• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“[ሻዕቢያ] በየቀኑ እየሞተ ነው”

December 30, 2012 11:58 am by Editor 2 Comments

ኤርትራ ከውጪና ከውስጥ ተዥጎርጉራለች። ከውጪ ደግሞ “በየቀኑ ትንሽ ትንሽ እየሞተች ነው፤ በቅርቡም የሚፈነዳ ነገር አለ” በሚል ግምት ከየአካባቢው እየተሰጠ ነው። ከውስጥ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የኢንቨስትመንት ጥያቄና ግብዣ ላይ ናቸው። የተበላሸባቸውን ዲፕሎማሲ ለማቃናት ላይ ታች እያሉ ነው።

“ኤርትራን በተመለከተ የሚወጡት መረጃዎች የችግሮቿን መወሳሰብና የፕሬዚዳንት ኢሳያስ እጣ ፈንታ መገባደጃው ላይ ለመድረሱ አመላካች ነው” የሚሉ ያሉትን ያህል “ኢሳያስ በውጪ ግንኙነታቸው ላይ የሰሩትን ስህተት በማረም ከበፊት ይልቅ አሁን ወደ ተሻለ መረጋጋትና የኢኮኖሚ ተሃድሶ ተሸጋግራለች” በሚል የሚከራከሩም አሉ። እንደውም ከህወሃት/ኢህአዴግ ይልቅ ሻዕቢያ ከስጋት የራቀ እንደሆነ አድርገው የሚከራከሩ አሉ።

በኤርትራ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ፣ መንግስት ከያዘው ሞኖፖሊ አስተሳሰብ እንደሚወጣና ቃል በመግባት ተወላጆቹንና ውጪ ባለሃብቶችን የሚወተውተው ሻዕቢያ “እየተንፈራገጠ ነው” በሚል ከመሸ የሚያደርገውን ጥረት ኑዛዜ አድርገው የሚመለከቱ አገሪቱ በለውጥ መብላላት ውስጥ እንደምትገኝ ነው የሚናገሩት። ይህንኑ የሚያጠናክር ዘገባ ቪኦኤ አሰምቶ ነበር።

ፈረንሳዊው የመገናኛ ብዙሃን ተመራማሪና ጋዜጠኛ ሊዮናል ቫንሶ ከምስራቅ አፍሪቃ የቪኦኤ ዘጋቢ ፒተር ሃይን ላየን ጋር ባካሄደው ጥያቄና መልስ ሊበጠስ የደረሰ የሚመስል ጉዳይ መድረሱን የሚያመላክት መረጃ አስተላልፏል። ስለ ኤርትራ መንግስት የተደራጀ መረጃ እንዳለው የሚያስታውቀው ጋዜጠኛ ቃለ መጠይቅ ያካሄደው “ተሰወሩ” የተባሉትን የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ አሊ አብዶን አስመልክቶ ነው።

አቶ አሊ ለህክምና ጀርመን እንደነበሩና በታህሳስ ወር አገራቸው መመለስ ሲገባቸው እስካሁን ኤርትራ እንዳልገቡ ከቅርብ የመረጃ ምንጩ ማረጋገጡን የገለጸው ጋዜጠኛ፤ አጋጣሚውን በ2006 ከተሰወሩት የኤርትራ የወጣቶች ንቅናቄ መሪና የቀድሞ የአቶ አሊ አለቃ ጋር አገናኝቶታል። ለጉብኝት ኢሲያ ከሄዱ በኋላ ሲመለሱ ኢሳያስ እንደሚያስሯቸው መረጃ ስለደረሳቸው አገራቸው አልገቡም። እስካሁን ያሉበት አይታወቅም።

አቶ አሊም አውሮፓ ስዊድንና ጀርመን ከመታየታቸው ውጪ የት እንዳሉ መረጃ ማግኘት እንዳልቻለ የጠቆመው ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ፣ የአቶ አሊን መሰወር “በየቀኑ ትንሽ ትንሽ እየሞተ ካለው መንግስት ራሳቸውን ማግለላቸው ይሆናል” ሲል ግምቱን ሰጥቷል። ፒተር ሃይን አቶ አሊ አገራቸውን የሚከዱ ሰው እንዳልሆኑና አሁን የት እንዳሉ ስለማወቁ ላቀረበው ጥያቄ “የት እንደሆኑ አናውቅም። የምናውቀው በተቀነባበረ ደረጃ መሰወራቸውን ነው” በሚል ፈረንሳዊው ተጠያቂ ጋዜጠኛ መልስ ሰጥቷል።

ጋዜጠኛ ሊዮናል የአቶ አሊን በተቀነባበረ ደረጃ መሰወር ተከትሎ ያሉትን መረጃዎች ሲያብራራ ሴት ልጃቸው የሳቸውን ዱካ ተከትላ ወደ ሱዳን ማምራቷን፣ ባለቤታቸው ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ካናዳ የሚኖሩ መሆኑና አስመራ መኖሪያ ቤታቸው በደህንነት ሰዎች መከበቡን አቶ አሊ አገር ውስጥ እንደሌሉ ማረጋገጫ አድርጎ ያቀርባል። በማያያዝም ቤተሰቦቻቸውን ተለይተው ብቻቸውን አስመራ በመኖራቸው ደስተኛ እንዳልነበሩ ተናግሯል።

በኤርትራ ውስጥ የሚታየው ሁኔታ የተካረረ መሆኑንን ያመለከተው ጋዜጠኛ አቶ አሊ በፖለቲካና በግል ጉዳይ በተጠና መንገድ እንደ ተሰወሩ ግምቱን አስቀምጦ፣ “ነገሮች አንድ ቀን ይፈነዳሉ። መንግስትም በአንድ ሰው የመተዳደሩና የመመራቱ እድል ያከትማል” ብሏል።በኤርትራ በጀኔራሎችና በሲቪል ባለስልጣናት መካከል አለመተማመን መንገሱንም አመልክቷል። የቅርብ መረጃ እንዳለው የተናገረው ጋዜጠኛ አቶ አሊ “አገራቸውን ከዱ” እንደማይባል፣ “ከዱ” የሚባለው ካሉበት ሆነው መንግስታቸው የሚያካሂደውን በሙሉ እንደማያምኑበትና እንደማይቀበሉት በገሃድ ሲያስታውቁ ብቻ መሆኑንን እንደሆነ ተናግሯል።አቶ አሊን አስመልክቶ “የኢሳያስ ልጅ አይከዳም! አናምንም” በሚል በስደት የሚኖሩ የኤርትራ  ተወላጆችን በማነጋገር ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ መዘገቡ ይታወሳል።

አቶ አሊ ኢሳያስን ወደ ማምለክ የደረሱ፣ በሽፍትነት ዘመናቸው የሬዲዮ መገናኛቸውን የሚያንቀሳቅሱ ታማቸውና የአቶ ኢሳያስን በርካታ ምስጢር የሚያውቁ የስርዓቱ ተጠቃሚ ስለሆኑ አገር ከድተው እንደማይጠፉ አሁን ድረስ የሚከራከሩ አሉ። እነዚህ ክፍሎች ኢሳያስ ታመዋል የተባሉበትን ወቅትና የርሳቸውም ምላሽ ያስታውሳሉ።

በኤርትራ ያለውን የፕሬስ ነፃነት ለማመጣጠን ጁላይ 15/2009 ከኤርትራ በተሰደዱ ጋዜጠኞች የተቋቋመና በድንበር የለሽ ዘጋቢዎች (Reporters Without Borders) የሚታገዘው ኤሬና /ERENA/ ሬዲዮ በሚያዚያ (April) ወር 2012 በኤርትራ ጄኔራሎች አስቸኳይ ስብሰባ “ኤርትራ እንዴት ትቀጥል?” በሚል መምከራቸውን ከፈረንሳይ መዘገቡን ተከትሎ ኢሳያስ አበቃላቸው ተብሎ እንደነበር ይታወሳል።

በኢትዮጵያ የስደት መንግስት ያቋቋሙትን የኤርትራ መንግስት ተቃዋሚዎች ስብስብ “የኤርትራን ነፃ አገርነት አሳልፈው የሸጡ ከዳተኞች” በማለት የሚጠራው ይህ ሬዲዮ፣ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በጠና መታመማቸውን ተከትሎ “… ጄኔራሎቹ ቀጣዩን የኤርትራ ጉዳይ ‘አገራዊ መግባባት’ በሚሰፍንበት መልኩ ለማስቀጠል ይቻል ዘንድ በፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ላይ መፈንቅለመንግሥት ለማካሄድ ሲያሴሩ ተደርሶባቸዋል በሚል በእስር ላይ ያሉት ከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲፈቱ ወስኗል። የሞቱም ካሉ ለቤተሰቦቻቸው እንዲነገር ከስምምነት ላይ ተደርሷል” የሚል ዘገባ አቅርቦ ነበር።

በዛው ወር ቀለል ባለ አለባበስ ነጠላ ጫማ ተጫምተው በብቸኛዋ ኤሪ-ቲቪ (ERITV) ብቅ በማለት ነገሩን ሁሉ አፈር ያስገቡት አቶ ኢሳያስ ለተወራው ሁሉ መልስ መስጠት እንደሚያስቸግር በማስታወስ፣ በልማት ስራ ተጠምደው ከመክረማቸው ውጪ በጤናቸውም ሆነ በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ አንዳችም ነገር እንዳልተፈጠረ ተናግረው ነበር።

የልማት ስራዎችን ሲጎበኙ አስራ አራት ሰዓት ያህል ያለማቋረጥ ስለተጓዙ ረዥም እንቅልፍ መተኛታቸውን፣ እንቅልፉ ሳይለቃቸው ወደ ቢሮ ሲገቡ የፕሬስ ፀሃፊያቸው ከሰጠቻቸው ወረቀቶች ላይ ስለእርሳቸው ሲወራ የነበረውን  መመልከታቸውን ተናግረዋል። “ሞባይል የለኝም፤ ኢንተርኔትም አልጠቀምም” የሚሉት አቶ ኢሳያስ የተወራውን ሁሉ እንደንፋስ እንደሚቆጥሩት አስምረውበታል። ውሸት በተወራ ቁጥር ቴሌቪዥን ላይ በመውጣት ማስተባበያ መስጠት እንደማይቻል በመጠቆም የተወራባቸውን ክፉ ወሬ በማምከን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ “እኛ ተመስገን ብለን አስራ ሁለት ሰዓት ስንተኛ፣ ውሸታሞቹ ሃያ ሶስት ሰዓት ከሃምሳ ዘጠኝ ደቂቃ እንቅልፍ የላቸውም” ሲሉ ድምጻቸውና አድራሻቸው ሳይታወቅ ለከረሙበት ጊዜያት መልስ ሰጥተዋል። አሜሪካንና ሲ.አይ.ኤንም ወቅሰዋል።

የእርሳቸው መግለጫ እንዳበቃ፣ ኢሳያስ ከጠፉበት ብቅ ብለው ኢንተርቪው መስጠታቸውን ያላጤነው በህወሃት/ኢህአዴግ የሚደገፈውና ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ሰዓት ተጋርቶ ዝግጅት የሚያቀርበው ዳሃይ ኤርትራ በፕሮግራም የፕሬዚዳንት ኢሳያስን የጤና መጓደል በተመለከተ “አጋጣሚውን በመጠቀም አዲሲቷን ኤርትራ ለመመስረት እንነሳ” ሲል ለወታደሮችና ለህዝቡ ጥሪ አሰምቶ ነበር። እስካሁን ግን ምንም የለም።

ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ “አጉራ ዘለል፣ ተናካሽ ውሻ፣ አተራማሽ …” እያሉ የሚሰድቡትን የበረሃ ባለውለታቸውን ሻዕቢያን አስፈንጥረው እንደሚወረውሩት ለዓመታት መዛታቸው አይዘነጋም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aklilu Hailu says

    December 30, 2012 10:18 pm at 10:18 pm

    Thanks Goolagule I apperciate that pls stand bold!!. Well done brothers.

    Reply
  2. Anti Woyanie says

    December 31, 2012 08:42 am at 8:42 am

    Whenever the political temperature in Ethiopia rises, ‘alleged near death’ scenarios of Eritrea, EPLF, or its leader pop up every where. It is hard to identify who is really marching towards death, the highly despised minority and non representative regime racist regime in Ethiopia or that of Eritrea. Time will tell. Remember, three of ur fingers are pointing inward. good luck!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule