• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ

December 14, 2022 09:59 am by Editor 1 Comment

ድሮ ገና ከዓመታት በፊት በ12 ዓመቱ ነበር ሰውን የመርዳት ፅንስ በትንሽ ልቡ ውስጥ የተጸነሰው። ሳድግ የራሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት ኖሮኝ ሰዎችን እረዳለሁ እያለ ያወራ ነበር። የእድሜ አቻዎቹ ዶክተር፣ ኢንጅነር፣ ፓይለትና ሌሎችም እሆናለሁ በሚሉበት ለጋ እድሜ የሱ ትንሽ ልብ መሻት አድጎ ሰውን መርዳት መቻል ነበር። ዛሬም በሕይወት ጉዞው ላይ በብዙ ካደገም በኋላ የየቀን ንግግሩ የዘወትር ውዳሴው “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የሚል ቃል ነው። ሰው ስለሆነ ብቻ ሰው ይረዳልና።

የራስን ሕይወት ትቶ ስለሰው በሚኖረው ባሕሪው ከሰዎች መካከል ይለያል። የሥጋ ሕመሙ የነፍሱን ቁስል በሻረለት መልካም ሥራው ይታወቃል። ድንቅ የመልካምነት ምሳሌ፣ የመቻል አብነት፤ የደግ ልብ ጌታ ነው። የጥሩዎች ዕንቁ የደጎች አውራ ነው። ብዙዎች በተለያዩ ጊዜያት ደጋችን ነህ ሲሉ በይፋ አመስግነውታል። ዓመታዊው የቅን ልብ ባለቤቶችን እውቅና ሰጪው የበጎ ሰው ሽልማትም አንተ የመሰናዷችን ባለ በጎ ልብ ነህ ሲል ሽልማት ሰጥቶታል። የክብር ዶክትሬት ባለቤቱ የመቄዶኒያ ወላጅ ወጣት ቢንያም በለጠን።

ዘመኑ እናት ለልጇ አባት ወንድሙን እህት አክስቷን የተቸገሩበት፣ ሰው በሰው ላይ የጭካኔ በትሩን በገዛ ወገኑ ላይ የሚያሳርፍበት ቢሆንም ከዚህ በተቃራኒ ለሰው ልጅ በጎ የሚሠሩ ጥቂት ቅን ልቦች አሉ። በተለይ ሰው በሕመም ሲጎዳ እንኳን ባዳ ዘመድ ሩቁ ይሆናል። የታመመ ሰው ደግሞ በሕመም ጉዳት ምክንያት ብዙ አስቸጋሪ ነገሮች አያጣውም። በሚከብድ የሕመም ጣር ውስጥ ያለን ሰው አክሞ ወደ ቀድሞ ጤንነቱ መልሶ ተንከባክቦ ማኖር ግን በብዛት በቅርብ ሰዎች የሚከወን ተጨማሪ አቅምንም የሚጠይቅ ነበር።

ደፋሩ ቢንያም በለጠ ግን ይህን ከወነ፤ በኢትዮጵያ የጊዜ ቀመር 2004 የበጎነት ሥራውን አርባ ያህል ሰዎችን ከሜዳ በማንሳት አሐዱ አለ። አንዳንድ ሰው አይደለም በመኖር በሕመም ይማራል፤ በቀና ቀኖቹ ብቻ ሳይሆን የሕይወቱ ክፉ ቀናትም እሱን ለማስተማር ዝግጁ ሆነው ይቀርባሉ፤ ያኔ ከዓመታት በፊት ሰውና ቀን የጣላቸውን በማንሳት የተጀመረው የቀናነት ጉዞ ዛሬ ላይ ቁጥሩን አሳድጎ ከሰባት ሺህ አምስት መቶ ለሚልቁ ነፍሶች መጠጊያ ታዛ ሆኗል።

የክርስቲያኖች የሕይወት መሠረት በሚባለው ቅዱስ መጽሐፍ ላይ ተከትቦ የሚገኝ አንድ ቃል ዛሬ የብዙኃን መጠለያ ለሆነው መቄዶኒያ ስያሜ መነሻ መሆኑን ራሱ ቢንያም ይናገራል። እንዲህም አለ፤ የመቄዶኒያ ሰዎች በብዙ ተፈትነው ሳለ የድህነታቸው ጥልቀት የልግስናቸውን መጠን አብዝቶታል ይላል የተከተበው ቃል፤ ድሀ ቢሆኑም ለገሱ የሚል ትርጓሜንም ይይዛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሠራተኛና አመራሮችም ዓመታዊ የሠራተኞች ቀናቸውን በመቄዶኒያ የአረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ተረጂዎችን ምሳ በማብላትና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን በማከናወን አሳልፈዋል።

እሁድ ረፋድ ላይ በመርጃ ማዕከሉ የደረሱት ሠራተኞች ፀሐይቷ ባለመራራት ያወረደችባቸው የንዳድ ውርጅብኝ ሳይሰማቸው በስፍራው ጉብኝት ጀምረዋል። በመርጃ ማዕከሉ የተሠሩትን ተግባራት የሚያስቃኝ ጥናታዊ ፊልም ሲቀርብ ገና አዳራሹ ኃዘን ባስነባቸው ሠራተኞች ተሞላ።

ማዕከሉ ውስጥ ለዘመናት አልጋን ተቆራኝተው የኖሩ፣ ሰዎችና ጊዜ የገፋቸው ምስኪኖች፣ የአዕምሮ ሕሙማን፣ እርጅና በሰፊ መዳፉ የደቆሳቸው፣ ብቻ ጤና ሰጥቶት ማዕከሉን ለመጎብኘት እድል ለተሰጠው ሰው ብዙ ማመስገኛ ምክንያት የሚሰጡ ሰዎች አሉበት። ከታማሚዎች፣ ከአረጋውያንና በቋሚነት ከቀጠራቸው ሠራተኞቹ ቁጥር ባልተናነሰም እዛው ታክመው ተረድተው የዳኑ በጎ ፍቃደኛ አገልጋዮችም ይገኛሉ። በሰው ተረድቶ ሰው መሆንን ተምረዋልና እነሱም ለተረኛ ተረጂዎች ሰው ሆኖ ለመገኘት እድላቸውን አያባክኑም።

የመርጃ ማዕከሉ መሥራች እንዲሁም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ቢንያም በለጠ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሠራተኞችን አክብሮ በታማሚ ጎኑ በጉብኝታቸው መሐል በመገኘት መልዕክቱን አስተላልፏል። ስፍራው በቀን ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አለበት። ይህን ወጪውንም ደግ አሳቢዎች ነግ በኔ ማለትን የለመዱ ቅኖች በሚያሰባስቡት ገቢ ነው የሚሸፍነው፤ አሁንም ግን ድጋፍ ይሻል ብሏል።

በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ባልደረቦች የተሠራው መልካም ሥራ ከፈጣሪ ዋጋ የሚያሰጥ ነው፤ በማዕከሉ የሚገኙ ተረጂዎችን ቁጥርም ሃያ ሺህ ለማድረስ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውንም አቶ ቢኒንያም ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰም ከጎብኚዎች መሐል ነበሩና መልዕክትና አደራቸውን አስተላልፈዋል። በነገ ቤታችንን በመቄዶኒያ መገኘት ለእኛ መልካም ነው፤ እዚህ በመገኘትና ማዕከሉን በመጎብኘት በብዙ አትርፌያለሁ ብለዋል።

አቶ ጌትነት ድርጅታቸው ለተቋሙ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ እኔም የግሌን ለማበርከት አቅሜ በፈቀደ ሁሉ ከመርጃ ማዕከሉ ጎን እቆማለሁ፤ ለድርጅቱም ኪስና ጉልበቴን እፈትሻለሁ ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አቶ ጌትነት በስፍራው መገኘታቸው ልባቸውን ያቀና ውስጣቸውን ያከመ መሆኑን ገልጸዋል። የድርጅታቸውን ሠራተኞችም ማዕከሉን በቋሚነት መልካም ፍቃደኞት ሆናችሁ አገልግሉ፤ ስፍራውን በመደገፍም የሥጋም የነፍስም ጥቅም ተጠቀሙ ብለዋቸዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Social Tagged With: Binyam Belete, Macedonia

Reader Interactions

Comments

  1. Don't incite bloody conflict among brotherly people of Tigray and Amhara says

    December 26, 2022 09:34 am at 9:34 am

    Is it beacuse you are humanely and care for entire humanity that many of you were blindly and deliberately supporting the massacre of Tegaru

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule