• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ተላላኪና አሸባሪ ነው” ኦህዴድ

August 21, 2016 10:24 pm by Editor Leave a Comment

* “ወደ ኢትዮጵያ ከተመለስኩ ሊገድሉኝ ይችላሉ” ፋይሣ ሊሊሣ

በሪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ሁለተኛ የወጣው ፋይሣ ሊሊሣ “ወደ ኢትዮጵያ ከተመለስኩ ሊገድሉኝ ይችላሉ” በማለት የህወሃትን ጨካኝነት ለዓለም ገለጸ፡፡ የፋይሳ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ሊደርሱለት እንደሚገባ ተነገረ፡፡ አትሌቱን “አሸባሪና ተላላኪ” ሲል ኦህዴድ ኮንኖታል፡፡

የወርቅ ሜዳሊያ ከወሰደው ኬኒያዊ በላቀ ሁኔታ የዓለምአቀፍ ሚዲያን ትኩረት የሳበው ፋይሳ እዚያው ሪዮ ብራዚል በሰጠው ቃለምልልስ የኦሮሞ ተቃውሞ የሚያሳመላክተውን እጁን ከአናቱ በላይ በማጣመር ሳየበትን ምክንያት ገልጾዋል፡፡ “ተቃውሞዬን የገለጽኩት ለሕዝቤ ነው፤ ዘመዶቼ እስር ቤት ናቸው፤ እስር ቤት ሄጄ ከዘመዶቼ ጋር መገናኘት፣ እነርሱን መጠየቅ እፈራለሁ፤ ካወራህ ይገድሉሃል፤ ስለንደዚህ ዓይነት ነገር ማውራት በጣም አደገኛ ነው፤ (እዚያ አገር) ነጻነት የሚኖርህ መንግሥትን ከደገፍህ ብቻ ነው፤ ይህንን ካላደረግህ መሥራት አትችልም፤ በጣም መጥፎ መንግሥት ነው” ብሏል፡፡ lilesa

በድርጊቱ አምኖበት እንዳደረገ በመግለጽ ሲናገር “የኢትዮጵያ መንግሥት ሕዝቤን እየገደለ ነው፤ እኔ ከኦሮሞ ጎሣ ነኝ፤ ስለዚህ ለሕዝቤ እጄን አንስቻለሁ” በማለት ተናግሯል፡፡ “አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ … ይህንን መንግሥት ይደግፋሉ፤ እነዚህ መንግሥታት በሚሰጡት ዕርዳታ የጦር መሣሪያ እየገዛ ሕዝቡን ይፈጃል” ብሏል፡፡

ፋይሣ እሁድ ማምሻው ላይ ከኢሣት ጋር ባደረገው አጭር ቃለምልልስ “አስቤበት ያደረኩት ነው፤ ብሞትም አይቆጨኝም” ያለ ሲሆን የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር በግፍ ስለሚገዛት ኢትዮጵያና ሕዝቧ “የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ላይ ተረባርቦ ይህንን ሥርዓት ሊያስወግደው ይገባል” በማለት መልዕክቱን አሰምቷል፡፡

“(አገር ቤት ብሄድ) ይገድሉኛል፤ ወይም ያስሩኛል፤ ወይም እዚያው አየር ማረፊያ ስደርስ ያግዱኛል” በማለት ፍርሃቱን የተናገረው ፋይሣ ሊሊሣ ወደ ሌላ አገር ለመሄድ እንደሚፈልግ በግልጽ ተናግሯል፡፡

በዓለምአቀፍ የፖለቲካ መድረክ እየከሰረ የመጣው ህወሃት በስፖርቱ መስክ በተለይም አገር ውስጥ በቀጥታ ስርጭት እየተላለፈ በዓለምዙሪያ ፋይሣ ያሳየው ተቃውሞ ዕርቃኑን አውጥቶታል፡፡ ከዚህ አንጻር የሥርዓቱ ደጋፊዎች በማኅበራዊ ገጾች ላይ ፋይሣን ወደ አገርቤት መመለስ ይገባል፤ ሕገመንግሥታዊ መብቱን ነው የተጠቀመው፤ የሚያስፈልገው ርብርብ ተደርጎ የኦሎምፒኩ ጀግና ወደ አገር እንዲመለስ በማለት የህወሃትን ዕርቃን ለመሸፈን ቅስቀሳ ጀምረዋል፡፡ ተመሳሳይ ተቃውሞ ያሳዩ እስከ 1ሺህ የሚጠጉ ኦሮሞዎች በጭካኔ እየገደሉ፤ እነ በቀለ ገርባን በግፍ አስረው እያሰቃዩ ፋይሳን ወደ አገርን ና ማለት የማያስቅ ቀልድ ነው በማለት አስተያየት ሰጪዎች ውድቅ አድርገውታል፡፡ blackpower

የህወሃት ውርደት ያንገበገባቸው በሌላ መልኩ የአትሌቱን ድርጊት በማውገዝ ሜዳሊያው ሊነጠቅ ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ እኤአ 1968 በአሜሪካ ጥቁሮች ላይ የሚደርሰውን ግፍ በኦሎምፒክ የሚዳሊያ ሥነሥርዓት ላይ ያሳዩትን ቶሚ ስሚዝና ጆን ካርሎስን ሲጠቅሱ ተሰምተዋል፡፡ አትሌቶቹ በ200ሜትር 1ኛ እና 3ና ከወጡ በኋላ ሜዳሊያው በሚሰጥበት ጊዜ “የጥቁር ኃይል” የሚባለውን እጅን በጡጫ መልክ የመጨበት ምልክት፣ የጥቁሮችን ድህነት ለማሳየት ያለጫማ በመሆን እንዲሁም ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ይገደሉ የነበሩትን ጥቁሮችን ለማመላከት ጨሌ አድገው ታይተዋል፡፡ የአሜሪካ የሕዝብ መዝሙር ሲዘመር አንገታቸውን በማቀርቀር በዝምታ ጨርሰዋል፡፡ በዚህ ድርጊታቸው የአለምዓቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሜዳሊያቸውን እንደሚልሱ አድርጓል፡፡ ከዘመናት በኋላ በአሜሪካ ውስጥ ጀግኖች ተብለው በተለያዩ ቦታዎች ሃውልቶች ቆመውላቸዋል፡፡

Lelisa_FeyisaA-World11በሌላ በኩል የፋይሳ የወደፊት ሁኔታ ያሳሰባቸው አሁን ባለበት ቦታ በቶሎ ድጋፍ ሊደረግለት በማለት የድረሱለት ጥያቄ እያቀረቡ ነው፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውን የሕግ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች፣ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ፋይሣን እንዲታደጉ፣ ሕጋዊ መብቱ እንዲጠበቅለትና ወደ ሦስተኛ አገር መሄድ የሚችልበትን መንገድ እንዲመቻችለት እንዲረዱት ተማጽኖዎች እየቀረቡ ነው፡፡ በሪዮ የዓለምአቀፉን ኦሎምፒክ ኮሚቴን እንዲወተውቱ፤ ጥገኝነት ሊሰጡ የሚችሉ መንግሥታትን እንዲያማክሩ፣ እርሱም ምን ማድረግ እንደሚገባው አስፈላጊው የምክር አገልግሎት እንዲሰጠው ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ በጥብቅ አሳስበዋል፡፡ በአረመኔው ህወሃት ቁጥጥር በምትገኘው ኢትዮጵያ መመለሱ ለበቀል እንደሚዳርገው ያላቸውን ፍርሃት ጨምረው ገልጸዋል፡፡

እሁድ ማምሻው ላይ ፋይሳን በገንዘብ ለመርዳት ድረገጽ ተከፍቷል፡፡ Go fund me በተባለው በዚህ ድረገጽ ላይ $40ሺህ ዶላር ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ $28,150 ዶላር ተሰብስቧል፡፡ ለመርዳት የሚፈልጉ ሁሉ ይህንን በመጫን ወደ ድረገጹ መድረስ ይችላሉ፡፡

በፋይሣ የተቃውሞ ድርጊት ያስቆጣው ኦህዴድ ከህወሃት በተሰጠው ትዕዛዝ አትሌቱን ተላላኪና አሸባሪ ሲል ድርጊቱን በማውገዝ በፌስቡክ ገጹ ላይ ኮንኖታል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule