• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚደነግጡት መቼ መቼ ነው?

October 7, 2021 10:05 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ መንግስት በውስጥ ጉዳዬ ላይ ገብተዋል፣ ከተፈቀደላቸው ዓላማና ተግባር ውጭ ሲንቀሳቀሱ ተገኝተዋል ያላቸውን 7 በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ ግከለሰቦችን በ72 ሰአታት ውስጥ የኢትዮጵያን ግዛት ለቀው እንዲወጡ ሲል አዟል።

ይህንን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ “በኢትዮጵያ ውሳኔ ደንግጫለሁ” ሲሉ በትዊተር ገጻቸው ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ በአሸባሪው ህወሓት በርካታ ንጹሀን ሲገደሉ፣ ከ400 በላይ መኪናዎች በአሸባሪው ድርጅት ታግተው ሲቀሩ፤ አሸባሪው ኢትዮጵያን ለማፍረስ እየሰራሁ ነው ሲል ድምጻቸውን አጥፍተው አሁን ላይ መንግስት የአገር ሉአላዊነትን በተጋፉ የድርጅቶቱ ሰራተኞች ላይ እርምጃ ሲወስድ ደንግጫለሁ ማለታቸው ተገቢነት የጎደለው ነው ሲሉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተችተዋል።

አቶ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት አስተያየት፤ “አገር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚደነግጡት መቼ መቼ ነው?” ሲሉ ትዝብታቸውን ገልጸዋል።

አቶ አንዳርጋቸው፤ አሸባሪው ህወሓት በአንድ አገር ሉዓላዊ ሰራዊት ላይ የክልል መንግስት ጥቃት ፈጽሞ ንጹሀን ዩኒፎርም የለበሱ ወንድና ሴት ወታደሮች ሲጨፈጨፉ አንቶኒዮ ጉተሬዝ መደንገጣቸውን አልነገሩንም ብለዋል።

አሸባሪው ድርጅት ባደራጃቸው ገዳይ ቡድኖች ከ1000 በላይ ንጹሀን የአማራ ብሄር ተወላጆች በማይካድራ ሲጨፈጨፉ ዋና ጸሀፊው እንደደነገጡ አልነገሩንም ያሉት አቶ አንዳርጋቸው፤ በአፋር ጋሊኮማ የራሳቸው ድርጅት አባል የሆነው ዩኒሴፍ ሳይቀር ባጋለጠው ጭፍጨፋ ከ240 በላይ ንጹሀን ህጻናትና ሴቶች ጭምር በተጠለሉበት ሲጨፈጨፉ ጉተሬዝ ያሉት ነገር የለም።

አማራ ክልል ጭና ላይ በርካታ ንጹሀን በአሸባሪው ታጣቂዎች ሲጨፈጨፉ ዋና ጸሀፊው ድንጋጤ ብሎ ነገር አልተሰማቸውም፤ በቆቦ በአንድ ቀን ከ600 በላይ ንጹሀን መጨፍጨፋቸውን ሰምተው ዋና ጸሀፊው ድንግጥም ስለማለታቸው የተሰማ ነገር የለም ሲሉም ነው አቶ አንዳርጋቸው የዋና ጸሀፊውን አቋም የተቹት።

አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፍረስ፤ ከ30 ሚሎዮን በላይ ከሆነው ከአማራ ህዝብ ጋር ሂሳብ አወራርዳለሁ ብሎ በግልጽ ሲናገርና ወረራ ሲፈጽም አንቶኒዮ ጉተሬዝ መደንገጣቸውን አልነገሩንም፤ መንግስት ሀምሌ ወር ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኞች ከአሸባሪው ህወሓት ጋር አብረው እየሰሩ ነው፤ ከዚህ ድርጊታቸው ካልተገቱ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ ሲያስታውቅ በሰራተኞቻቸው ድርጊት ዋና ጸሀፊው አላፈሩም፤ አልደነገጡም ነው ያሉት አቶ አንዳርጋቸው።

የእርዳታ እህል ይዘው ወደ ትግራይ ክልል ከገቡ 400 መኪናዎች ውስጥ የተመለሱት 38 ብቻ ናቸው፤ ምግብ ለማድረስ መኪና ተቸገርኩ ብሎ ድርጅታቸው አቤቱታ ሲያቀርብ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ምንም አለማለታቸውን ያስታወሱት አቶ አንዳርጋቸው፤ መንግስት ከተደጋጋሚ ማሳሰቢያና መስጠንቀቂያ በኋላ ሰባት የእርሳቸው ድርጅት ግለሰቦችን ስላልተገባ ድርጊታቸው አገር ለቃችሁ ውጡ ሲል ግን አንቶኒዮ ጉተሬዝ ደንግጠዋል፤ መደንገጣቸውንም በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፤ ይህ የእርሳቸውንም ሆነ የድርጅታቸውን ሚዛን የለሽነት ያሳብቃል ነው ያሉት።

“ለመሆኑ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የሚደነግጡት  መቼ መቼ ነው?” ሲሉ የሚጠይቁት አቶ አንዳርጋቸው፤ ከዋና ጸሀፊው አቋም ተነስቶ ለዚህ ጥያቄ መልሱ “አሸባሪው ህወሓት የተጎዳ ሲመስላቸው አብዘተው ይደነግጣሉ፤ አብዝተውም ይጮሃሉ” የሚል ብቻ ነው ሲሉ ተችተዋል። (ኢፕድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 8, 2021 10:26 am at 10:26 am

    አንቶኒዮ ጉተሬዝ ለነጭ መብት የቆመ በአሜሪካ የሚገፋ ምህታታዊ ሰው ነው። ራሺያ ህገ ወጥ በሆነ መልኩ ክሪሚያን አጥቅታ ስትይዝ ይህን ያህል ጫጫታና የተመድ ስብሰባ አልተደረገም። ሳውዲ በአሜሪካ እየተረዳች በየመን ላይ የቦንብ ዝናብ ስታዘንብ ምንም የተባለ ነገር የለም። አውሮፓውያንና አሜሪካ የራሳቸው ጥቅም እስካልተነካ ድረስ ለሌላው አይገዳቸውም። ለወያኔ ወገባቸውን ይዘው የሚታገሉት የአውሮፓ ሃገራት ከወያኔና ከተላላኪዎቻቸው የሚያገኙት የቀጥታም ሆነ የተዘዋዋሪ ጥቅም ቀርቶባቸው ነው። ከዚህ በጎላ መልኩ ደግሞ ነጩ ዓለም ጥቁሩ ዓለም በራሱ አስቦ እንዲኖር አይፈልጉም። ቆም ብሎ ላሰበ ነገሩ ሁሉ ወደ እብደት ተለውጧል። አምስቱ የወያኔ ወታደራዊ ጄኔራል ነን ባዪች ጦርነቱን ለመቀጠል፤ ከክልላቸው አልፈው ውጊያውን ለማጧጧፍ ሲደነፉ፤ እርዳታ ጭነው የተላኩ መኪናዎች በዚያው ተጠልፈው ሲቀሩ፤ እልፍ የአማራና የአፋር ሰዎች ሲፈናቀሉና ሲገደሉ ተመድ የሚለው የለም። አሁንም የሚያላዝነው ያንኑ ወያኔን ለማትረፍ ያቀደውን ብልሃት ተገን አርጎ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያን የሚወድትን ሁሉ መኮነን ነው። የተመድ ሰራተኞች ለወያኔ ሰልፈኛ ሆነው ቁሳቁስ ማቀበላቸው እውነት ሆኖ እያለ መረጃ ይቅረብልኝ የሚሉት አንቶኒዮ ጉተሬዝ መረጃው ቢቀርብላቸው ምንም እንደማያደርጉ ከአሁኑ የታወቀ ነገር ነው። አይናቸው ላይ ፈጦ የሚታየውን እውነት አንቀበልም ያሉት አውሮፓዊያንና አሜሪካኖች ልክ እንደ ሊቢያ የሃበሻዋ ምድር የዘረኛና የጎሰኛ መንጋ የሚንጋጋባት እንድትሆን ይሻሉ። ያኔ ነጩ ህዝብ ደራሽና መልአክ ጥቁሩ ህዝብ ደግሞ እርስ በርሱ የሚባላ እንደሆነ አድርገው በሚዲያቸው ያጠቁሩናል። በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ ነጻ ምርጫ የሆነበት ጊዜ አንድም አልነበረም። አሁን ግን ፍጽም ነጻ ነው ባይባልም ሰው የፈለገውን ያለ ምንም ጫና መርጧል። ይህን እውነታ እንኳን አምኖ የማይቀበል የአሜሪካ የውጭ ፓሊሲ እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ለኢትዮጵያ በጎ የሚያስበው?
    አሁን እንሆ የሰሜኑ ችግር ካልተፈታ የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ማዕቀብ በኢትዮጵያ ላይ እንደሚያደርጉ ዝተዋል። አትፍረድባቸው ታዘው ነው በአሜሪካ። ግን ይሰማኛል የኢትዮጵያውን ጉዳይ ከልባቸው የሚያወጣ ዓለምን የሚያናውጥ የፓለቲካ ንፋስ በቅርብ ይፈጠራል። ያኔ እኛ እንረሳለን። ላንባቢ ምን እያልክ ነው ለምትሉ እኔ ጠንቋይም/ነብይም አይደለሁም። ግን የጊዜውን ሁኔታና የዓለምን የጂኦፓለቲካል መፋተግ በማየት ብቻ የተወሰደ ግምት መሆኑን ተረድልኝ። ጠብቆ ማየት ነው። እስከዚያው በዚህም በዚያም እየተገፋንና ራሳችን ለማገዶ እያዘጋጀን በወያኔና በአጋሮቹ መሪነት መገዳደላችን ይቀጥላል። ወያኔ ማለት የሌቦች ሁሉ ቁንጮ ማለት ነው። በቅርብ በአማራና በአፋር ክልል ካደረጉት ብዙ ወንጅሎች የመርካቶ ሌባ አይነት የሆነውን እውነተኛ ታሪክ ላካፍላችሁ። ገበሬው በሬውን እንዲሸጥላቸው ሲጠይቁት ግምቱ 10 ሺ ብር ነው ይሏቸዋል። እረ እኛ 20 ሺህ እንሰጥሃለን በማለት የድሮውን ብር ማለትም ወያኔ ከስልጣን ከተባረረ በህዋላ የተለወጠውን ቆጥረው ይሰጧቸዋል። እነርሱ ብር መቀየሩን አላወቁም። ግን ሌባው ወያኔ ይህን ያህል ወርዶ አፈር ገፊውን ገበሬ የሚያታልል እጅግ ጨካኝና መራራ ገዳይና አፋኝ ነው። ከዚህ ሃይል ጋር ነው እንደራደር የሚባለው? ወያኔ በምንም መንገድ ለሰላም ዝግጅ አይደለም። ሁሌም ውጊያ እንደ ጀብድ የሚታይበት ወንድምና እህቱን ገድሎ የሚፎክር ገበሬው እንዳሉት የአውሬ ስብስብ ነው። የሰውነት ባህሪያቸው ተሟጧል። ጀሮ ያለው ይስማና አቋሙን ያስተካክል። መገዳደላችን ለጠላት እንጂ ለህዝባችን አንድም አይበጅም። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule