• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ

January 10, 2023 05:37 pm by Editor Leave a Comment


ክፍለ ጦሩ በሸኔ ላይ እየተወሠደ ያለውን ወታደራዊ እርምጃ ለማጠናከር በጉጂ ዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ ሚሊሻዎችን በማሰልጠን የቀጠናውን ሠላምና ፀጥታ በማረጋገጡ ረገድ ውጤታማ ሥራ መሠራቱን አሥታውቋል፡፡

የስልጠናው ዋና አስተባባሪ ሻምበል ባቡ ባላባት እንደገለፁት የፀረ ሽምቅ ግዳጅን በብቃት ከመወጣት ጎን ለጎን የዞኑን የፀጥታ ሀይል ለማጠናከር በርካታ ሚሊሻዎችን የአካል ብቃት የስልት እንዲሁም የተኩስ ልምምድ ሥልጠና በመስጠት ማሥመረቅ ተችሏል፡፡

በአካባቢው በንፁሃን ላይ የሽብር ተግባር ሲፈፅም በቆየው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ላይ እየተወሠደ ለሚገኘው የተጠናከረ ዘመቻ ሠልጣኝ የሚሊሻ ሃይሉ እገዛ ከፍተኛ መሆኑንም የሥልጠና አሥተባባሪው ገልፀዋል፡፡

አሰልጣኝ ዋና ሳጅን ዝናው በበኩላቸው እንደገለፁት የሚሊሻ አባላቱን አሠልጥኖ ማሥመረቁ በቀጠናው የሚገኘውን የፀጥታ ሃይል የሚያጠናክር ከመሆኑም ባሻገር ከህዝቡ ጋር ተናቦ የጥፋት ቡድኑን አባላት ለመከታተል እና ለመመንጠር አሥፈላጊነቱ ጉልህ ነው፡፡

በሚሊሻ አባላቱ ምርቃት ላይ አባ ገዳዎች የወረዳ ሽማግሌዎች የተገኙ ሲሆን በዘላቂነት የቀጠናውን ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ ከመከላከያ ሰራዊቱ እና ከክልሉ የፀጥታ ሃይል ጋር በጋራ እንደሚሠሩም ተናግረዋል፡፡ (መከላከያ ቴሌግራም፤ እዮብ ሰለሞን፤ ፎቶግራፍ እሱባለው ስሜ)

ከሸኔ ጋር በተያያዘ ዜና የአሸባሪው ሸኔ ቡድን አባል ሆነው ከቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያየ የመገናኛ ዘዴ በመገናኘት በአዲስ አበባና ዙሪያ ለሽብር ተግባር ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ÷ ኢፋ መኩሪያ፣ ናስረሰ ያሲን ፣ ገለታ ከተማ፣ ሰኔሳ አበራ፣ ሞሲሳ ቶሎሳ፣ ኢማሚ ደርበው፣ ኢፋት አሕመድ፣ ደበላ አማኑ እና አማንኤል በርኬሳ ናቸው፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ ተጠርጣሪዎቹን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቅርቦ ጉዳያቸው ዛሬ ታይቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ በማሰብ የሸኔ የሽብር ቡድን አባል ሆነው ከሽብር ቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያየ መገናኛ ዘዴ እየተገናኙ ተልዕኮ መቀበላቸውን ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ እና ዙሪያ በሕዝብ መገኛ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ÷ በህቡዕ በመደራጀት በሽብር ቡድኑ ስልጠና በመውሰድ፣ የከተማ እርምጃ ወሳጅ የአባቶርቤ አባላትን እና የተለያዩ የሎጅስቲክ አቅርቦትን በማቅረብ ታኅሣሥ 15 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና በዙሪያው የሽብር ተግባር ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን አብራርቷል፡፡

በተጨማሪም መርማሪ ፖሊስ÷ ቃላቸውን የመቀበል፣ ፎቶና ዐሻራ የማስነሳት ሥራ ማከናወኑን እንዲሁም በፍርድቤት ትዕዛዝ በመኖሪያ ቤታቸው ብርበራ ማካሔዱን አንስቷል፡፡ በእጃቸው ላይ የተገኘ የሞባይል ስልክን ለምርመራ መላኩንና ከግልና ከመንግስት ባንኮች የገንዘብ ዝውውር ለማጣራት ማስረጃ መጠየቁንም ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ማስረጃ ለማምጣት፣ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል፣ ተጨማሪ ማስረጃ ለማሰባሰብ ለመቅረብ በወ/መ/ስ/ህ/ቁግር 59/2 መሰረት የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ወንጀል አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው÷ ማስረጃ ለማሰባሰብ ተብሎ ተጨማሪ ጊዜ ለፖሊስ ሊሰጥ እንደማይገባ እና የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ችሎቱን ጠይቀዋል።

የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች ደግሞ በመንግስት መስሪያ ቤት ሠራተኛ መሆናቸውን እና ቋሚ አድራሻ እንዳላቸው፤ በዋስ ቢወጡ ወደ ሌላ ቦታ መሸሽ እንደማይችሉ ጠቁመው ÷ የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የሁለቱን ወገን መከራከሪያ ነጥብ የመረመረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የተጠርጣሪዎችን ዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ተጨማሪ ምርመራ መደረጉ አስፈላጊ መሆኑን አንስቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፖሊስ ከጠየቀው የ14 ቀን ጊዜ ውስጥ ማስረጃ አሰባስቦ የምስክር ቃል ተቀብሎ እንዲቀርብ የስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ መፍቀዱ ተመላክቷል፡፡ (ታሪክ አዱኛ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule