• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱን አቁሙ!” ፕ/ር መረራ ጉዲና

November 20, 2016 12:42 am by Editor Leave a Comment

“በውይይት የማይፈታ ችግር የለም። ስትወያዩ ግን የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱ ላይ አታተኩሩ። ትኩረታችሁን አሁን የተጋፈጥናቸው ችግሮች ላይ አድርጉ።” ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አስታወቁ።

ፕሮፌሰሩ ይህንን የገለጹት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ በኔዘርላንድ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያ ጋር በትላንትናው እለት 20 November 2016 በአምስተርዳም ባደረጉት ውይይት ላይ ነው። በውይይቱ የኦሮሞ አክቲቪስቶችም ተገኝተው ሃሳባቸውን አካፍለዋል።

ስለ ሃገሪቱ ፈታኝ ሁኔታ እና ስለወደፊቱ እጣ ፈንታ በስፋት ያብራሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ መሪ – ፕ/ር መረራ ጉዲና  ከተሰብሳቢው ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።

“አዋጁ እና ኮማንድ ፖስቱ ሕዝባዊ አመጹን ያበርደዋል ወይ?” ተብለው ሲጠየቁ፣ ሃገሪቱ አሁን በመስቀለኛ መንገድ ላይ መሆንዋን ገልጸው አሁን ያለው ሁኔታ ላይ እንዲህ ይሆናል ብሎ መናገር እንደማይቻል ገልጸው፣ነገሮች በሁሉም አቅጣጫ ሊሄዱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ችግሮች እስካልተፈቱና የህዝብ ጥያቄዎች በአግባቡ እስከልተመለሱ ድረስ ሁኔታው ወደ እርስ በርስ እልቂት ሊወስደንም ይችላል። ይላሉ። %e1%88%9d2

በይፋ አልተነገረም እንጂ ኮማንድ ፖስቱ ከአዋጁ በፊትም የነበረ የኢህአዴግ አሰራር እንደሆነ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምእራባውያን ስላላቸው ሚና ተጠይቀው፣ እኛ የቤት ስራችንን ካልሰራን ምእራቡ አለም ምንም ሊረዳን አይችልም። እኛ ካልሰራን እንኳን ምእራቡ አለም እግዚአብሄርም አይረዳንም። ብለዋል።

በዚህ ወቅታዊ የሀገር ጉዳይ ላይ የተዘጋጀ የውይይት ገለጻ ሲሰጡ በዲፕሎማሲው እና በአለም አቀፍ ህብረተሰብ በአንድ በኩል፣ በሃገር ውስጥ የተጀመሩት በርካታ የ”እርቅ” እንቅስቃሴዎችን በስፋት ቃኝተዋል።

በአለም አቀፉ ህብረተሰብ እና በምእራባውያን ሃገሮች በኩል አሁን ለተቃዋሚዎች በር ተከፍቷል ይላሉ ፕ/ር መረራ ጉዲና። በጋራ ሆነን በአንድ ቋንቋ የመናገሩ ህብረታችን ግን አሁንም ፈተና ላይ ነው።

በቅርቡ በአውሮፓ ህብረት ጥሪ ተደርጎላቸው ሃገሪቱ ስላለችበት መስቀለኛ መንገድ በስፋት ተናግረዋል። አሜሪካ በነበሩበት ግዜም ከሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ጋር “አትላንቲክ ካውንስል” ከተባለው የአሜሪካ ቲንክ ታንክ ቡድን ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ውይይት  ሄርማን ኮኽን እና የቀድሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ዴቪድ ሺል የተገኙ ሲሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች በህብረት  ያለመንቀሳቀስ ትኩረት ስቦ እንደነበር ይናገራሉ።

ገዥውን ፓርቲ ከተቃዋሚዎች ጋር ለማግባባት ሰባት የሚያህሉ የእርቅ እና ሰላም ቡድኖች በኢትዮጵያ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል። አብዛኞቹ የ”እርቅ” ቡድኖች ባህላዊውን የ”አንተም ተው ፣ አንተም ተው” ሚና እንኳን የማይጫወቱ አንድን ወገን ብቻ ለመጫን የተቋቋሙ መሆናቸውንም ይተቻሉ።

ስለ ቀድሞው ተማሪያቸው እና ስለ አሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስለ ወርቅነህ ገበየሁ ተጠይቀው፤  በምርጫ ውድድር ይጠቀምበት የነበረው ስም ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ ሲሆን በትምህርት በት ያለው ፋይል ላይ ደግሞ ወርቅነህ ገበየሁ ወልደ ኪዳን እንደሆነ ገልጸዋል። ይህንን ጉዳይ በሁለተኛው መጽሃፋቸውም ላይ መጥቀሳቸውን ተናግረዋል።

በመጨረሻም በሃገር በት በኦሮሞ እና በአማራው ህብረተሰብ እየተፈጠረ ያለው ትብብር እነ ጌታቸው ረዳን ሳይቀር በአደባባይ ወጥተው እንዲናገሩ ያደረገ ትልቅ የታሪክ አሻራ መሆኑን ገልጸው፣ በውጭ ያለውም ወገን የቀድሞ ሂሳብን ማወራረድ አቁሞ፣ በወደፊቱ የሃገሪቱ ሁኔታ ላይ እንዲወያይ ምክር ሰጥተዋል።

በቪዲዮ የተቀረጸው ሙሉ ውይይት እዚህና እዚህ ላይ ይገኛል።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule