• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእስራኤል ቀድሞው ጠ/ሚ/ር ወደ “ቃሊቲ” ወረዱ፤ የሃይማኖት መሪም ተከትለዋቸዋል

February 17, 2016 08:51 am by Editor Leave a Comment

* “ማንም ከሕግ በላይ መሆን አይችልም” ታሳሪው ጠ/ሚ/ር

የቀድሞ የእስራኤል ጠ/ሚ/ር ኤሁድ ኦልመርት ወደ እስር ቤት ወረዱ፡፡ በሃይማኖቱ ዓለም ታላቅ ዝነኝነትን የተጎናጸፉት ራባይ (ረቢ) ዮሺያሁ ፒንቶም ወደዚያው አምርተዋል፡፡ ጉዳዩን የሚከታተሉ ወገኖች የህወሃት/ኢህአዴግ “ሻኮችን” ማን ይንካቸው ሲሉ ጠይቀዋል?

እስራኤልን ለሦስት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት የሰባ ዓመቱ ኤሁድ ኦልመርት ከሙስና ጋር በተያያዘ የ19 ወራት እስር ተበይኖባቸው እስርቤት ወርደዋል፡፡

በአስተዳደር ዘመናቸው ከፍልስጤማውያን ጋር ስምምነት ለማድረግ ከፍተኛ እርምጃዎች ሲወስዱ የነበሩት ኦልመርት ወደ ወሳኝ ደረጃ ላይ ሲደርሱ በሥልጣን ላይ እንዳሉ በሙስና፣ ጉቦ፣ እና ሌሎች ገንዘብ ነክ ወንጀሎች መከሰሳቸው ይታወሳል፡፡ በተለይም የአናፖሊስ ኮንፍራንስ በተባለው ስብሰባ በርካታ ውሳኔዎችን ለድርድር በማምጣት ከፍልስጤማውያን ጋር ለመስማማት መሞከራቸው በአክራሪዎች ዘንድ ለሙስናው ክስ እንዳጋለጣቸው ይነገራል፡፡

እስራኤል ሙሉ በሙሉ ከምዕራብ ዳርቻዎች የመልቀቋን እንዲሁም የየሩሳሌምን ጥንታዊ ከተማ እስራኤልና ፍልስጤም በእኩል የሚጠቀሙባት ለማድረግ በዓለምአቀፍ ቁጥጥር ሥር እንድትውል የሚያደርግና የመሳሰሉ ያልታሰቡ አጀንዳዎችን ወደ ጠረጴዛ ማምጣታቸው እና ለስምምነት ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

የየሩሳሌም ከንቲባና የገንዘብ ሚ/ር በነበሩበት ጊዜ ከምርጫና የቤቶች ግንባታ ጋር በተያየዘ የወሰዱት ጉቦና መማለጃ አለ በሚል ክስ የተመሰረተባቸው ከፍልስጤማውያን ጋር ወደ ስምምነት ለመድረስ ከፍተኛ ሙከራ ባደረጉበት ወቅት መሆኑ ክሱ ፖለቲካዊ ይዘት እንዳለው ደጋፊዎቻቸው ይናገራሉ፡፡

ኦልመርት ከሥልጣናቸው እንደለቀቁ በእግራቸው የተተኩት የአሁኑ ጠ/ሚ/ር ቢኒያም ኔታኒያሁ ሲሆኑ ከፍልስጤማውያን ጋር የሚደረገው ድርድርም በዚያኑ መልክ አቅጣጫውን ቀይሯል፡፡

“በኔ ላይ የተመሰረተውን የጉቦ ክስ ፈጽሞ የማልቀበለው ነው” ያሉት ወደ እስርቤት በመሄድ የመጀመሪያው የእስራኤል ጠ/ሚ/ር የሆኑት ኦልመርት “ውሳኔው ቢከብድብኝም፤ እቀበለዋለሁ፤ ማንም ሰው ከህግ በላይ መሆን አይችልም” በማለት ከመታሰራቸው በፊት ባሰራጩት የቪዲዮ መልዕክት ተናግረዋል፡፡olmert pinto

በሌላ በኩል በእስራኤል አክራሪ ኦርቶዶክስ አይሁድ የሆኑትና የራሳቸውን የሃይማኖት መስመር የከፈቱት ራባይ (ረቢ) ዮሺያሁ ፒንቶ በሙስና እና ጉቦ ተከስሰው የተበየነባቸውን የአንድ ዓመት እስር ለመፈጸም ወደ እስር ቤት አምርተዋል፡፡ ከጉቦ ጋር በማያያዝም በሚመሯቸው ድርጅቶች ውስጥ በደረሰ ብክነት ክስ ተመስርቶባቸው ተፈርዶባቸዋል፡፡

ራሳቸውን “እኛ” እያሉ የሚጠሩት የ42ቱ የሃይማኖት መሪ በእስኤልና በአሜሪካ በተለይ በኒውዮርክ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ባለጸጋዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ … የአስተምህሮታቸው ደቀመዛሙርት በመሆናቸው እና ከግለሰቦቹ ጋር ባላቸው የጠበቀ ግንኙነት “አይነኬ” እንደሆኑ ይነገርላቸው ነበር፡፡

በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ሲሉ በመታመማቸው ምክንያት የፍርዱን አካሄድ የሚያስተጓጉሉ ቢመስሉም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ወደ እስር ቤት ከመወሰዳቸው በፊትም “እኛ ታምመን ነበር፤ ሆኖም ለአንዲትም ደቂቃ አልፈራንም” በማለት ተናግረዋል፡፡ ህምመማቸውን ምክንያት በማድረግ ወደ እስር ቤት እንዳይወሰዱ ሙከራ ቢያደርጉም ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡

በሙስና እና ግልጽነት ዓለምአቀፍ መለኪያ መሠረት እስራኤል 37ኛ ደረጃ አካባቢ ስትገኝ ኢትዮጵያ 110ኛ አካባቢ በሙስና ከተዘፈቁ አገራት መካከል አንዷ በመሆን ትጠቀሳለች፡፡

ሰሞኑን በእስራኤል የተከሰተውን የሚከታተሉ ወገኖች ሙስና የዕለት ተለዕት ክስተት በሆነባት የህወሃት/ኢህአዴግ ኢትዮጵያ የሚገኙን “የሙስና ሻርኮች” ማን ይደርስባቸው ይሆን በማለት ለጎልጉል ጥያቄ አዘል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ “እስከ እንጥላችን ገምተናል” በማለት በራሱ በመሪው የተተቸውና ከአናት ጀምሮ የሙስና ባህር ውስጥ የሚዋኘው ኢህአዴግ በተለይ በ“አይነኬው” ህወሃትና ግብረአበሮቹ የሚፈጸመው ዓይን ያወጣ ሙስና እና ግፍ ከሥሩ እስካልተነቀለ ድረስ አሁን የሚታየው “የመልካም አስተዳደር” ነጠላ ዜማ ከቀናት በኋላ መሰልቸቱ አይቀርም ብለዋል፡፡

ጥርስ አልባው የጸረ ሙስና ኮሚሽንም የፖለቲካ ሥራ ለመተግበር የተፈጠረና የተቀመጠ እንጂ በእርግጥ ሥልጣንና ኃይል የተጎናጸፈ በራሱ የሚወስን ድርጅት እንዳልሆነ እነዚሁ ወገኖች ያስረዳሉ፡፡

የሙስናውን “ሻርኮች” በተመለከተ ጉልጉል “ሙስናን በስንጥር” በሚል የዛሬ ሦስት ዓመት አካባቢ ባቀረበው ዘገባ ላይ እንዲህ ብሎ ነበር፡፡ “በቀረጥ፣ በሙስናና ባለስልጣናትን የንግድ ሸሪክ በማድረግ ኢትዮጵያን እየጋለቡዋት ያሉ “ባለሃብቶችና አሽከሮቻቸው” እስካልተነኩ ድረስ ኢህአዴግ በሙስና ላይ የጀመረውን ትግል ሙሉ ሊያደርገው አይችልም። ጅማሮው የችግሩ ቁልፍና እምብርት በሆነው ተቋም ላይ መሆኑ ይበል የሚያስብል ቢሆንም የሙስናው ድር ያልተበተበው የለምና የመጨረሻው አካሄድ ወዴት እንደሚያመራ ለመገመት ቢቻልም ጅምሩ ይገፋል የሚል ጥርጣሬ በስፋት አለ።…

“የባለስልጣናት ሚስቶችን፣ ዘመዶችና ወዳጆችን በተቋሞቻቸው ውስጥ በማይመጥኑት ሃላፊነት በመመደብ፣  ከተለያዩ የማማለያ ሽልማቶች ጋር ከፍተኛ ደሞዝ በመክፈል፣ አንዳንዴም ውጪ አገር ድረስ የህክምና ወጪ በመሸፈን ሰበብ የአገሪቱን የአመራር በትር ጨብጠው አገሪቱን እያለቡ ያሉት ሙሰኞች በይፋ እንደሚታወቁ የሚገልጹ ክፍሎች “አሁን ተጀመረ የተባለውና ይፋ የተደረገው የሙስና ትግል ህወሃት/ኢህአዴግ እነዚህን ክፍሎች ብብቱ ስር ይዞ የሚቀጥል ከሆነ ከቀልድ አይዘልም” ሲሉ ጥርጣሬያቸውን ያስቀምጣሉ። ራሱ ህወሃት የሙስናው ንጉሥ ሆኖ “ሙስናን እዋጋለሁ” ማለቱ ከንቱ ፕሮፓጋንዳ ነው …

“አትራፊ የሆኑ የህዝብና የአገር ተቋማትን ወደ ግላቸው ያለ ክፍያ፣ ያለ ተመጣጣኝ ዋጋ፣ በተጭበረበረ ጨረታና አሰራር ወደ ግላቸው በማዞር አቶ መለስ “ተራው ህዝብ” በማለት በሚጠሩት ህዝብ ትከሻ ላይ እንዳሻቸው የሚዘሉትን “የሙስና አባቶችን” መታገል የማይችል የጸረ ሙስና ቀረርቶ ከተራ የፖለቲካ ልዩነት የዘለለ መነሻና መድረሻ ሊኖረው አይችልም። ለዚህም ነው የጸረ ሙስና ኮሚሽን በርካታ መረጃዎች እየደረሱት አፉን እንደተለጎመ የጋማ እንስሳ እንደ ስሙ መሆን ያልቻለው፤ ምክንያቱም ፈጣሪው ለሆነው መስገድ የግዱ ነውና፡፡”

ስለዚህ አሁንም ጥያቄው “ዋናቹን ሌቦችና የሙስና ሻርኮች ማን ይነካቸዋል?” ነው!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule