• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሟቹ ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም የተሰበሰበው ገንዘብ ያስከተለው እሰጥ አገባ

November 4, 2018 07:30 am by Editor Leave a Comment

“በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም በጎፈንድሚ የተሰበሰበውን 73 ሺህ 9 መቶ ዶላር ወደ አካውንት ለማስገባት ፈቃደኛ አይደለሁም። ምክኒያቱም በኮሚቴው እምነት የለኝም” አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ።

“በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም በጎ ፈንድሚም ሆነ በማናቸውም መልኩ የተሰበሰበው ገንዘብ በስሙ ወደተከፈተው የባንክ አካውንት መግባት አለበት” የአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የህክምና ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ።

ይህ እሰጣ አገባ የተካሄደው ቅዳሜ ጥቅምት 24 በአፍሮዳይት ሆቴል የአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የህክምና ገቢ ለማሰባሰብ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ኮሚቴ በጠራው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

ኮሚቴው ለሁለት የተከፈለበትን ጉዳይ አንስቶ ባቀረበው ሪፖርት ላይ እንደገለጸው በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም የተሰበሰበው ገንዘብ ጉዳይን አስመልክቶ የተጓዘባቸውን ርቀቶች ዘግቧል። ከአርቲስት ፍቃዱ የህክምና ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ አማካኝነት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው አካውንት ላይ በአሁኑ ወቅት 1,200,895.69 (አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ ስምንት መቶ ከስልሳ ዘጠኝ ሳንቲም) ብር እንደሚገኝ ገልጸው ቀሪውን በጎፈንድሚ የተሰበሰበውን 73,900 ዶላር ወደ አካውንት እንዲያስገባ ለቴድሮስ ተሾመ ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም ለመቀበል እንዳልቻለና በኮሚቴው አባላት ላይ እምነት የለኝም በማለቱ ልዩነት እንደተፈጠረ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ጥቅምት 23 ቀን 2011 ዓ.ም በጊዮን ሆቴል ተሰብስቦ የወሰነውን ቃለ ጉባኤ በንባብ አስደምጧል። ይህንን አስመልክቶም ምላሽ የሰጠው አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ “ህዝብ ገንዘቡን የሰጠኝ የእኔን ስም አይቶ ነው። በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም የተሰበሰበውን ገንዘብ በኮሚቴው የክራይሲስ ማኔጅመንት ችግር ምክንያት እምነት ስለሌለኝ ገንዘቡን ወደ ተባለው አካውንት ገንዘቡን አላስገባሁም። ወደፊትም በዚህ ገንዘብ ላይ ሙሉ ኃላፊነቱን የምወስደውም ሆነ እየወስድኩ ያለሁት እኔ ነኝ። ጠበቃዬም ገንዘቡን ገቢ እንዳላደርግ አማክሮኛል። ለዚህም ለህሊናዬም ሆነ ለፈጣሪ ታማኝ በመሆን ገንዘቡን ህጋዊ ወራሽ ይሆናሉ ብዬ ለማስባቸው ቤተሰቦቹ ጥቅምና ለሀውልቱ ማሰሪያ እንዲሆን እየተንቀሳቀስን ነው” ብሏል።

ሌሎች የኮሚቴ አባላት ደግሞ በአጠቃላይ የተሰበሰበውን ገንዘብ ወደ አንድ ቋት እንዲገባና ፍርድ ቤት የሚያሳውቃቸውን ህጋዊ ወራሾች መጠበቅ አለበት የሚል አቋም ይዘዋል።

ለአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም ከህዝብ የተሰበሰበው ገንዘብ መጨረሻ ምን ይሆን? አሁንም ምላሽ የለውም። በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም በተሰበሰበው ገንዘብ ላይ የተነሳው ንትርክ ከዚህ በኋም የጤና እክል ለሚያገጥማቸው የኪነጥበብ ባለሙያዎች ህዝብ በአግባቡ እንዳያግዝ የራሱን አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳያሳርፍ ስጋት አጭሯል።

(ዘገባ፤ ጴጥሮስ አሸናፊ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule