• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እውነትም መክለፍለፍ

October 11, 2016 11:10 pm by Editor Leave a Comment

ጎልጉል “የዖሮምያ ሰነድ አዲሱ ቃልኪዳን” በሚል ርእስ ባወጣው ፅሁፍ የመክለፍለፍ ፖለቲካ ጎጂ አዝማሚያ በግልፅ መጠቆሙን ሳነብ እኔም “እውነትም መክለፍለፍ” ልል አማረኝ፤ እውነትም መክለፍለፍ።

መቼም በኢትዮጵያ የለውጥ ታሪክ ውስጥ ልሂቃን ፖለቲከኞችና ህዝብ ሆድና ጀርባ ከሆኑ ከ40 አመት በላይ ሆኗል። ህዝብ ለሃቀኛ ለውጥ ደሙን ያፈሳል፤ ብልጡ ልሂቅ ስልጣን ይወርሳል። ህዝብ ለጋራ አላማ ይደማል፤ ልሂቅ ለግል ጥቅሙ ይሿሿማል። ህዝብ ለለውጥ ይደማል፤ ብልጣብልጥ ፖለቲከኛ ስልጣን ይቀማል። ህዝብ ላንድነት ይጮሃል፤ ህዝብ እወክላለሁ ባይ ፖለቲከኛ ለልዩነት ይሰራል። ህዝብ ደማችን አንድ ነው በሚል ሰልፉን ሲያደምቅ ለዝቅም የሚማስነው ፖለቲከኛ ለጠብ ይሮጣል።

በሰሞኑም የሚታየው ይህንኑ የሚመስል ነው። ሞት አይፈሬዎቹ የህዝብ ልጆች  ከጨካኝ ባለክላሾች ጋር በባዶ እጃቸው በሚተጋተጉበትና ለፍትህ፣ ዲሞክራሲና አንድነት እየጣሉ በሚወድቁበት ባሁኑ ወቅት የዳያስፖራ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በየስፍራው ቻርተር በማርቀቅና የሽግግር መንግስት በማፅደቅ ስራ ተጠምደዋል ይባላል። ይህን የመሰለ ያገር ጉዳይ በቡድን እንዲወስኑ ከየትኛው ህዝብ እንዴት ያለ ውክልና እንደተቀበሉ የሚያውቁት እነርሱ ብቻ ናቸው። እኛ የምናውቀው ግን ህዝብ የሚለው ሌላ ፖለቲከኛ የሚለው ሌላ መሆኑን ነው።

አንድ ሁሉም ሊያውቀውና ሊጠነቀቅበት  የሚገባ ትልቅ አደጋ አለ። ይሄውም በህዝብ ትግልና መስዋእትነት እየመጣ ያለው ለውጥና የህዝብ አንድነት በተለመደው የፖለቲከኞች የማይረካ የስልጣን ጥም ሩጫ እንዳይኮላሽና ዳግም ኢትዮጵያን ለሞት የሚዳርግ የትውልድ ስህተት እንዳይፈፀም ነው። አሁን የሚበጀው አጋጣሚውን በመጠቀም ለሚያልፍ ስልጣን የማያልፍ የታሪክ ስህተት ለመፈፀም መጣደፍ ሳይሆን ከታሪክ ተምረን የህዝብን እውነተኛ ፍላጎት መሰረት በማድረግ ለሀገሪቱ ህልውናና ለህዝቧም ዘላቂ አንድነት የሚበጅ የጋራ ስልት መቀየስ ነው። -9 ክልል  ህዝብን እንዳላረካ ሁሉ 80 ቻርተር ለህዝብ ጥያቄ መልስ አይሆንም። ጉልጉል ጋዜጣ እንዳለው ለማይረባ የፖለቲካ አጀንዳ ከመክለፍለፍ ላገርና ህዝብ ዘላቂ ጥቅም በህብረት መጣደፍ ይበጃል።

እባካችሁ ለህዝብ ችግር ከቢሮ ተደስኩሮ ለህዝብ የሚወረወር መፍትሄ ሰልችቶናል። ንጉስ ሀይለስላሴ ስለምንወዳችሁ ህገመንግስት ሰጠናችሁ ብለው ከአርባ አመት በላይ ቀጥቅጠው ከገዙብ በኋላ ለጅብ ሰጥተውን ሄዱ። ደርግ ታሪክ አደራ ጣለብኝ አለና የህዝቡን አደራ በልቶ እሱም ህዝቡም በማያውቀው ባእድ ፍልስፍና ሲደናበር ከርሞ ለባሰበት የቀን ጅብ ሰጥቶን ተፈረካከሰ። ተረኛውም የህዝብ አደራ ቀማኛ ፥እናንተ ዝንበሉ እኔ አውቃለሁ መላ፥ አለና ብሄር፣ ብሄረሰብና ህዝብ በተሰኘ የእስታሊን ዘፈን 25 አመት ሲደንስብን ኖሮ አሁን ህልፈቱ እንደቀረበች በማወቅ አርፎ እንዳይሞት መቃብር አፋፍ ላይ ተዘቅዝቆ አስቸኳይ አዋጅ አጣዳፊ አዋጅ እያለ ያንቋርርብናል።

ይኼ ሁሉ የህዝብ መከራ በህዝብ ትግል ሊገፈፍ ተቃረበ በሚል ደስ ደስ ሊለን ሲጀምር ልማደኞቹ ፖለቲከኞች የህዝብ እውነተኛ ፍላጎት የሚነበብበትን ገፅ በመገልበጥ የራሳቸውን የስልጣን ጥም ማረጋገጫ ቻርተር ሊፅፉበት ወንበር ይጎትቱ ገቡ። ደግነቱ ጀግናው የዖሮሞ ህዝብ ባደባባይ ያሳየውን የአንድነትና ፍቅር ፍላጎት አሳምረው የሚያውቁ ፕሮፌሰር ሕዝቅኤል ገቢሳንና ዶ/ር ፀጋዬ ረጋሳን የመሳሰሉ ሃቀኛና በሳል የዖሮሞ ምሁራንን ስላፈራን በብስለት ሳይሆን በስሜት የሚነዱ አላዋቂ ፖለቲከኞች ከምንወደው ህዝባችን ሊለዩን አይችሉም። አረ ቀስ ጎበዝ! እየተስተዋለ እንጂ! የህዝብን ሀቀኛ የዲሞክራሲ ጩኸት ወደፖለቲካ ሸቀጥ ከመቀየር ደዌ ፈውስ የምናገኘው መቼ ነው?

ኢትዮጵያ ሆይ፣ የክፋት መልእክተኞች በሰይፍ የለዩት ህዝብሽ በሰልፍ ዳግም በፍቅር ሊተቃቀፍ እየገሰገሰ ነውና ደስ ይበልሽ! ትንሳኤሽን እናይ ዘንድ ጊዜው ቀርቧል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule