• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቆሻሻ የሚጥሉና ዘንባባ የሚገጩ ቅጣት አንሷል ተባለ

July 24, 2024 04:14 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ በየቦታው ቆሻሻ ለሚጥሉና በቅርቡ የተተከሉትን ዘንባባዎች ለሚገጩ የሚከፈለው ቅጣት ያነሰ መሆኑን በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ተግባሩን ለመከላከል የሌሎች አገራት ልምድ ተግባራዊ እንዲደረግና ጥፋቱን ለመቀነስ የቅጣት መጠኑ መጨመር እንዳለበት ነው ነዋሪዎች የተናገሩት።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች የሚገኙ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጋር ባደረገው ኢመደበኛ ጥናት ሁሉም ተጠያቂዎች የሰጡት ምላሽ ጥፋቱን በሚፈጽሙ ላይ የተበየነው ቅጣት ከዚህ መጨመር እንዳለበት ነው። ሌላው የሰጡት ምላሽ የሌሎች አገራትን ተሞክሮ በማጥናት በአገራችን ላይ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት ሲሆን፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ እንደ ጥንቃቄ የሰጡት ምላሽ ሁሉም ሰው አውቆ ዘንባባ ስለማይገጭ እንደ አገጫጩ ምክንያትና ዐውድ ቅጣቱም በዚያው መልኩ አጥፊዎችን ከአደጋ አድራሾች በመለየት የሚፈጸም ሊሆን እንደሚገባው ገልጸዋል።

ለምሳሌ በግዴለሽነትና ከተለመደው ፍጥነት በላይ ወይም ሌላውን ለመቅደም ወዘተ በሚደረግ መልኩ የሚገጭ ዘንባባ እና በሌላ አሽከርካሪ የተፈጸመን ስህተትና የሚያስከትለውን ከፍተኛ ጉዳት ለመታደግ ሲባል ሰውን ከመግጨት ይልቅ ዘንባባውን መግጨት የግድ የሚሆንበት ጊዜ የሚፈጸም ለይቶ መቅጣት ተገቢ ነው በማለት በምሳሌ ያስረዱም ነበሩ። ሌሎች ደግሞ ቆሻሻ መጣል ትክክል አለመሆኑ በዘመቻ መልክ ቢሠራበት እና ከታዋቂ ግለሰቦች ጀምሮ የኪነት ሰዎችን ያካተተ መርሃግብር ቢዘጋጅ፤ ተማሪዎችንም ብናስተምር ጥሩ ለውጥ ልናመጣ እንችላለን የሚል ጥቆማ ሰጥተዋል።

ጥናቱ ኢመደበኛና በሃብት ውሱንነት ምክንያት የተወሰደው ናሙናም በቂ ነው ባይባልም በተወሰነ መልኩ ጠቋሚ እንደሆነና የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት የተሻለ ጥናት እንዲያደርጉ የሚያመላክት እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል።

በአዲስ አበባ ከተማ በኮሪደር ልማት የተሠሩ ሥራዎችን በአግባቡ ያልተጠቀሙ እና ጉዳት ያደረሱ አካላት መቅጣት መጀመሩን ኢዜአ በቅርቡ ዘግቦ ነበር። በዚህም 3 ተቋማት ከተፈቀደ ቦታ ውጪ ቆሻሻ በመጣል እንደየጥፋት ደረጃቸው 100 ሺሕ ፣ 50 ሺ እና 20 ሺሕ ብር የተቀጡ ሲሆን 5 አሽከርካሪዎች በመንገድ አካፋይ ላይ የተተከሉ ዘንባባ ዛፎችን ገጭተው በመጣላቸው እንደየጥፋት ደረጃቸው ከ150 እስከ 300 ሺሕ ብር እንዲሁም 11 ሰዎች ከተፈቀደው የእግረኞች መንገድ ውጪ በመሄዳቸው ከ150 እስከ 1000 ብር ተቀጥተዋል።

የሠለጠኑ በሚባሉ አገራት የሚታየው ንጽህና ዋጋ የተከፈለበት ነው። ለምሳሌ በአሜሪካ የኦሪጎን ጠቅላይ ግዛት ያልጠፋ የሲጋራ ቁራጭ መጣል እስከ 2,500 ዶላር የሚስቀጣና ለስድስት ወር የሚያሳስር ነው። ግዛቱ ለሰደድ እሣት የተጋለጠ በመሆኑ የቅጣቱ መጠንም ከበድ ይላል።

በአጠቃላይ በአሜሪካ ቆሻሻ መጣል የሚያስከትለው ቅጣት በየግዛቱ የተለያየ ነው። ቅጣቱን በተመለከተ ብያኔ የሚያስተላልፉ ፍርድ ቤቶች ከገንዘብ ቅጣት በተጨማሪ የተጣለውን ቆሻሻ ማንሳትን የጨመረ ቅጣት ይበይናሉ። በጣም ትንሹ የሚባለው ቅጣት የማሳቹሴትስ ግዛት የሚበይነው የ25 ዶላር ሲሆን ትልቁ ደግሞ የሜሪላንድ ግዛት የሚበይነው የ30,000 ዶላር ቅጣት ነው። ከዚህ ሌላ እንደየግዛቱ የጥፋቱ ፈጻሚዎች መንጃ ፈቃዳቸው ሊታገድ፤ ዘብጥያ ሊወርዱም ይችላሉ። የበለጠ መረጃ ለማግኘት እና በእያንዳንዱ ግዛት የተደነገገውን ቅጣት ለመረዳት እዚህ ላይ ይጫኑ (https://www.ncsl.org/environment-and-natural-resources/states-with-littering-penalties)።

የቆሻሻ መጣል ጉዳይ ካሳሰባቸው መካከል ለምሳሌ በአሜሪካ የቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት “Don’t Mess With Texas” የሚለውን በርካታ ሽልማቶችን ያስገኘ የጸረ ቆሻሻ ዘመቻ ከመጀመሩ በፊት በ1980ዎቹ በቴክሳስ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ የሚጣለው ቆሻሻ ግዛቱን እስከ 20 ሚሊዮን ዶላር ያስወጣው ነበር። ይህ ዘመቻ በተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ዘፋኞች፣ የተለያዩ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ በትምህርት ቤቶች ወዘተ እንዲታወቅ በመደረጉ ቆሻሻ መጣል አሁንም እንደየቦታው ከፍተኛ ቅጣት የሚያስቀጣ ሆነ፤ አርባ ዓመት አካባቢ ያስቆጠረው ዘመቻ እስካሁንም ቀጥሏል።

በአውሮጳ የሚኖሩ ጎልጉል ያነጋገራቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊ እንዳሉት “አብዛኛው ዳያስፖራ በውጭ አገር ሲኖር ንጽሕናውን፣ ለዛፎች የሚደረገውን እንክብካቤ፤ አልፎ ተርፎ ያለ መንግሥት ፈቃድ በቤት ያለ ዛፍ እንኳን መቁረጥ እንደሚከለከል ያውቃል፤ ቅጣቱ የከፋ እንደሆነ አምኖ ተቀብሎ ሕጉን አክብሮ ይኖራል፤ ነገር ግን ኢትዮጵያ ላይ ተመሳሳይ ነገር ሲተገበር አቃቂር የሚያወጣውና በየማኅበራዊ ሚዲያ መሳለቂ የሚያደርገው ነገር አይገባኝም። እነዚህ የምናደንቃቸው አገራት ሕዝብ ካለው ዲሲፒሊን በተሻለ ያገራችን ሕዝብ በሕግ ለመመራትና ትክክል ያልሆነን ነገር ትቶ ለሕግ ለመገዛት የሚቀልለው ነው፤ ነገርግን ቆሻሻ ጥሩ ነገር ይመስል የኖርንበት የተበላሸ መስመር እንዲቀጥል፤ ለዛፎች ምንም ትኩረት ሳይሰጥ ሲገጩም ገጪዎች በነጻነት እንዲያልፉ ከተደረገ አውሮጳንና አሜሪካንን እያደነቅን መኖር ነው፤ ይህ ደግሞ በራስ ላይ መሳቅ ነው” ብለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: Anti littering campaign in Ethiopia, Don't Mess With Texas, Littering, Littering campaign

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule