• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“[ሻዕቢያ] በየቀኑ እየሞተ ነው”

December 30, 2012 11:58 am by Editor 2 Comments

ኤርትራ ከውጪና ከውስጥ ተዥጎርጉራለች። ከውጪ ደግሞ “በየቀኑ ትንሽ ትንሽ እየሞተች ነው፤ በቅርቡም የሚፈነዳ ነገር አለ” በሚል ግምት ከየአካባቢው እየተሰጠ ነው። ከውስጥ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የኢንቨስትመንት ጥያቄና ግብዣ ላይ ናቸው። የተበላሸባቸውን ዲፕሎማሲ ለማቃናት ላይ ታች እያሉ ነው።

“ኤርትራን በተመለከተ የሚወጡት መረጃዎች የችግሮቿን መወሳሰብና የፕሬዚዳንት ኢሳያስ እጣ ፈንታ መገባደጃው ላይ ለመድረሱ አመላካች ነው” የሚሉ ያሉትን ያህል “ኢሳያስ በውጪ ግንኙነታቸው ላይ የሰሩትን ስህተት በማረም ከበፊት ይልቅ አሁን ወደ ተሻለ መረጋጋትና የኢኮኖሚ ተሃድሶ ተሸጋግራለች” በሚል የሚከራከሩም አሉ። እንደውም ከህወሃት/ኢህአዴግ ይልቅ ሻዕቢያ ከስጋት የራቀ እንደሆነ አድርገው የሚከራከሩ አሉ።

በኤርትራ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ፣ መንግስት ከያዘው ሞኖፖሊ አስተሳሰብ እንደሚወጣና ቃል በመግባት ተወላጆቹንና ውጪ ባለሃብቶችን የሚወተውተው ሻዕቢያ “እየተንፈራገጠ ነው” በሚል ከመሸ የሚያደርገውን ጥረት ኑዛዜ አድርገው የሚመለከቱ አገሪቱ በለውጥ መብላላት ውስጥ እንደምትገኝ ነው የሚናገሩት። ይህንኑ የሚያጠናክር ዘገባ ቪኦኤ አሰምቶ ነበር።

ፈረንሳዊው የመገናኛ ብዙሃን ተመራማሪና ጋዜጠኛ ሊዮናል ቫንሶ ከምስራቅ አፍሪቃ የቪኦኤ ዘጋቢ ፒተር ሃይን ላየን ጋር ባካሄደው ጥያቄና መልስ ሊበጠስ የደረሰ የሚመስል ጉዳይ መድረሱን የሚያመላክት መረጃ አስተላልፏል። ስለ ኤርትራ መንግስት የተደራጀ መረጃ እንዳለው የሚያስታውቀው ጋዜጠኛ ቃለ መጠይቅ ያካሄደው “ተሰወሩ” የተባሉትን የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ አሊ አብዶን አስመልክቶ ነው።

አቶ አሊ ለህክምና ጀርመን እንደነበሩና በታህሳስ ወር አገራቸው መመለስ ሲገባቸው እስካሁን ኤርትራ እንዳልገቡ ከቅርብ የመረጃ ምንጩ ማረጋገጡን የገለጸው ጋዜጠኛ፤ አጋጣሚውን በ2006 ከተሰወሩት የኤርትራ የወጣቶች ንቅናቄ መሪና የቀድሞ የአቶ አሊ አለቃ ጋር አገናኝቶታል። ለጉብኝት ኢሲያ ከሄዱ በኋላ ሲመለሱ ኢሳያስ እንደሚያስሯቸው መረጃ ስለደረሳቸው አገራቸው አልገቡም። እስካሁን ያሉበት አይታወቅም።

አቶ አሊም አውሮፓ ስዊድንና ጀርመን ከመታየታቸው ውጪ የት እንዳሉ መረጃ ማግኘት እንዳልቻለ የጠቆመው ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ፣ የአቶ አሊን መሰወር “በየቀኑ ትንሽ ትንሽ እየሞተ ካለው መንግስት ራሳቸውን ማግለላቸው ይሆናል” ሲል ግምቱን ሰጥቷል። ፒተር ሃይን አቶ አሊ አገራቸውን የሚከዱ ሰው እንዳልሆኑና አሁን የት እንዳሉ ስለማወቁ ላቀረበው ጥያቄ “የት እንደሆኑ አናውቅም። የምናውቀው በተቀነባበረ ደረጃ መሰወራቸውን ነው” በሚል ፈረንሳዊው ተጠያቂ ጋዜጠኛ መልስ ሰጥቷል።

ጋዜጠኛ ሊዮናል የአቶ አሊን በተቀነባበረ ደረጃ መሰወር ተከትሎ ያሉትን መረጃዎች ሲያብራራ ሴት ልጃቸው የሳቸውን ዱካ ተከትላ ወደ ሱዳን ማምራቷን፣ ባለቤታቸው ከሁለት ወንድሞቻቸው ጋር ካናዳ የሚኖሩ መሆኑና አስመራ መኖሪያ ቤታቸው በደህንነት ሰዎች መከበቡን አቶ አሊ አገር ውስጥ እንደሌሉ ማረጋገጫ አድርጎ ያቀርባል። በማያያዝም ቤተሰቦቻቸውን ተለይተው ብቻቸውን አስመራ በመኖራቸው ደስተኛ እንዳልነበሩ ተናግሯል።

በኤርትራ ውስጥ የሚታየው ሁኔታ የተካረረ መሆኑንን ያመለከተው ጋዜጠኛ አቶ አሊ በፖለቲካና በግል ጉዳይ በተጠና መንገድ እንደ ተሰወሩ ግምቱን አስቀምጦ፣ “ነገሮች አንድ ቀን ይፈነዳሉ። መንግስትም በአንድ ሰው የመተዳደሩና የመመራቱ እድል ያከትማል” ብሏል።በኤርትራ በጀኔራሎችና በሲቪል ባለስልጣናት መካከል አለመተማመን መንገሱንም አመልክቷል። የቅርብ መረጃ እንዳለው የተናገረው ጋዜጠኛ አቶ አሊ “አገራቸውን ከዱ” እንደማይባል፣ “ከዱ” የሚባለው ካሉበት ሆነው መንግስታቸው የሚያካሂደውን በሙሉ እንደማያምኑበትና እንደማይቀበሉት በገሃድ ሲያስታውቁ ብቻ መሆኑንን እንደሆነ ተናግሯል።አቶ አሊን አስመልክቶ “የኢሳያስ ልጅ አይከዳም! አናምንም” በሚል በስደት የሚኖሩ የኤርትራ  ተወላጆችን በማነጋገር ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ መዘገቡ ይታወሳል።

አቶ አሊ ኢሳያስን ወደ ማምለክ የደረሱ፣ በሽፍትነት ዘመናቸው የሬዲዮ መገናኛቸውን የሚያንቀሳቅሱ ታማቸውና የአቶ ኢሳያስን በርካታ ምስጢር የሚያውቁ የስርዓቱ ተጠቃሚ ስለሆኑ አገር ከድተው እንደማይጠፉ አሁን ድረስ የሚከራከሩ አሉ። እነዚህ ክፍሎች ኢሳያስ ታመዋል የተባሉበትን ወቅትና የርሳቸውም ምላሽ ያስታውሳሉ።

በኤርትራ ያለውን የፕሬስ ነፃነት ለማመጣጠን ጁላይ 15/2009 ከኤርትራ በተሰደዱ ጋዜጠኞች የተቋቋመና በድንበር የለሽ ዘጋቢዎች (Reporters Without Borders) የሚታገዘው ኤሬና /ERENA/ ሬዲዮ በሚያዚያ (April) ወር 2012 በኤርትራ ጄኔራሎች አስቸኳይ ስብሰባ “ኤርትራ እንዴት ትቀጥል?” በሚል መምከራቸውን ከፈረንሳይ መዘገቡን ተከትሎ ኢሳያስ አበቃላቸው ተብሎ እንደነበር ይታወሳል።

በኢትዮጵያ የስደት መንግስት ያቋቋሙትን የኤርትራ መንግስት ተቃዋሚዎች ስብስብ “የኤርትራን ነፃ አገርነት አሳልፈው የሸጡ ከዳተኞች” በማለት የሚጠራው ይህ ሬዲዮ፣ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በጠና መታመማቸውን ተከትሎ “… ጄኔራሎቹ ቀጣዩን የኤርትራ ጉዳይ ‘አገራዊ መግባባት’ በሚሰፍንበት መልኩ ለማስቀጠል ይቻል ዘንድ በፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ላይ መፈንቅለመንግሥት ለማካሄድ ሲያሴሩ ተደርሶባቸዋል በሚል በእስር ላይ ያሉት ከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲፈቱ ወስኗል። የሞቱም ካሉ ለቤተሰቦቻቸው እንዲነገር ከስምምነት ላይ ተደርሷል” የሚል ዘገባ አቅርቦ ነበር።

በዛው ወር ቀለል ባለ አለባበስ ነጠላ ጫማ ተጫምተው በብቸኛዋ ኤሪ-ቲቪ (ERITV) ብቅ በማለት ነገሩን ሁሉ አፈር ያስገቡት አቶ ኢሳያስ ለተወራው ሁሉ መልስ መስጠት እንደሚያስቸግር በማስታወስ፣ በልማት ስራ ተጠምደው ከመክረማቸው ውጪ በጤናቸውም ሆነ በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ አንዳችም ነገር እንዳልተፈጠረ ተናግረው ነበር።

የልማት ስራዎችን ሲጎበኙ አስራ አራት ሰዓት ያህል ያለማቋረጥ ስለተጓዙ ረዥም እንቅልፍ መተኛታቸውን፣ እንቅልፉ ሳይለቃቸው ወደ ቢሮ ሲገቡ የፕሬስ ፀሃፊያቸው ከሰጠቻቸው ወረቀቶች ላይ ስለእርሳቸው ሲወራ የነበረውን  መመልከታቸውን ተናግረዋል። “ሞባይል የለኝም፤ ኢንተርኔትም አልጠቀምም” የሚሉት አቶ ኢሳያስ የተወራውን ሁሉ እንደንፋስ እንደሚቆጥሩት አስምረውበታል። ውሸት በተወራ ቁጥር ቴሌቪዥን ላይ በመውጣት ማስተባበያ መስጠት እንደማይቻል በመጠቆም የተወራባቸውን ክፉ ወሬ በማምከን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ “እኛ ተመስገን ብለን አስራ ሁለት ሰዓት ስንተኛ፣ ውሸታሞቹ ሃያ ሶስት ሰዓት ከሃምሳ ዘጠኝ ደቂቃ እንቅልፍ የላቸውም” ሲሉ ድምጻቸውና አድራሻቸው ሳይታወቅ ለከረሙበት ጊዜያት መልስ ሰጥተዋል። አሜሪካንና ሲ.አይ.ኤንም ወቅሰዋል።

የእርሳቸው መግለጫ እንዳበቃ፣ ኢሳያስ ከጠፉበት ብቅ ብለው ኢንተርቪው መስጠታቸውን ያላጤነው በህወሃት/ኢህአዴግ የሚደገፈውና ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ሰዓት ተጋርቶ ዝግጅት የሚያቀርበው ዳሃይ ኤርትራ በፕሮግራም የፕሬዚዳንት ኢሳያስን የጤና መጓደል በተመለከተ “አጋጣሚውን በመጠቀም አዲሲቷን ኤርትራ ለመመስረት እንነሳ” ሲል ለወታደሮችና ለህዝቡ ጥሪ አሰምቶ ነበር። እስካሁን ግን ምንም የለም።

ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ “አጉራ ዘለል፣ ተናካሽ ውሻ፣ አተራማሽ …” እያሉ የሚሰድቡትን የበረሃ ባለውለታቸውን ሻዕቢያን አስፈንጥረው እንደሚወረውሩት ለዓመታት መዛታቸው አይዘነጋም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aklilu Hailu says

    December 30, 2012 10:18 pm at 10:18 pm

    Thanks Goolagule I apperciate that pls stand bold!!. Well done brothers.

    Reply
  2. Anti Woyanie says

    December 31, 2012 08:42 am at 8:42 am

    Whenever the political temperature in Ethiopia rises, ‘alleged near death’ scenarios of Eritrea, EPLF, or its leader pop up every where. It is hard to identify who is really marching towards death, the highly despised minority and non representative regime racist regime in Ethiopia or that of Eritrea. Time will tell. Remember, three of ur fingers are pointing inward. good luck!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule