• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እውነትም መክለፍለፍ

October 11, 2016 11:10 pm by Editor Leave a Comment

ጎልጉል “የዖሮምያ ሰነድ አዲሱ ቃልኪዳን” በሚል ርእስ ባወጣው ፅሁፍ የመክለፍለፍ ፖለቲካ ጎጂ አዝማሚያ በግልፅ መጠቆሙን ሳነብ እኔም “እውነትም መክለፍለፍ” ልል አማረኝ፤ እውነትም መክለፍለፍ።

መቼም በኢትዮጵያ የለውጥ ታሪክ ውስጥ ልሂቃን ፖለቲከኞችና ህዝብ ሆድና ጀርባ ከሆኑ ከ40 አመት በላይ ሆኗል። ህዝብ ለሃቀኛ ለውጥ ደሙን ያፈሳል፤ ብልጡ ልሂቅ ስልጣን ይወርሳል። ህዝብ ለጋራ አላማ ይደማል፤ ልሂቅ ለግል ጥቅሙ ይሿሿማል። ህዝብ ለለውጥ ይደማል፤ ብልጣብልጥ ፖለቲከኛ ስልጣን ይቀማል። ህዝብ ላንድነት ይጮሃል፤ ህዝብ እወክላለሁ ባይ ፖለቲከኛ ለልዩነት ይሰራል። ህዝብ ደማችን አንድ ነው በሚል ሰልፉን ሲያደምቅ ለዝቅም የሚማስነው ፖለቲከኛ ለጠብ ይሮጣል።

በሰሞኑም የሚታየው ይህንኑ የሚመስል ነው። ሞት አይፈሬዎቹ የህዝብ ልጆች  ከጨካኝ ባለክላሾች ጋር በባዶ እጃቸው በሚተጋተጉበትና ለፍትህ፣ ዲሞክራሲና አንድነት እየጣሉ በሚወድቁበት ባሁኑ ወቅት የዳያስፖራ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በየስፍራው ቻርተር በማርቀቅና የሽግግር መንግስት በማፅደቅ ስራ ተጠምደዋል ይባላል። ይህን የመሰለ ያገር ጉዳይ በቡድን እንዲወስኑ ከየትኛው ህዝብ እንዴት ያለ ውክልና እንደተቀበሉ የሚያውቁት እነርሱ ብቻ ናቸው። እኛ የምናውቀው ግን ህዝብ የሚለው ሌላ ፖለቲከኛ የሚለው ሌላ መሆኑን ነው።

አንድ ሁሉም ሊያውቀውና ሊጠነቀቅበት  የሚገባ ትልቅ አደጋ አለ። ይሄውም በህዝብ ትግልና መስዋእትነት እየመጣ ያለው ለውጥና የህዝብ አንድነት በተለመደው የፖለቲከኞች የማይረካ የስልጣን ጥም ሩጫ እንዳይኮላሽና ዳግም ኢትዮጵያን ለሞት የሚዳርግ የትውልድ ስህተት እንዳይፈፀም ነው። አሁን የሚበጀው አጋጣሚውን በመጠቀም ለሚያልፍ ስልጣን የማያልፍ የታሪክ ስህተት ለመፈፀም መጣደፍ ሳይሆን ከታሪክ ተምረን የህዝብን እውነተኛ ፍላጎት መሰረት በማድረግ ለሀገሪቱ ህልውናና ለህዝቧም ዘላቂ አንድነት የሚበጅ የጋራ ስልት መቀየስ ነው። -9 ክልል  ህዝብን እንዳላረካ ሁሉ 80 ቻርተር ለህዝብ ጥያቄ መልስ አይሆንም። ጉልጉል ጋዜጣ እንዳለው ለማይረባ የፖለቲካ አጀንዳ ከመክለፍለፍ ላገርና ህዝብ ዘላቂ ጥቅም በህብረት መጣደፍ ይበጃል።

እባካችሁ ለህዝብ ችግር ከቢሮ ተደስኩሮ ለህዝብ የሚወረወር መፍትሄ ሰልችቶናል። ንጉስ ሀይለስላሴ ስለምንወዳችሁ ህገመንግስት ሰጠናችሁ ብለው ከአርባ አመት በላይ ቀጥቅጠው ከገዙብ በኋላ ለጅብ ሰጥተውን ሄዱ። ደርግ ታሪክ አደራ ጣለብኝ አለና የህዝቡን አደራ በልቶ እሱም ህዝቡም በማያውቀው ባእድ ፍልስፍና ሲደናበር ከርሞ ለባሰበት የቀን ጅብ ሰጥቶን ተፈረካከሰ። ተረኛውም የህዝብ አደራ ቀማኛ ፥እናንተ ዝንበሉ እኔ አውቃለሁ መላ፥ አለና ብሄር፣ ብሄረሰብና ህዝብ በተሰኘ የእስታሊን ዘፈን 25 አመት ሲደንስብን ኖሮ አሁን ህልፈቱ እንደቀረበች በማወቅ አርፎ እንዳይሞት መቃብር አፋፍ ላይ ተዘቅዝቆ አስቸኳይ አዋጅ አጣዳፊ አዋጅ እያለ ያንቋርርብናል።

ይኼ ሁሉ የህዝብ መከራ በህዝብ ትግል ሊገፈፍ ተቃረበ በሚል ደስ ደስ ሊለን ሲጀምር ልማደኞቹ ፖለቲከኞች የህዝብ እውነተኛ ፍላጎት የሚነበብበትን ገፅ በመገልበጥ የራሳቸውን የስልጣን ጥም ማረጋገጫ ቻርተር ሊፅፉበት ወንበር ይጎትቱ ገቡ። ደግነቱ ጀግናው የዖሮሞ ህዝብ ባደባባይ ያሳየውን የአንድነትና ፍቅር ፍላጎት አሳምረው የሚያውቁ ፕሮፌሰር ሕዝቅኤል ገቢሳንና ዶ/ር ፀጋዬ ረጋሳን የመሳሰሉ ሃቀኛና በሳል የዖሮሞ ምሁራንን ስላፈራን በብስለት ሳይሆን በስሜት የሚነዱ አላዋቂ ፖለቲከኞች ከምንወደው ህዝባችን ሊለዩን አይችሉም። አረ ቀስ ጎበዝ! እየተስተዋለ እንጂ! የህዝብን ሀቀኛ የዲሞክራሲ ጩኸት ወደፖለቲካ ሸቀጥ ከመቀየር ደዌ ፈውስ የምናገኘው መቼ ነው?

ኢትዮጵያ ሆይ፣ የክፋት መልእክተኞች በሰይፍ የለዩት ህዝብሽ በሰልፍ ዳግም በፍቅር ሊተቃቀፍ እየገሰገሰ ነውና ደስ ይበልሽ! ትንሳኤሽን እናይ ዘንድ ጊዜው ቀርቧል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule