• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ

January 10, 2023 05:37 pm by Editor Leave a Comment


ክፍለ ጦሩ በሸኔ ላይ እየተወሠደ ያለውን ወታደራዊ እርምጃ ለማጠናከር በጉጂ ዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ ሚሊሻዎችን በማሰልጠን የቀጠናውን ሠላምና ፀጥታ በማረጋገጡ ረገድ ውጤታማ ሥራ መሠራቱን አሥታውቋል፡፡

የስልጠናው ዋና አስተባባሪ ሻምበል ባቡ ባላባት እንደገለፁት የፀረ ሽምቅ ግዳጅን በብቃት ከመወጣት ጎን ለጎን የዞኑን የፀጥታ ሀይል ለማጠናከር በርካታ ሚሊሻዎችን የአካል ብቃት የስልት እንዲሁም የተኩስ ልምምድ ሥልጠና በመስጠት ማሥመረቅ ተችሏል፡፡

በአካባቢው በንፁሃን ላይ የሽብር ተግባር ሲፈፅም በቆየው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ላይ እየተወሠደ ለሚገኘው የተጠናከረ ዘመቻ ሠልጣኝ የሚሊሻ ሃይሉ እገዛ ከፍተኛ መሆኑንም የሥልጠና አሥተባባሪው ገልፀዋል፡፡

አሰልጣኝ ዋና ሳጅን ዝናው በበኩላቸው እንደገለፁት የሚሊሻ አባላቱን አሠልጥኖ ማሥመረቁ በቀጠናው የሚገኘውን የፀጥታ ሃይል የሚያጠናክር ከመሆኑም ባሻገር ከህዝቡ ጋር ተናቦ የጥፋት ቡድኑን አባላት ለመከታተል እና ለመመንጠር አሥፈላጊነቱ ጉልህ ነው፡፡

በሚሊሻ አባላቱ ምርቃት ላይ አባ ገዳዎች የወረዳ ሽማግሌዎች የተገኙ ሲሆን በዘላቂነት የቀጠናውን ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ ከመከላከያ ሰራዊቱ እና ከክልሉ የፀጥታ ሃይል ጋር በጋራ እንደሚሠሩም ተናግረዋል፡፡ (መከላከያ ቴሌግራም፤ እዮብ ሰለሞን፤ ፎቶግራፍ እሱባለው ስሜ)

ከሸኔ ጋር በተያያዘ ዜና የአሸባሪው ሸኔ ቡድን አባል ሆነው ከቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያየ የመገናኛ ዘዴ በመገናኘት በአዲስ አበባና ዙሪያ ለሽብር ተግባር ሲንቀሳቀሱ ነበሩ የተባሉ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ÷ ኢፋ መኩሪያ፣ ናስረሰ ያሲን ፣ ገለታ ከተማ፣ ሰኔሳ አበራ፣ ሞሲሳ ቶሎሳ፣ ኢማሚ ደርበው፣ ኢፋት አሕመድ፣ ደበላ አማኑ እና አማንኤል በርኬሳ ናቸው፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መርማሪ ተጠርጣሪዎቹን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቅርቦ ጉዳያቸው ዛሬ ታይቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ በማሰብ የሸኔ የሽብር ቡድን አባል ሆነው ከሽብር ቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያየ መገናኛ ዘዴ እየተገናኙ ተልዕኮ መቀበላቸውን ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ እና ዙሪያ በሕዝብ መገኛ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ÷ በህቡዕ በመደራጀት በሽብር ቡድኑ ስልጠና በመውሰድ፣ የከተማ እርምጃ ወሳጅ የአባቶርቤ አባላትን እና የተለያዩ የሎጅስቲክ አቅርቦትን በማቅረብ ታኅሣሥ 15 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና በዙሪያው የሽብር ተግባር ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን አብራርቷል፡፡

በተጨማሪም መርማሪ ፖሊስ÷ ቃላቸውን የመቀበል፣ ፎቶና ዐሻራ የማስነሳት ሥራ ማከናወኑን እንዲሁም በፍርድቤት ትዕዛዝ በመኖሪያ ቤታቸው ብርበራ ማካሔዱን አንስቷል፡፡ በእጃቸው ላይ የተገኘ የሞባይል ስልክን ለምርመራ መላኩንና ከግልና ከመንግስት ባንኮች የገንዘብ ዝውውር ለማጣራት ማስረጃ መጠየቁንም ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ማስረጃ ለማምጣት፣ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል፣ ተጨማሪ ማስረጃ ለማሰባሰብ ለመቅረብ በወ/መ/ስ/ህ/ቁግር 59/2 መሰረት የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ወንጀል አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው÷ ማስረጃ ለማሰባሰብ ተብሎ ተጨማሪ ጊዜ ለፖሊስ ሊሰጥ እንደማይገባ እና የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ችሎቱን ጠይቀዋል።

የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች ደግሞ በመንግስት መስሪያ ቤት ሠራተኛ መሆናቸውን እና ቋሚ አድራሻ እንዳላቸው፤ በዋስ ቢወጡ ወደ ሌላ ቦታ መሸሽ እንደማይችሉ ጠቁመው ÷ የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የሁለቱን ወገን መከራከሪያ ነጥብ የመረመረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የተጠርጣሪዎችን ዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ተጨማሪ ምርመራ መደረጉ አስፈላጊ መሆኑን አንስቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፖሊስ ከጠየቀው የ14 ቀን ጊዜ ውስጥ ማስረጃ አሰባስቦ የምስክር ቃል ተቀብሎ እንዲቀርብ የስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ መፍቀዱ ተመላክቷል፡፡ (ታሪክ አዱኛ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule