• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኮንትሮባንድ ንግድ እንደ ተቋም

October 31, 2015 12:57 am by Editor 3 Comments

በሻሸመኔ አካባቢ የኮንትሮባንድ ንግድ ተቋማዊ ቅርጽ መያዙን የሚያሳይ መረጃ ጠቆመ፡፡ ሌሎች በኮንትሮባንድ ንግድ እንዳይሳተፉ የሚከለክለው ሕግ የሚጸናባቸው ከህወሃት ራቅ ያሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸው ድርጊቱን “ማስመጥ” አሰኝቶታል፡፡ ዜጎችም “የኮንትሮባንድ ንግድ ትርጉሙ ምን ይሆን?” እያሉ ነው፡፡

የኮንትሮባንድ ንግድ በህጋዊነት በተለይ የሚፈጸመው ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም ላለፉት 25 ዓመታት በግፍ እየገዛ ባለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ህወሃትና በአፍቃሪዎቹ መሆኑን በማረጋገጥ የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በዓይን ምስክርነት የታዘቡትን በፎቶ የተደገፈ መረጃ ልከውልናል፡፡ ዜናውን እማኝ ዘጋቢው ይላኩት እንጂ በድፍን አገሪቱ ህወሃቶች፣ የህወሃት አገልጋዮች፣ የህወሃት ሽፋን ሰጪዎች፣ ነባር ተጋዳላዮች፣ ተላላኪዎች፣ ወዘተ በዚህ ሥራ እንዲሰማሩ የተፈቀደላቸውና የይለፍ ካርድ/መታወቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡

ከእማኝ ዘጋቢው ጋር በተደጋጋሚ በተላላክነውና ባጠናቀርነው መረጃ መሠረት ጉዳዩ እየተፈጸመ ያለው በሻሸመኔ ከተማ ነው፡፡ ዘጋቢው ሁኔታውን በማስመልከት እንዴት የህወሃት ድጋፍ ባለው መልኩ የኮንትሮባንድ ንግዱ እንደሚካሄድ ሲገልጹ እንዲህ ይላሉ፡-

“ይኼ የላኩላችሁ ፎቶ በሻሸመኔ ከተማ በጠራራ ጸሃይ በህወሃት እየተካሄደ ያለው ሕገወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ነው፤ … እነዚህ ሰዎች ያለ ማንም ከልካይ ዕቃ ከሞያሌና ከዶሎ (ሶማሌ ክልል በነጌሌ ቦረን በኩል) በአይሱዙ ይጭናሉ፡፡ መንገድ ላይ ያሉትን የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ኬላዎችን ያለ አንዳች ከልካይ ያልፋሉ፤ (ኬላ ላይ ሲያቆሟቸውም) just በትግሪኛ ያወሯቸዋል፤ ግፋ ቢባል የሆነች ብጣሽ ወረቀት ያሳያሉ፤ ይቺ ወረቀት የምትለው ደግሞ አባል ስለሆኑ ይለፉ ነው፤ … የህወሃት ማኅተም ተመቶበታል፡፡ በቃ ሁሉንም ኬላዎች ያልፉና ሻሸመኔ በግላጭ ያራግፋሉ፤” በማለት ሁኔታውን አስረድተዋል፡፡

በኮንትሮባንድ ያስገቡትን ዕቃ መጠን እና የት እንደሚያከማቹ ሲገልጹ ደግሞ፤

“… ቢያንስ በሳምንት አራት FSR Isuzu በእያንዳንዱ መጋዘናቸው ያራግፋሉ፤ እኔ እንኳን የታዘብኩት ሰፈሮች ደግሞ ከሚካኤል ቤ/ክ ወረድ ብሎ 07 እና 08 ቀበሌዎች አራት መጋዘኖች አሏቸው፡፡ አንደኛው ከሸገር አሮጌ ጫማ ማደሻ ወረድ ብሎ 3ኛው ግቢ ውስጥ ሲገኝ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ከአንደኛው ግቢ 200 ሜትር ወረድ ብሎ ከሚገኘው furniture ቤት በቀኝና በግራ ያሉት ግቢ ውስጥ ነዉ። አራተኛው ማከማቻ 08 ቀበሌ ተክሌ ቦጋለ የሚባል ባለ አንድ ፎቅ pension ግቢ ውስጥ ነው። (ከእነዚህ ማከማቻዎች በተጨማሪ) ሸዋ በር በሚባል አካባቢ 3 መጋዘኖች አሉ፡፡ አንደኛው ዘቢብ ሆቴል፤ ሁለተኛው መናፈሻ ጊቢ ውስጥ ሲሆን ሦስተኛው ደግሞ የዱሮው እንጆሪ ጊቢ ውስጥ ናቸው፤ … እነዚህ ቡድኖች እንደዚህ ወንጀል እየሠሩ ማንም አይናገራቸውም፤ … ነገር ግን የሌላ ብሔር ተወላጅ ድንገት አንዲት ፌስታል ሰልባጅ ከተያዘበት 7 ዓመት ተፈርዶበት ወኅኒ ይወርዳል፤ … በዚህች አንድ ወር እንኳን 4 ልጆች ተፈርዶባቸው እስር ቤት ወርደዋል፡፡”

በዚህ የኮንትሮባንድ ንግድ የተሰማሩት የህወሃት ባለፈቃዶች የሚያስገቡት ዕቃ “በአብዛኛው ሰልባጅ ልብሶች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ አረቢያን መጅሊስ፣ ቶርሽን ጫማዎችና የመሳሰሉት” መሆናቸውን ስማቸው እንዳይነገር የጠቀሱት እማኝ ዘጋቢው አስረድተዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ይህንን ስራ በንደዚህ መልኩ በገሀድ መስራት ከጀመሩ ከሁለት ዓመት በላይ” እንደሆናቸው ዘጋቢው ሲያስታውቁ “በተለይ ከአንድ አመት ወዲህ ደግሞ ቁጥራቸው እጅጉን በጣም” እየጨመረ እንደመጣ እማኝነት በላኩልን መረጃ አስታውቀዋል፡፡ የህወሃት ውክልና እና ፈቃድ የተሰጣቸው “ልማታዊ ኮንትሮባንዲስቶቹ” በከተማው ዕቃውን ለመሸጥ ሱቅ እንደሌላቸው ነገር ግን የኮንትሮባንድ “እቃውን ካስገቡ በኋላ ለነጋዴዎች በጅምላ ለተጠቃሚ ደግሞ በችርቻሮ … እዛው እቃው ባለበት ግቢ” ውስጥ እንደሚሸጡ የዓይን ምስክር ነኝ በማለት ለጎልጉል ከሥፍራው በፎቶግራፍ የተደገፈ መረጃ የላኩልን እማኝ ዘጋቢ አስረድተዋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ መሰል ሕገወጥ ንግዶች በህወሃቶች እንደሚፈጸም ከዚህ በፊት መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በተቋማዊ መልክ በአገሪቱ ውስጥ ስለተንሰራፋው ሕገወጥ ንግድ እና በድርጅት ፈቃድ እና ዋስትና ስለሚካሄደው የኮንትሮባንድ ንግድ የጸረ ሙስና ኮሚሽንን መጠየቁ ከኮሚሽኑ አፈጣጠር፣ ዓቅምና ህልውና በላይ ይመስለናል፡፡ በህወሃት አገዛዝ ውስጥ ህጋዊ የሆነ ህገወጥነት አለ፤ ህገወጥ የሆነ ህጋዊነት አለ፡፡ ተቋማቱ ሁሉ የሚሠሩት በዚህ ባልተጻፈ ወይም ባልተደነገገ መመሪያ ስለሆነ “ማጣራት” የሚባለው ነገር አቅመቢስ፣ ዋጋቢስ ነው፡፡

ጎልጉል የእማኝ ሪፖርተሮች ያሉት ሲሆን በነዚሁ ምንጮቹ አማካይነት መረጃ ለህዝብ ሲያቀርብ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ለዚህም ነው “ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ ነው” የምንለው፡፡ ይህንን ዜና ተመለከተ ከአገዛዙ አካላት ምላሽ ለመስጠት ድፍረት ወይም ብቃት ያላቸው ካሉ ለዝግጅት ክፍላችን ሊልኩልን ይችላሉ፡፡


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” እና “ማኅበራዊ (Social)” ዓምዶች የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Gilentufagonji says

    November 1, 2015 10:27 pm at 10:27 pm

    These smugglers are enemy of the country and the people, so, try to kill them systematically.That is all:

    Reply
  2. Gilentufagonji says

    November 1, 2015 10:31 pm at 10:31 pm

    They are enemies, So, avoid them in a sublease way

    Reply
  3. Gilentufagonji says

    November 1, 2015 10:35 pm at 10:35 pm

    Blow up their store and next,hang them one by one

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule