• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ተላላኪና አሸባሪ ነው” ኦህዴድ

August 21, 2016 10:24 pm by Editor Leave a Comment

* “ወደ ኢትዮጵያ ከተመለስኩ ሊገድሉኝ ይችላሉ” ፋይሣ ሊሊሣ

በሪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ሁለተኛ የወጣው ፋይሣ ሊሊሣ “ወደ ኢትዮጵያ ከተመለስኩ ሊገድሉኝ ይችላሉ” በማለት የህወሃትን ጨካኝነት ለዓለም ገለጸ፡፡ የፋይሳ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ሊደርሱለት እንደሚገባ ተነገረ፡፡ አትሌቱን “አሸባሪና ተላላኪ” ሲል ኦህዴድ ኮንኖታል፡፡

የወርቅ ሜዳሊያ ከወሰደው ኬኒያዊ በላቀ ሁኔታ የዓለምአቀፍ ሚዲያን ትኩረት የሳበው ፋይሳ እዚያው ሪዮ ብራዚል በሰጠው ቃለምልልስ የኦሮሞ ተቃውሞ የሚያሳመላክተውን እጁን ከአናቱ በላይ በማጣመር ሳየበትን ምክንያት ገልጾዋል፡፡ “ተቃውሞዬን የገለጽኩት ለሕዝቤ ነው፤ ዘመዶቼ እስር ቤት ናቸው፤ እስር ቤት ሄጄ ከዘመዶቼ ጋር መገናኘት፣ እነርሱን መጠየቅ እፈራለሁ፤ ካወራህ ይገድሉሃል፤ ስለንደዚህ ዓይነት ነገር ማውራት በጣም አደገኛ ነው፤ (እዚያ አገር) ነጻነት የሚኖርህ መንግሥትን ከደገፍህ ብቻ ነው፤ ይህንን ካላደረግህ መሥራት አትችልም፤ በጣም መጥፎ መንግሥት ነው” ብሏል፡፡ lilesa

በድርጊቱ አምኖበት እንዳደረገ በመግለጽ ሲናገር “የኢትዮጵያ መንግሥት ሕዝቤን እየገደለ ነው፤ እኔ ከኦሮሞ ጎሣ ነኝ፤ ስለዚህ ለሕዝቤ እጄን አንስቻለሁ” በማለት ተናግሯል፡፡ “አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ … ይህንን መንግሥት ይደግፋሉ፤ እነዚህ መንግሥታት በሚሰጡት ዕርዳታ የጦር መሣሪያ እየገዛ ሕዝቡን ይፈጃል” ብሏል፡፡

ፋይሣ እሁድ ማምሻው ላይ ከኢሣት ጋር ባደረገው አጭር ቃለምልልስ “አስቤበት ያደረኩት ነው፤ ብሞትም አይቆጨኝም” ያለ ሲሆን የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር በግፍ ስለሚገዛት ኢትዮጵያና ሕዝቧ “የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ላይ ተረባርቦ ይህንን ሥርዓት ሊያስወግደው ይገባል” በማለት መልዕክቱን አሰምቷል፡፡

“(አገር ቤት ብሄድ) ይገድሉኛል፤ ወይም ያስሩኛል፤ ወይም እዚያው አየር ማረፊያ ስደርስ ያግዱኛል” በማለት ፍርሃቱን የተናገረው ፋይሣ ሊሊሣ ወደ ሌላ አገር ለመሄድ እንደሚፈልግ በግልጽ ተናግሯል፡፡

በዓለምአቀፍ የፖለቲካ መድረክ እየከሰረ የመጣው ህወሃት በስፖርቱ መስክ በተለይም አገር ውስጥ በቀጥታ ስርጭት እየተላለፈ በዓለምዙሪያ ፋይሣ ያሳየው ተቃውሞ ዕርቃኑን አውጥቶታል፡፡ ከዚህ አንጻር የሥርዓቱ ደጋፊዎች በማኅበራዊ ገጾች ላይ ፋይሣን ወደ አገርቤት መመለስ ይገባል፤ ሕገመንግሥታዊ መብቱን ነው የተጠቀመው፤ የሚያስፈልገው ርብርብ ተደርጎ የኦሎምፒኩ ጀግና ወደ አገር እንዲመለስ በማለት የህወሃትን ዕርቃን ለመሸፈን ቅስቀሳ ጀምረዋል፡፡ ተመሳሳይ ተቃውሞ ያሳዩ እስከ 1ሺህ የሚጠጉ ኦሮሞዎች በጭካኔ እየገደሉ፤ እነ በቀለ ገርባን በግፍ አስረው እያሰቃዩ ፋይሳን ወደ አገርን ና ማለት የማያስቅ ቀልድ ነው በማለት አስተያየት ሰጪዎች ውድቅ አድርገውታል፡፡ blackpower

የህወሃት ውርደት ያንገበገባቸው በሌላ መልኩ የአትሌቱን ድርጊት በማውገዝ ሜዳሊያው ሊነጠቅ ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ እኤአ 1968 በአሜሪካ ጥቁሮች ላይ የሚደርሰውን ግፍ በኦሎምፒክ የሚዳሊያ ሥነሥርዓት ላይ ያሳዩትን ቶሚ ስሚዝና ጆን ካርሎስን ሲጠቅሱ ተሰምተዋል፡፡ አትሌቶቹ በ200ሜትር 1ኛ እና 3ና ከወጡ በኋላ ሜዳሊያው በሚሰጥበት ጊዜ “የጥቁር ኃይል” የሚባለውን እጅን በጡጫ መልክ የመጨበት ምልክት፣ የጥቁሮችን ድህነት ለማሳየት ያለጫማ በመሆን እንዲሁም ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ይገደሉ የነበሩትን ጥቁሮችን ለማመላከት ጨሌ አድገው ታይተዋል፡፡ የአሜሪካ የሕዝብ መዝሙር ሲዘመር አንገታቸውን በማቀርቀር በዝምታ ጨርሰዋል፡፡ በዚህ ድርጊታቸው የአለምዓቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሜዳሊያቸውን እንደሚልሱ አድርጓል፡፡ ከዘመናት በኋላ በአሜሪካ ውስጥ ጀግኖች ተብለው በተለያዩ ቦታዎች ሃውልቶች ቆመውላቸዋል፡፡

Lelisa_FeyisaA-World11በሌላ በኩል የፋይሳ የወደፊት ሁኔታ ያሳሰባቸው አሁን ባለበት ቦታ በቶሎ ድጋፍ ሊደረግለት በማለት የድረሱለት ጥያቄ እያቀረቡ ነው፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውን የሕግ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች፣ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ፋይሣን እንዲታደጉ፣ ሕጋዊ መብቱ እንዲጠበቅለትና ወደ ሦስተኛ አገር መሄድ የሚችልበትን መንገድ እንዲመቻችለት እንዲረዱት ተማጽኖዎች እየቀረቡ ነው፡፡ በሪዮ የዓለምአቀፉን ኦሎምፒክ ኮሚቴን እንዲወተውቱ፤ ጥገኝነት ሊሰጡ የሚችሉ መንግሥታትን እንዲያማክሩ፣ እርሱም ምን ማድረግ እንደሚገባው አስፈላጊው የምክር አገልግሎት እንዲሰጠው ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ በጥብቅ አሳስበዋል፡፡ በአረመኔው ህወሃት ቁጥጥር በምትገኘው ኢትዮጵያ መመለሱ ለበቀል እንደሚዳርገው ያላቸውን ፍርሃት ጨምረው ገልጸዋል፡፡

እሁድ ማምሻው ላይ ፋይሳን በገንዘብ ለመርዳት ድረገጽ ተከፍቷል፡፡ Go fund me በተባለው በዚህ ድረገጽ ላይ $40ሺህ ዶላር ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ $28,150 ዶላር ተሰብስቧል፡፡ ለመርዳት የሚፈልጉ ሁሉ ይህንን በመጫን ወደ ድረገጹ መድረስ ይችላሉ፡፡

በፋይሣ የተቃውሞ ድርጊት ያስቆጣው ኦህዴድ ከህወሃት በተሰጠው ትዕዛዝ አትሌቱን ተላላኪና አሸባሪ ሲል ድርጊቱን በማውገዝ በፌስቡክ ገጹ ላይ ኮንኖታል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule