• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ

December 14, 2022 09:59 am by Editor 2 Comments

ድሮ ገና ከዓመታት በፊት በ12 ዓመቱ ነበር ሰውን የመርዳት ፅንስ በትንሽ ልቡ ውስጥ የተጸነሰው። ሳድግ የራሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት ኖሮኝ ሰዎችን እረዳለሁ እያለ ያወራ ነበር። የእድሜ አቻዎቹ ዶክተር፣ ኢንጅነር፣ ፓይለትና ሌሎችም እሆናለሁ በሚሉበት ለጋ እድሜ የሱ ትንሽ ልብ መሻት አድጎ ሰውን መርዳት መቻል ነበር። ዛሬም በሕይወት ጉዞው ላይ በብዙ ካደገም በኋላ የየቀን ንግግሩ የዘወትር ውዳሴው “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የሚል ቃል ነው። ሰው ስለሆነ ብቻ ሰው ይረዳልና።

የራስን ሕይወት ትቶ ስለሰው በሚኖረው ባሕሪው ከሰዎች መካከል ይለያል። የሥጋ ሕመሙ የነፍሱን ቁስል በሻረለት መልካም ሥራው ይታወቃል። ድንቅ የመልካምነት ምሳሌ፣ የመቻል አብነት፤ የደግ ልብ ጌታ ነው። የጥሩዎች ዕንቁ የደጎች አውራ ነው። ብዙዎች በተለያዩ ጊዜያት ደጋችን ነህ ሲሉ በይፋ አመስግነውታል። ዓመታዊው የቅን ልብ ባለቤቶችን እውቅና ሰጪው የበጎ ሰው ሽልማትም አንተ የመሰናዷችን ባለ በጎ ልብ ነህ ሲል ሽልማት ሰጥቶታል። የክብር ዶክትሬት ባለቤቱ የመቄዶኒያ ወላጅ ወጣት ቢንያም በለጠን።

ዘመኑ እናት ለልጇ አባት ወንድሙን እህት አክስቷን የተቸገሩበት፣ ሰው በሰው ላይ የጭካኔ በትሩን በገዛ ወገኑ ላይ የሚያሳርፍበት ቢሆንም ከዚህ በተቃራኒ ለሰው ልጅ በጎ የሚሠሩ ጥቂት ቅን ልቦች አሉ። በተለይ ሰው በሕመም ሲጎዳ እንኳን ባዳ ዘመድ ሩቁ ይሆናል። የታመመ ሰው ደግሞ በሕመም ጉዳት ምክንያት ብዙ አስቸጋሪ ነገሮች አያጣውም። በሚከብድ የሕመም ጣር ውስጥ ያለን ሰው አክሞ ወደ ቀድሞ ጤንነቱ መልሶ ተንከባክቦ ማኖር ግን በብዛት በቅርብ ሰዎች የሚከወን ተጨማሪ አቅምንም የሚጠይቅ ነበር።

ደፋሩ ቢንያም በለጠ ግን ይህን ከወነ፤ በኢትዮጵያ የጊዜ ቀመር 2004 የበጎነት ሥራውን አርባ ያህል ሰዎችን ከሜዳ በማንሳት አሐዱ አለ። አንዳንድ ሰው አይደለም በመኖር በሕመም ይማራል፤ በቀና ቀኖቹ ብቻ ሳይሆን የሕይወቱ ክፉ ቀናትም እሱን ለማስተማር ዝግጁ ሆነው ይቀርባሉ፤ ያኔ ከዓመታት በፊት ሰውና ቀን የጣላቸውን በማንሳት የተጀመረው የቀናነት ጉዞ ዛሬ ላይ ቁጥሩን አሳድጎ ከሰባት ሺህ አምስት መቶ ለሚልቁ ነፍሶች መጠጊያ ታዛ ሆኗል።

የክርስቲያኖች የሕይወት መሠረት በሚባለው ቅዱስ መጽሐፍ ላይ ተከትቦ የሚገኝ አንድ ቃል ዛሬ የብዙኃን መጠለያ ለሆነው መቄዶኒያ ስያሜ መነሻ መሆኑን ራሱ ቢንያም ይናገራል። እንዲህም አለ፤ የመቄዶኒያ ሰዎች በብዙ ተፈትነው ሳለ የድህነታቸው ጥልቀት የልግስናቸውን መጠን አብዝቶታል ይላል የተከተበው ቃል፤ ድሀ ቢሆኑም ለገሱ የሚል ትርጓሜንም ይይዛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሠራተኛና አመራሮችም ዓመታዊ የሠራተኞች ቀናቸውን በመቄዶኒያ የአረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ተረጂዎችን ምሳ በማብላትና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን በማከናወን አሳልፈዋል።

እሁድ ረፋድ ላይ በመርጃ ማዕከሉ የደረሱት ሠራተኞች ፀሐይቷ ባለመራራት ያወረደችባቸው የንዳድ ውርጅብኝ ሳይሰማቸው በስፍራው ጉብኝት ጀምረዋል። በመርጃ ማዕከሉ የተሠሩትን ተግባራት የሚያስቃኝ ጥናታዊ ፊልም ሲቀርብ ገና አዳራሹ ኃዘን ባስነባቸው ሠራተኞች ተሞላ።

ማዕከሉ ውስጥ ለዘመናት አልጋን ተቆራኝተው የኖሩ፣ ሰዎችና ጊዜ የገፋቸው ምስኪኖች፣ የአዕምሮ ሕሙማን፣ እርጅና በሰፊ መዳፉ የደቆሳቸው፣ ብቻ ጤና ሰጥቶት ማዕከሉን ለመጎብኘት እድል ለተሰጠው ሰው ብዙ ማመስገኛ ምክንያት የሚሰጡ ሰዎች አሉበት። ከታማሚዎች፣ ከአረጋውያንና በቋሚነት ከቀጠራቸው ሠራተኞቹ ቁጥር ባልተናነሰም እዛው ታክመው ተረድተው የዳኑ በጎ ፍቃደኛ አገልጋዮችም ይገኛሉ። በሰው ተረድቶ ሰው መሆንን ተምረዋልና እነሱም ለተረኛ ተረጂዎች ሰው ሆኖ ለመገኘት እድላቸውን አያባክኑም።

የመርጃ ማዕከሉ መሥራች እንዲሁም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ቢንያም በለጠ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሠራተኞችን አክብሮ በታማሚ ጎኑ በጉብኝታቸው መሐል በመገኘት መልዕክቱን አስተላልፏል። ስፍራው በቀን ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አለበት። ይህን ወጪውንም ደግ አሳቢዎች ነግ በኔ ማለትን የለመዱ ቅኖች በሚያሰባስቡት ገቢ ነው የሚሸፍነው፤ አሁንም ግን ድጋፍ ይሻል ብሏል።

በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ባልደረቦች የተሠራው መልካም ሥራ ከፈጣሪ ዋጋ የሚያሰጥ ነው፤ በማዕከሉ የሚገኙ ተረጂዎችን ቁጥርም ሃያ ሺህ ለማድረስ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውንም አቶ ቢኒንያም ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰም ከጎብኚዎች መሐል ነበሩና መልዕክትና አደራቸውን አስተላልፈዋል። በነገ ቤታችንን በመቄዶኒያ መገኘት ለእኛ መልካም ነው፤ እዚህ በመገኘትና ማዕከሉን በመጎብኘት በብዙ አትርፌያለሁ ብለዋል።

አቶ ጌትነት ድርጅታቸው ለተቋሙ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ እኔም የግሌን ለማበርከት አቅሜ በፈቀደ ሁሉ ከመርጃ ማዕከሉ ጎን እቆማለሁ፤ ለድርጅቱም ኪስና ጉልበቴን እፈትሻለሁ ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አቶ ጌትነት በስፍራው መገኘታቸው ልባቸውን ያቀና ውስጣቸውን ያከመ መሆኑን ገልጸዋል። የድርጅታቸውን ሠራተኞችም ማዕከሉን በቋሚነት መልካም ፍቃደኞት ሆናችሁ አገልግሉ፤ ስፍራውን በመደገፍም የሥጋም የነፍስም ጥቅም ተጠቀሙ ብለዋቸዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Social Tagged With: Binyam Belete, Macedonia

Reader Interactions

Comments

  1. Don't incite bloody conflict among brotherly people of Tigray and Amhara says

    December 26, 2022 09:34 am at 9:34 am

    Is it beacuse you are humanely and care for entire humanity that many of you were blindly and deliberately supporting the massacre of Tegaru

    Reply
  2. Samuel says

    October 16, 2025 11:29 am at 11:29 am

    Good job

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule