• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ

January 10, 2023 05:37 pm by Editor Leave a Comment


ክፍለ ጦሩ በሸኔ ላይ እየተወሠደ ያለውን ወታደራዊ እርምጃ ለማጠናከር በጉጂ ዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ ሚሊሻዎችን በማሰልጠን የቀጠናውን ሠላምና ፀጥታ በማረጋገጡ ረገድ ውጤታማ ሥራ መሠራቱን አሥታውቋል፡፡

የስልጠናው ዋና አስተባባሪ ሻምበል ባቡ ባላባት እንደገለፁት የፀረ ሽምቅ ግዳጅን በብቃት ከመወጣት ጎን ለጎን የዞኑን የፀጥታ ሀይል ለማጠናከር በርካታ ሚሊሻዎችን የአካል ብቃት የስልት እንዲሁም የተኩስ ልምምድ ሥልጠና በመስጠት ማሥመረቅ ተችሏል፡፡

በአካባቢው በንፁሃን ላይ የሽብር ተግባር ሲፈፅም በቆየው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ላይ እየተወሠደ ለሚገኘው የተጠናከረ ዘመቻ ሠልጣኝ የሚሊሻ ሃይሉ እገዛ ከፍተኛ መሆኑንም የሥልጠና አሥተባባሪው ገልፀዋል፡፡

አሰልጣኝ ዋና ሳጅን ዝናው በበኩላቸው እንደገለፁት የሚሊሻ አባላቱን አሠልጥኖ ማሥመረቁ በቀጠናው የሚገኘውን የፀጥታ ሃይል የሚያጠናክር ከመሆኑም ባሻገር ከህዝቡ ጋር ተናቦ የጥፋት ቡድኑን አባላት ለመከታተል እና ለመመንጠር አሥፈላጊነቱ ጉልህ ነው፡፡

በሚሊሻ አባላቱ ምርቃት ላይ አባ ገዳዎች የወረዳ ሽማግሌዎች የተገኙ ሲሆን በዘላቂነት የቀጠናውን ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ ከመከላከያ ሰራዊቱ እና ከክልሉ የፀጥታ ሃይል ጋር በጋራ እንደሚሠሩም ተናግረዋል፡፡ (መከላከያ ቴሌግራም፤ እዮብ ሰለሞን፤ ፎቶግራፍ እሱባለው ስሜ)

ከሸኔ ጋር በተያያዘ ዜና የአሸባሪው ሸኔ ቡድን አባል ሆነው ከቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያየ የመገናኛ ዘዴ በመገናኘት በአዲስ አበባና ዙሪያ ለሽብር ተግባር ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ÷ ኢፋ መኩሪያ፣ ናስረሰ ያሲን ፣ ገለታ ከተማ፣ ሰኔሳ አበራ፣ ሞሲሳ ቶሎሳ፣ ኢማሚ ደርበው፣ ኢፋት አሕመድ፣ ደበላ አማኑ እና አማንኤል በርኬሳ ናቸው፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ ተጠርጣሪዎቹን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቅርቦ ጉዳያቸው ዛሬ ታይቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ በማሰብ የሸኔ የሽብር ቡድን አባል ሆነው ከሽብር ቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያየ መገናኛ ዘዴ እየተገናኙ ተልዕኮ መቀበላቸውን ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ እና ዙሪያ በሕዝብ መገኛ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ÷ በህቡዕ በመደራጀት በሽብር ቡድኑ ስልጠና በመውሰድ፣ የከተማ እርምጃ ወሳጅ የአባቶርቤ አባላትን እና የተለያዩ የሎጅስቲክ አቅርቦትን በማቅረብ ታኅሣሥ 15 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና በዙሪያው የሽብር ተግባር ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን አብራርቷል፡፡

በተጨማሪም መርማሪ ፖሊስ÷ ቃላቸውን የመቀበል፣ ፎቶና ዐሻራ የማስነሳት ሥራ ማከናወኑን እንዲሁም በፍርድቤት ትዕዛዝ በመኖሪያ ቤታቸው ብርበራ ማካሔዱን አንስቷል፡፡ በእጃቸው ላይ የተገኘ የሞባይል ስልክን ለምርመራ መላኩንና ከግልና ከመንግስት ባንኮች የገንዘብ ዝውውር ለማጣራት ማስረጃ መጠየቁንም ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ማስረጃ ለማምጣት፣ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል፣ ተጨማሪ ማስረጃ ለማሰባሰብ ለመቅረብ በወ/መ/ስ/ህ/ቁግር 59/2 መሰረት የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ወንጀል አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው÷ ማስረጃ ለማሰባሰብ ተብሎ ተጨማሪ ጊዜ ለፖሊስ ሊሰጥ እንደማይገባ እና የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ችሎቱን ጠይቀዋል።

የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች ደግሞ በመንግስት መስሪያ ቤት ሠራተኛ መሆናቸውን እና ቋሚ አድራሻ እንዳላቸው፤ በዋስ ቢወጡ ወደ ሌላ ቦታ መሸሽ እንደማይችሉ ጠቁመው ÷ የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የሁለቱን ወገን መከራከሪያ ነጥብ የመረመረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የተጠርጣሪዎችን ዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ተጨማሪ ምርመራ መደረጉ አስፈላጊ መሆኑን አንስቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፖሊስ ከጠየቀው የ14 ቀን ጊዜ ውስጥ ማስረጃ አሰባስቦ የምስክር ቃል ተቀብሎ እንዲቀርብ የስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ መፍቀዱ ተመላክቷል፡፡ (ታሪክ አዱኛ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule