• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጃዋር ሰለባዎች ዝርዝር በከፊል!

October 28, 2019 04:16 am by Editor Leave a Comment

ራሱን ከሚገባው በላይ መካብ የማይበቃው የጫትና የመጠጥ ሱሰኛው ጃዋር መሐመድ ተጽዕኖ ፈጣሪ ነኝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለሥልጣን ያበቃሁት እኔ ነኝ፤ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አህመድ ግራኝ ነኝ፤ ብዙ ዕውቀት አለኝ፤ ብዙ ችሎታ አለኝ፤ ወዘተ በማለት ያለማቋረጥ ከመትፋት አልፎ “ተከበብኩኝ፤ ልገደል ነው” የሚል የሃሰት መረጃ በማውጣት፤ ከህወሓት ጋር በመመሳጠር ለመተግበር የሞከረውን ዕቅድ እንደፈለገ የሚነዳውንና ማሰብ የተሳነውን የቄሮ ኃይል በመጠቀም ለማስፈጸም ባደረገው ሙከራ በግፍ የተጨፈጨፉ ንጹሃን ዝርዝር የሚከተለው ነው፤ ጃዋርን የምትደግፉ እፈሩ! ኅሊና ካላችሁ ወደምታምኑት አምላክ ንሰሐ ግቡና ተመለሱ፤ ከሌላችሁ ከሱ ያላነሰ ፍርድን በራሳችሁ ወይም በልጆቻችሁ እንደምታገኙ አትጠራጠሩ፤  

አምቦ

በአምቦ ከተማ ከተገደሉት ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በጥይት ከተገደሉት መካከል የ80 ዓመቱ አዛውንት አቶ ሞሮዳ ሞሳ የሚባሉ ይገኙበታል በማለት ነዋሪዎች ተናግረዋል። አቶ ሞረዳ ልጃቸውን ፍለጋ በወጡበት ከጸጥታ አስከባሪ ኃይል በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸውን የከተማው ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በአምቦ ከተገደሉት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ሰዎቸ በጥይት ተመትተዋል።

የአምቦ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር አቶ ደበበ ፈጠነ፤ “14 ሰዎች በጥይት ተመተው እኛ ጋር መጥተዋል። ሁለቱ ህይታቸው አልፏል። 9 ሰዎች ደግሞ ተኝተው እየታከሙ ሲሆን የተቀሩት ቀላል ህክምና ተደርጎላቸው ወደየቤታቸው ተመልሰዋል” በማለት ያስረዳሉ።

አቶ ደበበ ወደ ሆስፒታላቸው የመጡት ሰዎች በሙሉ ወንዶች መሆናቸውን እና ዕድሜያቸውም ከ17-80 እንደሚገመት ተናግረዋል። በዚህም በአምቦ ትናንት 3፤ ዛሬ 2 በድምሩ የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል።

ዶዶላ 

በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ ረቡዕና ሐሙስ በነበሩ ግጭቶች በጠቅላላው 6 ሰዎች መገደላቸውም ታውቋል።  ሐሙስ በነበረ ግጭት 4 ሰዎች ሞተው ወደ ዶዶላ አጠቃላይ ሆስፒታል መምጣታቸውን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ቶላ ቢዮ ተናግረዋል።  ረቡዕ ደግሞ ሁለት ሰዎች ተገድለው ነበር።

ምስራቅ ሐረርጌ 

ረቡዕ እና ሐሙስ በምስራቅ ሃረርጌ በነበሩ ግጭቶች የሟቾች ቁጥር ቢያንስ 6 መድረሱን ሰምተናል።  በዞኑ የኮሚኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ አየለ ዴሬሳ፤ በጉሮ ጉቱ 5 እንዲሁም በሃማሬሳ 1 ሰው መገደሉን ተናግረዋል።

ባለሜንጫውና ቀድሞ የጃዋር ተቃዋሚ የነበረው አፈንዲ ሙተቂ

አቶ አየለ፤ ትናንት 5ቱ ሰዎች የተገደሉት ጉሮ ጉቱ በምትባል ከተማ ወደ ብሄር በተቀየር ግጭት ስለመሆኑ ይናገራሉ። “አንድ ባለሃብት የደህንነት ስጋት ተሰምቶት ሁለት ሰዎችን በጥይት ተኩሶ ገደለ። ከዚያም በቂም በቀል ግለሰቡ እና ሁለት የቤተሰብ አባላቱ ተገደሉ” ሲሉ ሁኔታውን ለቢቢሲ አስረድተው ነበር። 

የአወዳይ ከተማ ነዋሪ የሆነ ወጣት ከመከላከያ ሠራዊት በተተኮሰ ጥይት ስለመገደሉ የአወዳይ ከተማ ከንቲባ ጃፋር ሙሐመድ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።

ሐረር 

በሐረር ከተማ ረቡዕ ዕለት 3 ሰዎች መገደላቸውን ከነዋሪዎች ሰምተናል።

ድሬ ዳዋ

በድሬዳዋ ከተማም ረቡዕ 1 ሰው የተገደለ ሲሆን ዛሬ ደግሞ 4 ሰዎች ተገድለዋል። የድል ጮራ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አብዱራሃማን አቡበከር ለህክምና ከመጡት ሰዎች መካከል 4ቱ ህይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።

ባሌ ሮቤ

በባሌ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ሮቤ ከተማም ባለፉት ሁለት ቀናት ግጭት ተከስቶ በሰው እና በአካል ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል። ቢቢሲ በዞኑ በተከሰቱት ግጭቶች በሰው እና በአካል ላይ የደረሰውን ጉዳት ከገለልተኛ አካል ለማጣራት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። 

ይህ የሟቾች አሃዝ ከሆስፒታል ምንጮች፣ ከመንግሥት አካላትና ከሟች ቤተሰቦች የተገኘ ሲሆን ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል ስጋት አለ። መንግሥት በግጭቱ ምክንያት የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ ግልጽ ባያደርግም፤ ግጭት በተከሰተባቸው ስፍራዎች የመከላከያ ሠራዊት እንዲሰማራ መደረጉን የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ ሜጄር ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ዛሬ ከሰዓት አስታውቀዋል። 

የተቃውሞ ሠልፍ በተካሄደባቸው የኦሮሚያ፣ ሐረርና ድሬዳዋ ከተሞች በክልሎችና በአስተዳደሩ ጥያቄ መሰረት በአምቦ፣ ቢሾፍቱ፣ ባሌ ሮቤ፣ አዳማ፣ ሞጆ እንዲሁም በድሬ ዳዋ እና ሐረር የመከላከያ ሠራዊት እንዲሰማራ መደረጉን ተናግረዋል።

1. ወጣት እሱባለው – ድሬዳዋ ገንደቆሬ ሰፈር፤ (ይህ ወጣት ገና የ8 ወር ጨቅላ ልጅ አባት ነበርም ተብሏል)

2. ደረጄ ሀይሉ (ምስራቅ ሀረርጌ – በሮዳ)

3. ዳመና ሀይሉ (ምስራቅ ሀረርጌ – በሮዳ)

4. አቶ ሞረዳ (አምቦ በራፋቸው ላይ የተገደሉ)

5. ወ/ሮ ወላንሳ ፍቅረ (የአቶ ዳመና ሀይሉ ሚስት – ምስራቅ ሀረርጌ በሮዳ)

6. መስፍን አለማየሁ (ሀረር ከተማ ቤቱ ተቃጥሎ በደቦ ፍርድ ተገድሎ አስከሬኑ የውሀ ቦይ ውስጥ የተጣለ)

7. አምቦ ከተማ ውስጥ ሶስት ወገኖች እንደተገደሉ VOA ዘግቧል።

8. አቶ ገላሁንና ሌሎች ሶስት ኢትዮጵያውያን (ወለቴ – አዲስአበባ አካባቢ በቄሮ የተገደሉ)

9. አቶ አነጋግር ደሴ – ባሌ ዶዶላ

10. አቶ ዝናቡ ጌታሁን – ባሌ ዶዶላ

11. አቶ ግርማ ተስፋዬ – ባሌ ዶዶላ

12. ወጣት ምህረተአብ ደጀኔ – ባሌ ዶዶላ

13. ወጣት እሸቱ ተስፋዬ – ባሌ ዶዶላ

14. አቶ ሃይሉ አስማረ – ባሌ ዶዶላ

15. ሰመር ኑሪ – ናዝሬት

16. ፍጹም ወጋየሁ – ናዝሬት

17. አቢቲ ታምራት – አርሲ ኮፈሌ

18. አቶ ታምራት ጸጋዬ – አርሲ ኮፈሌ – ልጃቸውም የተገደለ

19. አብርሃም ክንዴ – ድሬዳዋ

20. ትዕግስት – ገንደሀራ ናዝሬት

ከላይ በቢቢሲ አማርኛ ከተዘገበው ጋር ይህ ዝርዝር ከማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰበሰበና ስማቸው እስካሁን የታወቀው ብቻ ነው። ሰበታ አካባቢ ሶስት ጋሞ ኢትዮጵያውያን እንደተገደሉ መረጃ አለ። ደብረ ዘይት ከስድስት በላይ ወጣቶች ተገድለዋል። ቢቢሲ የመንግሥት ምንጮችን ጠቅሶ እስካሁን ህይወታቸው የተቀጠፈው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 67 መድረሱን ዘግቧል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

(ፎቶ፤ ከአፈንዲ ፎቶ በስተቀር ሌሎቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ በመሆናቸው የሰሞኑ ግድያ ለመሆናቸው ማረጋገጫ የለም፤ የደረሰውን ጭፍጨፋ ለማሳየት የቀረቡ ናቸው)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: jawar, Left Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule