩኸት በአካባቢው ያሉትን ስመጥር የሃይማኖት አባቶችንና ሩቅ ያሉትን የህዝበ ሙስሊሙን ነጻ ሚዲያዎች ቀልብ አሳስተው ለዚህ መስሪ ተግባራቸው ግበአት በማድረግ በህዝበ ሙስሊሙ አንድንት ላይ አደጋ ከመጋረጥ አልፈው በአቋራጭ የግል ኑሮቸውን ለማደርጀት ሲያደርጉ የነበረው ጥረት በሃገር ሽማግሌና በኃይማኖት አባቶች ውሻ በቀደድው ጅብ እንዳይገባ ሲነገራቸው የነበረውን ምከር አሻፈረን ብለው በህዝበ ሙስሊሙ ትግል ሽፋን ንጹሃን  ለማደናገር ሞክረዋል።

እነዚህ ወገኖች ጅዳ መካና መዲና ላይ እውነተኛ በሆኑ የትግሉ ባለቤቶች ሲተፉ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል እንዳለችው እንሰሳ ከፋፋዩን ዶሴያቸውን ሸንክፈው ሪያድ ከተማ ውስጥ በማድባት ጠንካራ ተብሎ በሚነገርለትን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አንድነት ለመፈታተን ያልሸረቡት ሴራ እንደሌለ ሰሞኑን በድምጽ ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

በጣም የሚያሳዝነው ከጥቅማቸው ባሻገር የህዝበ ሙስሊሙ የትግል አንድነት ማየት የተሰናቸው እነዚህ ጀሌዎች ብዙሃኑን ተመስለው የሚያሰሙትን ጩኸት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ በማስተጋባት ከአያሌ እህቶቻችን ቦርሳ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ በትግል ሽፋን ስለሚሰበስቡት በመቶሺ የሚቆጠር ገንዘብ አግባብ አለመሆኑ በነዚህ የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ቢመከሩም አባታዊ ምክርን ሰምቶ ከመቀበል ይልቅ መካሪዎቹን አባቶች ከመኮነን አልፈው ያልሆነ ስም በመስጠት እየፈጸሙ ያለውን ነውረኛ ተግባር በማድበስበስና ለህዝብ የቀረበውን መረጃ ከሃቅ የራቀ አስመስለው በማናፈስ «ውሻ በበላበት አፉ» እንዲሉ የህዝብ ሚዲያዎችን እስከ መዝለፍ ርቀው የሄዱበት ተግባራቸው ሰሞኑን ሪያድ በሚኖሩ የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች እርቃኑን መቅረት መቻሉ የጀሌዎቹን ማንነት ከመቼውም ጊዜ በላይ ግልጽ አድርጎታል። ዛሬ እነዚህ ጀሌዎች በፈጸሙት ነገር ሁሉ ተፀጽተው የበደሉትን ሁሉ በአደባባይ ይቅርታ በመጠየቅ ከጥፋታቸው መመለሳቸውን በደረሰን የድምጽ መረጃ አረጋግጠናል!

የድምጽ መረጃውን ለመስማት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

ኢንጂነር መሃመድ አባስ ከሪያድ ሳውዲ አረቢያ – ፎቶው ቀደም ብሎ ሳውዲ አረቢያ ድምጻችን ይሰማ ካደረገው ስብሰባ የተወሰደ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule