• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ መለስ መታሰቢያ ተቋም (Foundation)! – ክፍል ሁለት

May 10, 2013 04:17 am by Editor 1 Comment

መንግስት በመፈንቀል ስልጣን የጨበጠው የትናንቱ አምባገነን መንግስቱ ኃይለማሪያም የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላማዊ ሰልፍ አብዮቱን እንድጠብቅ አደራ ሰጥቶኛል ብሎን ነበር። ስልጣን አልለቅም ማለቱ ነበር። የአምባገነኑ መለስ አደራ መፈክሮች ቢለዋወጡም “የልማት ጠባቂ ነኝ” እያለ መሞቱ ይታወሳል። ዛሬ በስልጣን ላይ ያሉት የአቶ መለስ ፍጡራን አምባገነኖች ደግሞ “የአቶ መለስ ራዕይ ሞግዚት” ነን ይላሉ። ሌላ ሃያ አመቶች ሊገዙን። የትናት በስቲያው አብዮት ጠባቂ፣ የትናንቱ ልማት ጠባቂ፣ የዛሬዎቹ ደግሞ ራዕይ ጠባቂ። የአምባገኖች መተካካት በኢትዮጵያ የሚያከትመው የኢትዮጵያ ህዝብ አፉን እና እጁን አንድ አድርጎ አደባባይ በመውጣት የስልጣን ባለቤት እኔ ነኝ ሲላቸው ብቻ ነው። በሰላማዊ ትግል የመንግስት ስልጣን ባለቤት ሲሆን ብቻ ነው። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 17, 2013 09:20 pm at 9:20 pm

    **ራዕይ አስፈፃሚና ተከታዮቹ ተጠራሩ…የአምባገነኑ መለስ አደራ መፈክሮች ቢለዋወጡም “የልማት ጠባቂ ነኝ” እያለ መሞቱ ይታወሳል።በእርግጥ የቀድሞው ድልድይ አፍራሽ፣ ጎተራ ገልባጭ፣ባለትዳር ሴት ደፋሪ፤ የአሁን አብኦታዊ ዲሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት።ይች ሀውልት ለልትቆም በሥሯ ስንቱ ተቀብሯል?ከእየ ብሔሩ ለመስረቅ ለማሰረቅ፣በልተው ለማባላት እራሳቸውን የሸጡ ሀገር ያስቆረሱ ዘጋ በማፈናቀል መሬት አከራይተው ስንቶች ከበሩ?ቀበሩ?
    ከፍል ፪… አቶ መለስ፥ “አገር ወዳድ፣ የልማት ጀግና፣ ፓን-አፍሪካዊ፣ የሰላም አባት፣ ለህዝብ ፍትህ፣ ጥሩ አስተዳደር እና ዲሞክራሲ ያመጣ” ታላቅ መሪ ነበር ይላል ዘመቻው። ከዚያስ የምሥራቅ ሀገሮችን ውስጠዊ ሚስጠር ዘክዝከው እስኪጨርሱ ሙሉ ድጋፍና ማንቆላጳጰሳቸው ቀጠለ…ሁድአደሩና አድርባዩ ባለሀብት ባለሥልጣን ሆነ ሰውዬው የሰበሰባትን ሳይበላት በጨረር አንጫረሩት…። ነሀሴ 14/2004 ዓ.ም ማለዳ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ለኢትዮጵያውያንና ለመላው አለም አንድ ያልተጠበቀ የጧት መርዶ አረዳ እነኛው የአዞ እንባ እያነቡ አልቅሰው አላቀሱ በእርግጠኝነትም ለመቀበሩ ቆመው ተመለከቱ!።” መለስ ህያው ነው – ራዕዩ ይፈጸም ዘንድም ፋውንዴሽኑ ተመሰረተ!!”ጉድ ነሽ የአንኮበር ቅጠል” አለ ሰውዬው።
    (1ኛ) እርግጥ አቶ መለስ‘አገር ወዳድ‘ ነበርን? እንድሪያስ እሸቴ እንደሚለው አቶ መለስ ‘የልማት ጀግና’ ነበርን?
    **አቶ መልስ ክልል ወዳድ ናቸው።በብሔር፣በነገድ፣ በጎሳ፣ ዘረኝነት፣ን መቃቃር፣ን መበጣበጥን፣ መጠራጠርን፣ ማፈናቀልን፣ ፈጥረዋል አስተምረዋል።፸፪ ማንብብና መፃፍ በማይችል ህዝብ ትቂቶች እነዲህ ይላሉ” አልሞ ተኳሹ መለስ፣ ታግሎ ጣዩ መለስ፣ ተናግሮ ረቺው መለስ፣ አቅዶ ተግባሪው መለስ፣ መርማሪ ተመራማሪው መለስ፣ የአፍሪካ አንድነት አቀንቃኙ መለሰ፣ የኔፓድ ወላጅ አባቱ መለስ፣ የአሁንዋ ኢትዮጵያና አፍሪካ ለውጥ የማእዘን ድንጋዩ መለስ፣ የልማታዊ መንግስት ንድፈሃሳብ ቀማሪና ተግባሪው መለስ፣…ዛሬ በህይወት አይኑር እንጂ ተግባራቱ ሁሉ አሉ፣ ቃሉም ይፈፀማል፡፡(የመልስ ራዕይ ምዕራፍ ፪ ቁጥር ( )ከሞትኩ በኃላም ህያው ነኝ “በሰኔ ፓርላማውን የሚዘጋው መጣሁ ብሎ ከፍቶት ሄደ በለው!!
    (2) እርግጥ አቶ መለስ ፓን-አፍሪካዊ ነበርን?
    ***መለስ ማለት “የአገሩ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካና የአለም ፍፁም ዲሞክራሲያዊ መሪ” (የቀድሞው
    የናይጂሪያ ፕሬዘዳንት፣ ኦባሳነጆ)፣ “መለስ በተለይ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም ዘብ የቆመ” (የሶማሊያው ጠ/ሚኒስትር ሚስተር አብዲ ፋራህ ሺርዶን)፣ “መለስ የተግባር ሰው፤ አፍሪካ ነፃ መሆን አለባት የሚል የማይናወጥ አቋም ያለው” (የጅቡቲ ሪፐብሊክ ፕረዘዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ)፣ “በአለም አቀፍ ጉባኤ የአፍሪካ ምርጥ ልጅ” (የሱዳን ፐሬዚዳንት ኦማር ሃሰነ አልበሽር)፣ አዲሱ የአፍሪካ መሪ፣ አፍሪካን ከሦስተኛው አለም ወደ አንደኛው አለም ደረጃዋን እያሸጋገረ የነበረ ታላቅ መሪ፣ ወዳጅ ጠለት በሚል ክፍልፍይ ውስጥ የማይጠመድ፣ አፍሪካ ባለፉት 50 አመታት የፈፀመችውን ስህተት ያረመ፣ አፍሪካን ከጨለማ ወደ ብርሃን ለመቀየር (አባይን በመገደብ) የጣረና መሰረቱን የጣለ፣ ስለአፍሪካ በ’እነዚያ ሰዎች’ አካባቢ የነበረውን የተዛባ አመለካከት የቀየረ፣ – – -” (የዩጋንዳው ፕሬዘዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ) ሲሉ መለስ ዜናዊን በጥልቀት ገልጸውታል፡፡ የቀድሞ የዓለም ባንክ ፕሬዘዳንትም “አፍሪካ ያለ መለስ አስተሳሰብ የተሻለ ኢኮኖሚ ልትፈጥር አትችልም ነበር” ሲሉ መግለፃቸውን ማንነቱ ያልታወቀ ቱልተላ አይጋ ፎረም ላይ ነፍቶታል እርግጠኛ ነኝ አቶ መለስ አልፃፉትም አድርባይ ምሁር እንጂ…መለስ የሠራው እንዲነገር ሐውልት እነዲቆምለት ቢልቦርድ እንዲሠቀልለት ደረት እነዲደቃለት ድንኳን ተጥሎ የዕርዳታ ስንዴ ንፍሮ እንደወቃ አልተናዘዘም!
    (3) እርግጥ አቶ መለስ የኢትዮጵያ የሰላም አባት ነበርን?
    **ደረጃውን የጠበቀ መፀሕፍት ቤትና የምርምር ማእከል፣ ትምህርታዊ ፕሮግራሞችን መዘርጋትና ማስፋፋት፣ ነፃ የትምህርት ዕድል መፍጠር፣ በሥራቸው ብልጫ ላሳዩ የሚሰጥ ሽልማት፣ ለአየር ንብረት እንክብካቤ የሚደረግ ድጋፍ እና የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መታሰቢያ ፓርክ ናቸው፡፡በእነዚህ አበይት የፋውንዴሽኑ ተግባራት ስር ሌሎች በርካታ ንዑስ ተግባራት የተዘረዘሩ ሲሆን ሁሉም ዋና አላማቸው የመለስን ሌጋሲ አጠናክሮ መቀጠልና ማስቀጠል” ይህ የሚያስረዳው ሰውዬው “የሙታን ፓርቲ” ማቋቋማቸውን እንጂ ስለሠላም የሚናገር አደለም።ይልቁንም በዘህ ፋውንዴሽን አማካኝነት ብዙ ባለድረሻ አካላት እነደሚኖሩ ተደብቆ የነበረው ገንዘብ ሁሉ በእርዳታ መልክ ተመልሶ ለህሓት/ወያኔ/ኢህአዴግና/መከላከያ ሚ/ር እና ለኢፈርት ጥሩ የወንጀል መከለያ ተቐም ሆኖ ኢትኦጵያን ለመበታተንና ለማተራመስ ለሚፈልጉ ሁሉ ጥሩ የመሸጋገሪያም የመግቢያም የመተላለፊያም ድልድይ ሆኖ ያገለግላል ይህንንም በለንደን የተደረገውን ጉባዔ ያጢኑ!!
    (4) እርግጥ አቶ መለስ ለኢትዮጵያ ህዝብ ፍትህ፣ ጥሩ አስተዳደር እና ዲሞክራሲ አምጥቷልን?
    ***ይህ ሁሉ ከሆነ ሴት እህቶቻችን የዐረብ መጫወቻ ህጻናት ለነጭ መሸት ወጣቱ ያደንዛዥ ዕፅ የሴሰኝነት የአልኮልና የወንጀል ልምድ መች ይኖረው ነበር።የሥራ አጥ ቁጥር መጨመር፣ የትምህርት ውድቀት፣ የኑሮ ውድነት፣የጤና ቀውስ፣ በእሥረኛ ብዛት፣በመፈናቀልና ከጥቂት ግለሰቦች በቀር በድህነት ሉዓላዊነቷ፣ሰንደቋ፣ዜጎቿ፣ባሕልና ሃይማኖትን ያረከሱባት ሀገር አድረገው ለሌባ አሳልፈው ሰጥተውን እሳቸው ያለፉ የ፵፻፪፻ብር ቅጥረኛ ድሃ ነበሩ።…አዜብ መስፍን
    “ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው”…ለመሆኑ ሌሎች እኛ ቤት ምን አደርጋሉ? ?
    “ሱዳን ሁለት ሚሊዮን ዶላር፣ ደቡብ ሱዳን አንድ ሚሊዮን ዶላር፣ ጅቡቲ 500 ሺህ ዶላር እንዲሁም ዩጋንዳ 300
    ሺህ ዶላር ለፋውንዴሽኑ ምስረታ መስጠታቸውን የየሀገሮቹ መሪዎች በዚሁ እለት አስታውቀዋል፤ ይህ ድጋፋቸው አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ ቀጣይ መሆኑን ጭምር በማከል። መለስ በጉባኤው “ወደር የለሽ አለም አቀፍ ምሁር፣ አብሪ ኮከብ…” ወዘተ ከሚሉት ምስክርነታቸው ጀምሮ ብዙ ብዙ ተብሎላቸዋል፡፡ “በዚህ አለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ በሚገነባው “መለስ ፋውንዴሽን” ተመራማሪዎች፣ የፖለቲካ ተንታኞች፣ የአገራት መሪዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ አባላት – – – ሁሉ የመለስን ተሞክሮ የሚቋደሱበት፣ የሚማሩበት፣ የሚመራመሩበትና በርካታ ለመጪው ትውልድ አመራር አባላት በቂ የመነሻ ሃሳብ የሚያገኙበት በጥቅሉ ለጥልቅ ጥናትና ምርምር አንጡራ ሀብት መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ያላወቀውንና ያላመንበትን በግድ እንዲያምን የራሱን ገንዘብ ሌሎች በእርዳታ ውም እሠጡለት ያላግጡበታል፣ ይመፃደቁበታል፣ንግድ ይከፍቱበታል፣ከትውልድ ትውልድ የሚሻገር ሥልጣናቸውን ያጠናክሩበታል፣ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች እያነቡ እስክስታ በዘፈን ካሴት በመሸጥ፣ በባርኔጣ፣ በካኒቴራ፣ በአንገት ልብስ፣ በክልል ባንዲራ፣ ታጅሎ በወያኔ ደጋፊ ኢትዮጵአ ጠላቶች ታጅቦ በቋንቋ በዘር በብሔር ሱቧደን ” ጉበት ሲያድር አጥንት” ይሆናልና ዓረብ፣ ቻይና፣ህንድ፣ የአውሮፓውያን ክንድ ከኢንቨስትመንት ወደ ነዋሪነት ቀጥሎም የሀገር ባለቤትነት ሲሸጋገር ቆመህ ተመልከት ያስቸግርሃል ተቀምጦ ማንሳት በለው!! ከሀገረ ካናዳ በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule