• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጃዋር ሰለባዎች ዝርዝር በከፊል!

October 28, 2019 04:16 am by Editor Leave a Comment

ራሱን ከሚገባው በላይ መካብ የማይበቃው የጫትና የመጠጥ ሱሰኛው ጃዋር መሐመድ ተጽዕኖ ፈጣሪ ነኝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለሥልጣን ያበቃሁት እኔ ነኝ፤ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አህመድ ግራኝ ነኝ፤ ብዙ ዕውቀት አለኝ፤ ብዙ ችሎታ አለኝ፤ ወዘተ በማለት ያለማቋረጥ ከመትፋት አልፎ “ተከበብኩኝ፤ ልገደል ነው” የሚል የሃሰት መረጃ በማውጣት፤ ከህወሓት ጋር በመመሳጠር ለመተግበር የሞከረውን ዕቅድ እንደፈለገ የሚነዳውንና ማሰብ የተሳነውን የቄሮ ኃይል በመጠቀም ለማስፈጸም ባደረገው ሙከራ በግፍ የተጨፈጨፉ ንጹሃን ዝርዝር የሚከተለው ነው፤ ጃዋርን የምትደግፉ እፈሩ! ኅሊና ካላችሁ ወደምታምኑት አምላክ ንሰሐ ግቡና ተመለሱ፤ ከሌላችሁ ከሱ ያላነሰ ፍርድን በራሳችሁ ወይም በልጆቻችሁ እንደምታገኙ አትጠራጠሩ፤  

አምቦ

በአምቦ ከተማ ከተገደሉት ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በጥይት ከተገደሉት መካከል የ80 ዓመቱ አዛውንት አቶ ሞሮዳ ሞሳ የሚባሉ ይገኙበታል በማለት ነዋሪዎች ተናግረዋል። አቶ ሞረዳ ልጃቸውን ፍለጋ በወጡበት ከጸጥታ አስከባሪ ኃይል በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸውን የከተማው ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በአምቦ ከተገደሉት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ሰዎቸ በጥይት ተመትተዋል።

የአምቦ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር አቶ ደበበ ፈጠነ፤ “14 ሰዎች በጥይት ተመተው እኛ ጋር መጥተዋል። ሁለቱ ህይታቸው አልፏል። 9 ሰዎች ደግሞ ተኝተው እየታከሙ ሲሆን የተቀሩት ቀላል ህክምና ተደርጎላቸው ወደየቤታቸው ተመልሰዋል” በማለት ያስረዳሉ።

አቶ ደበበ ወደ ሆስፒታላቸው የመጡት ሰዎች በሙሉ ወንዶች መሆናቸውን እና ዕድሜያቸውም ከ17-80 እንደሚገመት ተናግረዋል። በዚህም በአምቦ ትናንት 3፤ ዛሬ 2 በድምሩ የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል።

ዶዶላ 

በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ ረቡዕና ሐሙስ በነበሩ ግጭቶች በጠቅላላው 6 ሰዎች መገደላቸውም ታውቋል።  ሐሙስ በነበረ ግጭት 4 ሰዎች ሞተው ወደ ዶዶላ አጠቃላይ ሆስፒታል መምጣታቸውን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ቶላ ቢዮ ተናግረዋል።  ረቡዕ ደግሞ ሁለት ሰዎች ተገድለው ነበር።

ምስራቅ ሐረርጌ 

ረቡዕ እና ሐሙስ በምስራቅ ሃረርጌ በነበሩ ግጭቶች የሟቾች ቁጥር ቢያንስ 6 መድረሱን ሰምተናል።  በዞኑ የኮሚኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ አየለ ዴሬሳ፤ በጉሮ ጉቱ 5 እንዲሁም በሃማሬሳ 1 ሰው መገደሉን ተናግረዋል።

ባለሜንጫውና ቀድሞ የጃዋር ተቃዋሚ የነበረው አፈንዲ ሙተቂ

አቶ አየለ፤ ትናንት 5ቱ ሰዎች የተገደሉት ጉሮ ጉቱ በምትባል ከተማ ወደ ብሄር በተቀየር ግጭት ስለመሆኑ ይናገራሉ። “አንድ ባለሃብት የደህንነት ስጋት ተሰምቶት ሁለት ሰዎችን በጥይት ተኩሶ ገደለ። ከዚያም በቂም በቀል ግለሰቡ እና ሁለት የቤተሰብ አባላቱ ተገደሉ” ሲሉ ሁኔታውን ለቢቢሲ አስረድተው ነበር። 

የአወዳይ ከተማ ነዋሪ የሆነ ወጣት ከመከላከያ ሠራዊት በተተኮሰ ጥይት ስለመገደሉ የአወዳይ ከተማ ከንቲባ ጃፋር ሙሐመድ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።

ሐረር 

በሐረር ከተማ ረቡዕ ዕለት 3 ሰዎች መገደላቸውን ከነዋሪዎች ሰምተናል።

ድሬ ዳዋ

በድሬዳዋ ከተማም ረቡዕ 1 ሰው የተገደለ ሲሆን ዛሬ ደግሞ 4 ሰዎች ተገድለዋል። የድል ጮራ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አብዱራሃማን አቡበከር ለህክምና ከመጡት ሰዎች መካከል 4ቱ ህይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።

ባሌ ሮቤ

በባሌ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ሮቤ ከተማም ባለፉት ሁለት ቀናት ግጭት ተከስቶ በሰው እና በአካል ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል። ቢቢሲ በዞኑ በተከሰቱት ግጭቶች በሰው እና በአካል ላይ የደረሰውን ጉዳት ከገለልተኛ አካል ለማጣራት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። 

ይህ የሟቾች አሃዝ ከሆስፒታል ምንጮች፣ ከመንግሥት አካላትና ከሟች ቤተሰቦች የተገኘ ሲሆን ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል ስጋት አለ። መንግሥት በግጭቱ ምክንያት የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ ግልጽ ባያደርግም፤ ግጭት በተከሰተባቸው ስፍራዎች የመከላከያ ሠራዊት እንዲሰማራ መደረጉን የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ ሜጄር ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ዛሬ ከሰዓት አስታውቀዋል። 

የተቃውሞ ሠልፍ በተካሄደባቸው የኦሮሚያ፣ ሐረርና ድሬዳዋ ከተሞች በክልሎችና በአስተዳደሩ ጥያቄ መሰረት በአምቦ፣ ቢሾፍቱ፣ ባሌ ሮቤ፣ አዳማ፣ ሞጆ እንዲሁም በድሬ ዳዋ እና ሐረር የመከላከያ ሠራዊት እንዲሰማራ መደረጉን ተናግረዋል።

1. ወጣት እሱባለው – ድሬዳዋ ገንደቆሬ ሰፈር፤ (ይህ ወጣት ገና የ8 ወር ጨቅላ ልጅ አባት ነበርም ተብሏል)

2. ደረጄ ሀይሉ (ምስራቅ ሀረርጌ – በሮዳ)

3. ዳመና ሀይሉ (ምስራቅ ሀረርጌ – በሮዳ)

4. አቶ ሞረዳ (አምቦ በራፋቸው ላይ የተገደሉ)

5. ወ/ሮ ወላንሳ ፍቅረ (የአቶ ዳመና ሀይሉ ሚስት – ምስራቅ ሀረርጌ በሮዳ)

6. መስፍን አለማየሁ (ሀረር ከተማ ቤቱ ተቃጥሎ በደቦ ፍርድ ተገድሎ አስከሬኑ የውሀ ቦይ ውስጥ የተጣለ)

7. አምቦ ከተማ ውስጥ ሶስት ወገኖች እንደተገደሉ VOA ዘግቧል።

8. አቶ ገላሁንና ሌሎች ሶስት ኢትዮጵያውያን (ወለቴ – አዲስአበባ አካባቢ በቄሮ የተገደሉ)

9. አቶ አነጋግር ደሴ – ባሌ ዶዶላ

10. አቶ ዝናቡ ጌታሁን – ባሌ ዶዶላ

11. አቶ ግርማ ተስፋዬ – ባሌ ዶዶላ

12. ወጣት ምህረተአብ ደጀኔ – ባሌ ዶዶላ

13. ወጣት እሸቱ ተስፋዬ – ባሌ ዶዶላ

14. አቶ ሃይሉ አስማረ – ባሌ ዶዶላ

15. ሰመር ኑሪ – ናዝሬት

16. ፍጹም ወጋየሁ – ናዝሬት

17. አቢቲ ታምራት – አርሲ ኮፈሌ

18. አቶ ታምራት ጸጋዬ – አርሲ ኮፈሌ – ልጃቸውም የተገደለ

19. አብርሃም ክንዴ – ድሬዳዋ

20. ትዕግስት – ገንደሀራ ናዝሬት

ከላይ በቢቢሲ አማርኛ ከተዘገበው ጋር ይህ ዝርዝር ከማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰበሰበና ስማቸው እስካሁን የታወቀው ብቻ ነው። ሰበታ አካባቢ ሶስት ጋሞ ኢትዮጵያውያን እንደተገደሉ መረጃ አለ። ደብረ ዘይት ከስድስት በላይ ወጣቶች ተገድለዋል። ቢቢሲ የመንግሥት ምንጮችን ጠቅሶ እስካሁን ህይወታቸው የተቀጠፈው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 67 መድረሱን ዘግቧል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

(ፎቶ፤ ከአፈንዲ ፎቶ በስተቀር ሌሎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ በመሆናቸው የሰሞኑ ግድያ ለመሆናቸው ማረጋገጫ የለም፤ የደረሰውን ጭፍጨፋ ለማሳየት የቀረቡ ናቸው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: jawar, Left Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule