• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱን አቁሙ!” ፕ/ር መረራ ጉዲና

November 20, 2016 12:42 am by Editor Leave a Comment

“በውይይት የማይፈታ ችግር የለም። ስትወያዩ ግን የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱ ላይ አታተኩሩ። ትኩረታችሁን አሁን የተጋፈጥናቸው ችግሮች ላይ አድርጉ።” ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አስታወቁ።

ፕሮፌሰሩ ይህንን የገለጹት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ በኔዘርላንድ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያ ጋር በትላንትናው እለት 20 November 2016 በአምስተርዳም ባደረጉት ውይይት ላይ ነው። በውይይቱ የኦሮሞ አክቲቪስቶችም ተገኝተው ሃሳባቸውን አካፍለዋል።

ስለ ሃገሪቱ ፈታኝ ሁኔታ እና ስለወደፊቱ እጣ ፈንታ በስፋት ያብራሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ መሪ – ፕ/ር መረራ ጉዲና  ከተሰብሳቢው ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።

“አዋጁ እና ኮማንድ ፖስቱ ሕዝባዊ አመጹን ያበርደዋል ወይ?” ተብለው ሲጠየቁ፣ ሃገሪቱ አሁን በመስቀለኛ መንገድ ላይ መሆንዋን ገልጸው አሁን ያለው ሁኔታ ላይ እንዲህ ይሆናል ብሎ መናገር እንደማይቻል ገልጸው፣ነገሮች በሁሉም አቅጣጫ ሊሄዱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ችግሮች እስካልተፈቱና የህዝብ ጥያቄዎች በአግባቡ እስከልተመለሱ ድረስ ሁኔታው ወደ እርስ በርስ እልቂት ሊወስደንም ይችላል። ይላሉ። %e1%88%9d2

በይፋ አልተነገረም እንጂ ኮማንድ ፖስቱ ከአዋጁ በፊትም የነበረ የኢህአዴግ አሰራር እንደሆነ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምእራባውያን ስላላቸው ሚና ተጠይቀው፣ እኛ የቤት ስራችንን ካልሰራን ምእራቡ አለም ምንም ሊረዳን አይችልም። እኛ ካልሰራን እንኳን ምእራቡ አለም እግዚአብሄርም አይረዳንም። ብለዋል።

በዚህ ወቅታዊ የሀገር ጉዳይ ላይ የተዘጋጀ የውይይት ገለጻ ሲሰጡ በዲፕሎማሲው እና በአለም አቀፍ ህብረተሰብ በአንድ በኩል፣ በሃገር ውስጥ የተጀመሩት በርካታ የ”እርቅ” እንቅስቃሴዎችን በስፋት ቃኝተዋል።

በአለም አቀፉ ህብረተሰብ እና በምእራባውያን ሃገሮች በኩል አሁን ለተቃዋሚዎች በር ተከፍቷል ይላሉ ፕ/ር መረራ ጉዲና። በጋራ ሆነን በአንድ ቋንቋ የመናገሩ ህብረታችን ግን አሁንም ፈተና ላይ ነው።

በቅርቡ በአውሮፓ ህብረት ጥሪ ተደርጎላቸው ሃገሪቱ ስላለችበት መስቀለኛ መንገድ በስፋት ተናግረዋል። አሜሪካ በነበሩበት ግዜም ከሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ጋር “አትላንቲክ ካውንስል” ከተባለው የአሜሪካ ቲንክ ታንክ ቡድን ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ውይይት  ሄርማን ኮኽን እና የቀድሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ዴቪድ ሺል የተገኙ ሲሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች በህብረት  ያለመንቀሳቀስ ትኩረት ስቦ እንደነበር ይናገራሉ።

ገዥውን ፓርቲ ከተቃዋሚዎች ጋር ለማግባባት ሰባት የሚያህሉ የእርቅ እና ሰላም ቡድኖች በኢትዮጵያ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል። አብዛኞቹ የ”እርቅ” ቡድኖች ባህላዊውን የ”አንተም ተው ፣ አንተም ተው” ሚና እንኳን የማይጫወቱ አንድን ወገን ብቻ ለመጫን የተቋቋሙ መሆናቸውንም ይተቻሉ።

ስለ ቀድሞው ተማሪያቸው እና ስለ አሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስለ ወርቅነህ ገበየሁ ተጠይቀው፤  በምርጫ ውድድር ይጠቀምበት የነበረው ስም ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ ሲሆን በትምህርት በት ያለው ፋይል ላይ ደግሞ ወርቅነህ ገበየሁ ወልደ ኪዳን እንደሆነ ገልጸዋል። ይህንን ጉዳይ በሁለተኛው መጽሃፋቸውም ላይ መጥቀሳቸውን ተናግረዋል።

በመጨረሻም በሃገር በት በኦሮሞ እና በአማራው ህብረተሰብ እየተፈጠረ ያለው ትብብር እነ ጌታቸው ረዳን ሳይቀር በአደባባይ ወጥተው እንዲናገሩ ያደረገ ትልቅ የታሪክ አሻራ መሆኑን ገልጸው፣ በውጭ ያለውም ወገን የቀድሞ ሂሳብን ማወራረድ አቁሞ፣ በወደፊቱ የሃገሪቱ ሁኔታ ላይ እንዲወያይ ምክር ሰጥተዋል።

በቪዲዮ የተቀረጸው ሙሉ ውይይት እዚህና እዚህ ላይ ይገኛል።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule