• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱን አቁሙ!” ፕ/ር መረራ ጉዲና

November 20, 2016 12:42 am by Editor Leave a Comment

“በውይይት የማይፈታ ችግር የለም። ስትወያዩ ግን የታሪክ ሂሳብ ማወራረዱ ላይ አታተኩሩ። ትኩረታችሁን አሁን የተጋፈጥናቸው ችግሮች ላይ አድርጉ።” ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አስታወቁ።

ፕሮፌሰሩ ይህንን የገለጹት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ በኔዘርላንድ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያ ጋር በትላንትናው እለት 20 November 2016 በአምስተርዳም ባደረጉት ውይይት ላይ ነው። በውይይቱ የኦሮሞ አክቲቪስቶችም ተገኝተው ሃሳባቸውን አካፍለዋል።

ስለ ሃገሪቱ ፈታኝ ሁኔታ እና ስለወደፊቱ እጣ ፈንታ በስፋት ያብራሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ መሪ – ፕ/ር መረራ ጉዲና  ከተሰብሳቢው ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።

“አዋጁ እና ኮማንድ ፖስቱ ሕዝባዊ አመጹን ያበርደዋል ወይ?” ተብለው ሲጠየቁ፣ ሃገሪቱ አሁን በመስቀለኛ መንገድ ላይ መሆንዋን ገልጸው አሁን ያለው ሁኔታ ላይ እንዲህ ይሆናል ብሎ መናገር እንደማይቻል ገልጸው፣ነገሮች በሁሉም አቅጣጫ ሊሄዱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ችግሮች እስካልተፈቱና የህዝብ ጥያቄዎች በአግባቡ እስከልተመለሱ ድረስ ሁኔታው ወደ እርስ በርስ እልቂት ሊወስደንም ይችላል። ይላሉ። %e1%88%9d2

በይፋ አልተነገረም እንጂ ኮማንድ ፖስቱ ከአዋጁ በፊትም የነበረ የኢህአዴግ አሰራር እንደሆነ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምእራባውያን ስላላቸው ሚና ተጠይቀው፣ እኛ የቤት ስራችንን ካልሰራን ምእራቡ አለም ምንም ሊረዳን አይችልም። እኛ ካልሰራን እንኳን ምእራቡ አለም እግዚአብሄርም አይረዳንም። ብለዋል።

በዚህ ወቅታዊ የሀገር ጉዳይ ላይ የተዘጋጀ የውይይት ገለጻ ሲሰጡ በዲፕሎማሲው እና በአለም አቀፍ ህብረተሰብ በአንድ በኩል፣ በሃገር ውስጥ የተጀመሩት በርካታ የ”እርቅ” እንቅስቃሴዎችን በስፋት ቃኝተዋል።

በአለም አቀፉ ህብረተሰብ እና በምእራባውያን ሃገሮች በኩል አሁን ለተቃዋሚዎች በር ተከፍቷል ይላሉ ፕ/ር መረራ ጉዲና። በጋራ ሆነን በአንድ ቋንቋ የመናገሩ ህብረታችን ግን አሁንም ፈተና ላይ ነው።

በቅርቡ በአውሮፓ ህብረት ጥሪ ተደርጎላቸው ሃገሪቱ ስላለችበት መስቀለኛ መንገድ በስፋት ተናግረዋል። አሜሪካ በነበሩበት ግዜም ከሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ጋር “አትላንቲክ ካውንስል” ከተባለው የአሜሪካ ቲንክ ታንክ ቡድን ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። በዚህ ውይይት  ሄርማን ኮኽን እና የቀድሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ዴቪድ ሺል የተገኙ ሲሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች በህብረት  ያለመንቀሳቀስ ትኩረት ስቦ እንደነበር ይናገራሉ።

ገዥውን ፓርቲ ከተቃዋሚዎች ጋር ለማግባባት ሰባት የሚያህሉ የእርቅ እና ሰላም ቡድኖች በኢትዮጵያ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል። አብዛኞቹ የ”እርቅ” ቡድኖች ባህላዊውን የ”አንተም ተው ፣ አንተም ተው” ሚና እንኳን የማይጫወቱ አንድን ወገን ብቻ ለመጫን የተቋቋሙ መሆናቸውንም ይተቻሉ።

ስለ ቀድሞው ተማሪያቸው እና ስለ አሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስለ ወርቅነህ ገበየሁ ተጠይቀው፤  በምርጫ ውድድር ይጠቀምበት የነበረው ስም ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ ሲሆን በትምህርት በት ያለው ፋይል ላይ ደግሞ ወርቅነህ ገበየሁ ወልደ ኪዳን እንደሆነ ገልጸዋል። ይህንን ጉዳይ በሁለተኛው መጽሃፋቸውም ላይ መጥቀሳቸውን ተናግረዋል።

በመጨረሻም በሃገር በት በኦሮሞ እና በአማራው ህብረተሰብ እየተፈጠረ ያለው ትብብር እነ ጌታቸው ረዳን ሳይቀር በአደባባይ ወጥተው እንዲናገሩ ያደረገ ትልቅ የታሪክ አሻራ መሆኑን ገልጸው፣ በውጭ ያለውም ወገን የቀድሞ ሂሳብን ማወራረድ አቁሞ፣ በወደፊቱ የሃገሪቱ ሁኔታ ላይ እንዲወያይ ምክር ሰጥተዋል።

በቪዲዮ የተቀረጸው ሙሉ ውይይት እዚህና እዚህ ላይ ይገኛል።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule