• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ክስ ተመሰረተባቸው

September 13, 2024 03:02 pm by Editor Leave a Comment

* በሁሉም ባንኮች ያለው ሒሳብ ታገደ

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ አራት አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና ሌሎች ተያያዝ ጉዳዮች ክስ ተመሰረተባቸው። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሁሉም ባንኮች ያለው ሒሳብ ታገደ።

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፤ ዐቃቤ ነዋይዋ ዶ/ር ኤደን አሸናፊ፣ ዋና ፀሐፊ አቶ ዳዊት አስፋው እና ምክትል ፀሐፊ አቶ ገዛኸኝ ወልዴም ከተከሳሾቹ መካከል ነው።

ክሱን የመሰረቱት ሻለቃ አትሌት ኃይሌ_ገብረሥላሴ፣ አትሌት ገዛኸኝ አበራ፣ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ቴኒስ ፌዴሬሽን ናቸው። በከሳሾቹ ጠበቆች በኩል ክሱ የቀረበለት የፌደራል አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት አራድ ምድብ ችሎት ኮሚቴው ፤ ግንቦት 5 እና ሰኔ 4፤ 2016 ዓ.ም. ያካሄዳቸው ጠቅላላ ጉባኤዎች እና ውሳኔዎች እንዲታገዱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

የከሳሽ ጠበቃ የሆኑት አቶ አያሌው ቢታኔ “ከፓሪስ ኦሊምፒክ ጋር በተያያዘ [ተከሳሾቹ] ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሰማርተዋል ብለን እንጠረጥራለን። የወንጀል ተጠያቂነቱ እንዳለ ሆኖ ሥልጣናቸውን ያለ አግባብ በመጠቀም ኦሊምፒክ ኮሚቴውን [በዝብዘዋል]” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጠበቃው አክለው “ደብዳቤ ስለተጻፈ ብቻ የማይመለከተው ሰው [ወደ ፓሪስ] ይሄድ ነበር” ብለዋል።

የሰው ዝውውር ተብሎ በደምሳሳው የተጠቀሰው ክስ በተለይ የኦሎምፒክ ውድድሮችን ምክንያት በማድረግ የሚመጣውን ቪዛ ከአገር ለመውጫ ከመሸጥ ጀምሮ ለሌሎች ማስተላለፍን የሚጠቀልል ነው።

የሕገወጥ የሰው ዝውውር በዓለምአቀፍ ሕግ ጭምር የሚያስከስስ ወንጀል በመሆኑ እንደተባለው ክሱ በማስረጃ ከተረጋገጠ በዚህ ሥራ ላይ የተሳተፉ በሙሉ በዓለምአቀፉ ሕግ ይቀጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ግንቦት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ባደረገው አስቸኳይ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የተላለፉ ውሳኔዎችና ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. ያካሄደው የኦሊምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ምርጫ እንዲታገድ በቀረበው የፍትሐብሔር ክስ መሠረት በፍርድ ቤት ዕግድ ተሰጠ (ሪፖርተር)፡፡

በከሳሾች አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ አትሌት ገዛኸኝ አበራ፣ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽንና በኢትዮጵያ ቴኒስ ፌዴሬሽን በቀረበው የፍትሐብሔር ክስ አቤቱታ፣ ክስ የቀረባበቸው፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ (ዶ/ር) አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ፣ ኤደን አሸናፊ (ዶ/ር)፣ አቶ ዳዊት አስፋውና አቶ ገዛኸኝ ወልዴ ናቸው፡፡

ተከሳሾቹ በዋናነት የቀረበባቸው ክስ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 154 እና 205 ድንጋጌዎችን በመተላለፍ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ጠቅላላ ጉባዔ በማካሄድ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፋቸውና ሕገወጥ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ምርጫ አካሄደዋል በሚል ነው፡፡

በመሆኑም ተከሳሾች ባደረጉት ሕገወጥ ጠቅላላ ጉባዔ የተላለፉ ውሳኔዎች፣ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ምርጫ እንዲታገድ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ.ም. የክስ አቤቱታ ቀርቧል፡፡

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ያለው ተቀማጭ ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ዕግድ እንዲሰጥበትም ከሳሾች ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡

የክስ አቤቱታውን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍትሐብሔር ጊዜ ቀጠሮ ችሎት፣ በከሳሾች የተጠየቀውን ዕግድ ተቀብሎ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሁሉም ባንኮች ያለው ሒሳብ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ እንዳይንቀሳቀስና ግንቦት 6 እና ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. ከቦርድ ምርጫ ጋር ተያይዞ የተላለፉ ውሳኔዎችም ታግደው እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ክሱ ፍርድ ቤቶች መደበኛ ሥራ ሲጀምሩ የሚንቀሳቀስ መሆኑም ታውቋል፡፡ 

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Ashebir, Derartu TUlu, Ethiopian Olympics Committee, Haile Gebreselassie

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule