• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ በ2032

December 4, 2019 07:29 am by Editor 1 Comment

የምንፈልጋት ኢትዮጵያ በ2032 በሚል ርእስ ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ሀገር አቀፍ የውይይት መድረኩን በፎረም ኦፍ ፌዴሬሽን እና ዴስትኒ ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቭ ናቸው በጋራ ያዘጋጁት።

በመድረኩ ላይም የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ የክልል ርእሳነ መስተዳድሮች እና ምክትል ርእሳነ መስተዳድሮች፣ የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የበርካታ ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ተወካዮችም በመድረኩ ላይ ተሳትፈዋል።

መድረኩ የሀገሪቱን የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን በማቀራረብ የወደፊት የሀገሪቱ እጣ ፈንታ ላይ ለመወያየት በማለም የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችም፤ በመድረኩ ደስተኛ መሆናቸውን በመግለፅ፤ አሁንም ለኢትዮጵያ በርትተው እንዲሰሩ እድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ተወካዮቹ ከዚህ ቀደም በዚህ መድረክ ስር በጋራ በነበራቸው ቆይታ ስለ ሀገሪቱ ፖለቲካ በስፋት መምከራቸውን እና በሀገሪቱ የሚስተዋሉ ችግሮች በውይይት ብቻ የሚፈቱ እንደሆኑ ከመግባባት መድረሳቸውን አስታውቅዋል።

የኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፥ መድረኩ በሀገር ጉዳይ ሁሉም በንግግር የሚፈታ መሆኑን ልምድ የተገኘበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የአብን ሊቀ መንበር ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ፥ መድረኩ የተራራቀ አቋም ያላቸው የፖለቲካ ሀይሎችን ያቀራረበ መሆኑን ተናግረዋል።

በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ምንም አይነት የተራራቀ የአቋም ልዩነት ቢኖርም፤ በመቀራረብ እና በመወያየት የማይፈታ ነገር እንደሌለ ያስተማረ መድረክ መሆኑን ተቅሰዋል።

የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳም፥ “መድረኩ መጀመሪያ ሲጀመር ውጤቱ ላይ ጥርጣሬ ነበረኝ፤ ወደ ስራ ስገባ ግን ቀስ በቀስ በመነጋገር፣ በመወያየትና በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ መፈለግ እንደሚቻል ልምድ ያገኘሁበት ነው” ብለዋል።

የአዴፓ ተወካይ ዶክተር ስንታየሁ ወልደሚካኤል፥ “በመድረኩ በጋራ በመሆን ሀገርን፣ የዴሞክራሲ ስርዓትን፣ መንግስትን እና ኢኮኖሚን መገንባት እንደሚቻል አረጋግጫለሁ” ብለዋል።

የሀገር ሽማግሌ ተወካዮችም በመድረኩ ላይ መድረኩ ለኢትዮጵያ መፃኢ እድል በር የሚከፍት መሆኑን በመግለጽ፤ ለኢትዮጵያ ስንል ሁላችንም ዝቅ ብለን እንስራ ሲሉ መናገራቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

በመድረኩ ላይም ከ50 በላይ የተቋማት መሪዎች በኢትዮጵያ የወደፊት እጣ ፈንታ ዙሪያ ንግግር እንደሚያደርጉም ነው የተገለፀው። (ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: ethiopia 2032, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ashebir says

    December 12, 2019 08:12 pm at 8:12 pm

    በኔ ግምት ሰው ለውይይት ሲተጋ የመጀመሪያ ጥረቱ መሆን ያለበት ለውይይት መክንያት የሆነውን ችገር አንጥሮ በማውጣት፤ የውይይቱ ተሳታፊ በሙሉ ነጥሮ በወጣው ችግር ላይ መስማማት ያስፈልጋቸዋል። ችግሮች ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ። ሁሉም ችግሮች ባንድ ጊዜ ባንድ መንገድ ይፈታሉ ማለትም አይደለም። ነገር ገን ከችግሮቹ ውስጥ መጀመሪአ መፈታት ያለበት የቱ ነው በማለት ችግሮቹን በቅደም ተከተል ዘርዝሮ ማስቀምት ያስፈልጋል። እስካሁን ባየሁዋቸው ውይይቶች ላይ ኡሉ እንዳቸውም በጋራ የትስማሙበትን ችግር አንጥረው አውጥተው ከፊታቸው በማስቀመጥ አይደለም በእውነት እንነጋግር ካልን ውይይት የሚያልቀው ላልታውቅ ችግር መፍትሄ በማፈላለግ ጊዜው የሚያልቀው። ምሳሌ ኮሌጆ ትማሪዎችን ጉዳይ በንውሰ ካማራ አገር የመጣው ተማር ለምን ኦርሞ አገር ይገደላል? ከአኦሮሞ ኧርስ የመጣው ተማሪ ለምን አማራ አገር ይገደላል ለሚለው ጥያቄ ተስብስበው የነብሩ ሊሂቃን ምክንያቱን አንትሮ አውጥቶ ከማውጣትና ለዚያ መፍትሄ ከምውፈለግ ይልቅ፤ ወላጆች ልጆቻችሁን ምከሩ፤ ተማሪዎችም ተምራችሁ ትልቅ ስው እንድትሁኑ ትምሕርታችሁን አጠናክሩ … ውዘት ንው። ጥያቄው ታድያ በርግጥ ተማሪዎቸ ትምህርታቸውን አለማጥናከራችው ነው የግድያው ክንያት? ዝውላጆቸ ልጆቻቸው አለመምከርም ምክንያት መሆኑ እንዴት ታወቀ?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule