• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው ተጀመረ!

June 3, 2013 08:34 am by Editor Leave a Comment

ሙስናው ላይ የተጀመረው ዘመቻ ሙስናን በስንጥር የሚያሰኝ ቢሆንም አቶ መለስ ያልደፈሩትን ሰፈር አቶ ሃይለማርያም ነክተውታልና በኢህአዴግ ታሪክ የሙስናን ሰፈር በማንኳኳት ግንባር ቀደሙ ሰው ያደርጋቸዋል። እኛም ጅምሩ መልካም ነው እንላለን። ግን ጥያቄም ማሳሰቢያም አለን። ለማንኛውም በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው የተጀመረ ይመስለናል።

በሙስና የተጠረጠሩ ነጋዴዎች፣ ደላሎች፣ አቀባባይ የተባሉና የመንግስት ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ከተሰማ ጀምሮ ህዝብ በስፋት እየተቸ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የተደላደለውን ሙስና ህዝብ ጠንቅቆ ከነባለቤቶቹ ያውቃል። ይረዳል። ያሸታል። ባለፈ ባገደመ ቁጥር ለድህነቱ ማስታገሻ ያላምጣቸዋል።

ሙስና ሲባል ሙስና ነው። ወንጀል ሲባል ወንጀል ነው። ህግ መተላለፍ ያስጠይቃል። አሁን እንደሚታየው ግን የጸረ ሙስናው ዘመቻ ሰፈር የለየ ይመስላል። ዋናዎቹ “ሻርኮች” አልተነኩም። ዋናዎቹ “የማበስበሻው ባህር” ፊታውራሪዎች አሁንም እያገሱ ነው። እነዚህ አገር ወዳድ የሚመስሉ  የሙስና መፈልፈያ ማሽን አምራቾች ለምን ዝም ተባሉ? የህዝብ ጥያቄ ነው? የምስኪን ዜጎች ጥያቄ ነው። በተለይም “ጠቁሙኝ እርምጃ እወስዳለሁ” በማለት ለተናገሩት አዲሱ መሪ፡፡

በኢትዮጵያ በትዕዛዝ ንብረታቸውን የተነጠቁ፣ በደል ደርሶባቸው ፍርድ እናገኛለን ብለው ወደ ህግ አምርተው በትዕዛዝ የተበየነባቸው፣ በባለጊዜዎች መመሪያ ቅርስና ርስታቸውን የተነጠቁ፣ ተራ የቀበሌ ጭቃ ቤት ሳይቀር የተዘረፉ፣ የነፍስና የወንጀል ጉዳዮች ውስጥ መዘፈቃቸው እየታወቀ ክስ የማይመሰረትባቸውና በወንጀል ተጨማልቀው አገሪቱ ላይ የነገሱ ስለመኖራቸው መነገር ከጀመረ ያው የኢህአዴግን የስልጣን ዘመን ያክል ቆይቷል።

ፍርድና ርትዕ እንዲጓደል ብር ከባንክ በትዕዛዝ ተበድረው በፌስታል የሚረጩ፣ እዳ በሚጮህበት ሆቴሎቻቸው ውስጥ አልኮሆል እያራጩ “የገበያ ወሲብ” የሚያሻቅጡ፣ የሰው ትዳር የሚደፍሩ፣ አስፈራርተውና አስገድደው አህቶችና እናቶችን ከትዳራቸው የሚለዩ፣ ቤተሰብ የሚበትኑ፣ ቀና ብላችሁ ለምን አያችሁን በሚል እስከ ነፍስ ማጥፋት የሚደርሱ ማፍያዎች ፍርድ ቤቱንና የፍትህ ደጅ ዙሪያ ገባውን ቁልፍ ተረክበው አገሪቱን እየጋለቡዋት ነው የሚለው ዜና ተብሎ፣ ተብሎ ያለቀለት የማይሸፈን የአደባባይ ጉዳይ ነው።

“ግብር ለምን ክፈሉ እንባላለን” በሚል የስርዓቱን ቁንጮዎች በመያዝ ባለስልጣናትን ከሃላፊነታቸው የሚያስነሱ፣ ግብር የሚጠየቁበትን ሰነድ ቢሮ እያሰበሩ የሚዘርፉ፣ ሰነድ የሚያጠፉ፣ ለሰሩት ወንጀል በህግ ሲጠየቁ የህግ አካሄዱን በመመሪያ የሚያሳግዱ፣ በራሳቸው ፊርማና ማህተም “በትዕዛዝ ክስ አዘጋን” ብለው ለየጋዜጣው መግለጫ የሚበትኑ ወረበሎች ስለመበራከታቸው መለፍለፍ ከተጀመረ አንድ ጠ/ሚኒስትር አልፈው ሁለተኛው ተተክተዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ደብዳቤ እያጻፉና ትዕዛዝ እንዲተላለፍላቸው እያደረጉ የንግድ ውድድሩን ያዛቡ፣ ህግ አክብረው የሚሰሩትን ዜጎች ከገበያና ከውድድር እንዲገለሉ ያስደረጉ፣ ኢትዮጵያን “ለጠቅላይ “ሊጫወቱባት የሚዳዳቸው ወረበሎችን ያላካተተ የጸረ ሙስና ዘመቻ ከቶውንም ተቀባይነት እንደሌለው ህዝብ እያወጋ ነው።

የፍትህ ሚኒስትሩ ከሃላፊነት መነሳታቸውን ተከትሎ የፍርድ ሂደት ያዛቡ፣ መረጃ የቀረበባቸውን ክሶች ያሳገዱ፣ በመመሪያና በተለያዩ ንክኪዎች ህግ እንዲሰቀል ያደረጉ አቃብያነህግ እንደሚታሰሩ ሰምተናል። ምርመራው በሰነድ የተደገፈ ስለመሆኑ ይፋ ሆኗል። ይህንን ዜና የሰሙ “አዋራው ጨሰ፤ በህዝብ አቆጣጠር ጨዋታው ተጀመረ” እያሉ ነው።

ፍትህ ተጓድሎባቸው የአቤቱታ ፋይላቸው የተዘጋባቸው የጨዋታውን መጀመር ሲጠብቁ ነበር። በህይወት ጉዳይ ሻርኮቹን ከሰው ፋይላቸው የተቀረቀረባቸው አሉ። ሻርኮቹን በህግ በመጠየቃቸው ብቻ እስር ቤት የተቀረቀሩ አሉ። ፍትህ እንዲዛባ አድርገው የራሳቸውን ያልሆነ ንብረት የወሰዱ አሉ። ንብረታቸውን ተዘርፈው ልመና የወጡ አሉ። ሚስቶቻቸውን ተቀምተው እጃቸውን አጣጥፈው የተቀመጡ አሉ። ብዙ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል የሰሩና የሚጠየቁበትን ፋይል ያሳገዱ መጨረሻቸው ምን ይሆን? በግፍ የሞቱ ደማቸው ይጮሃል። በግፍ በልማት ስም ቤቷ የፈረሰባትና ለባለጊዜ ስፍራ የለቀቀች ደቃቃ እናት የጣር ድምጽ ይሰማል። ህግ ጎድሎባቸው፣ አቤት የሚሉበት ያጡ ወገኖች ሮሮ ከልክ አልፏል። በፖሊስ፣ በአቃቤ ህግ፣ በዳኛ፣ ከዛም በላይ በ”ተላላኪ ባለስልጣኖች” ትዕዛዝ መብቶቻቸውን የተገፈፉ የፍትህ ያለህ እያሉ ዓመታት አስቆጥረዋል።

አሁን በእኛ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። በህዝብ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። ኳሷ አደገኛ ቀጣና ውስጥ ናት። የተነቁ ፋይሎች፣ የታገዱ ጉዳዮች፣ የታደፈኑ የፍትህ ጉዳዮች ከልክ በላይ ናቸው። አሳፋኞቹም እዛው ኢህአዴግ ደጅ አረፍ እንዲሉ የተደረጉትን ጨምሮ በየደረጃው አሉ። አብረው የሚነግዱም አሉ። እነዚህን ሁሉ አልፈው መሔድ ከተቻለ ጨዋታው በትክክል በህዝብ የሰዓት አቆጣጠር ተጀምሯል። አለበለዚያ ግን የህዝብና የመንግስት አቆጣጠር ተለያይቷል። አንዱ ሲተኛ አንዱ ይነቃል። ሳይገናኙ ይተላለፋሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule