• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው ተጀመረ!

June 3, 2013 08:34 am by Editor Leave a Comment

ሙስናው ላይ የተጀመረው ዘመቻ ሙስናን በስንጥር የሚያሰኝ ቢሆንም አቶ መለስ ያልደፈሩትን ሰፈር አቶ ሃይለማርያም ነክተውታልና በኢህአዴግ ታሪክ የሙስናን ሰፈር በማንኳኳት ግንባር ቀደሙ ሰው ያደርጋቸዋል። እኛም ጅምሩ መልካም ነው እንላለን። ግን ጥያቄም ማሳሰቢያም አለን። ለማንኛውም በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው የተጀመረ ይመስለናል።

በሙስና የተጠረጠሩ ነጋዴዎች፣ ደላሎች፣ አቀባባይ የተባሉና የመንግስት ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ከተሰማ ጀምሮ ህዝብ በስፋት እየተቸ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የተደላደለውን ሙስና ህዝብ ጠንቅቆ ከነባለቤቶቹ ያውቃል። ይረዳል። ያሸታል። ባለፈ ባገደመ ቁጥር ለድህነቱ ማስታገሻ ያላምጣቸዋል።

ሙስና ሲባል ሙስና ነው። ወንጀል ሲባል ወንጀል ነው። ህግ መተላለፍ ያስጠይቃል። አሁን እንደሚታየው ግን የጸረ ሙስናው ዘመቻ ሰፈር የለየ ይመስላል። ዋናዎቹ “ሻርኮች” አልተነኩም። ዋናዎቹ “የማበስበሻው ባህር” ፊታውራሪዎች አሁንም እያገሱ ነው። እነዚህ አገር ወዳድ የሚመስሉ  የሙስና መፈልፈያ ማሽን አምራቾች ለምን ዝም ተባሉ? የህዝብ ጥያቄ ነው? የምስኪን ዜጎች ጥያቄ ነው። በተለይም “ጠቁሙኝ እርምጃ እወስዳለሁ” በማለት ለተናገሩት አዲሱ መሪ፡፡

በኢትዮጵያ በትዕዛዝ ንብረታቸውን የተነጠቁ፣ በደል ደርሶባቸው ፍርድ እናገኛለን ብለው ወደ ህግ አምርተው በትዕዛዝ የተበየነባቸው፣ በባለጊዜዎች መመሪያ ቅርስና ርስታቸውን የተነጠቁ፣ ተራ የቀበሌ ጭቃ ቤት ሳይቀር የተዘረፉ፣ የነፍስና የወንጀል ጉዳዮች ውስጥ መዘፈቃቸው እየታወቀ ክስ የማይመሰረትባቸውና በወንጀል ተጨማልቀው አገሪቱ ላይ የነገሱ ስለመኖራቸው መነገር ከጀመረ ያው የኢህአዴግን የስልጣን ዘመን ያክል ቆይቷል።

ፍርድና ርትዕ እንዲጓደል ብር ከባንክ በትዕዛዝ ተበድረው በፌስታል የሚረጩ፣ እዳ በሚጮህበት ሆቴሎቻቸው ውስጥ አልኮሆል እያራጩ “የገበያ ወሲብ” የሚያሻቅጡ፣ የሰው ትዳር የሚደፍሩ፣ አስፈራርተውና አስገድደው አህቶችና እናቶችን ከትዳራቸው የሚለዩ፣ ቤተሰብ የሚበትኑ፣ ቀና ብላችሁ ለምን አያችሁን በሚል እስከ ነፍስ ማጥፋት የሚደርሱ ማፍያዎች ፍርድ ቤቱንና የፍትህ ደጅ ዙሪያ ገባውን ቁልፍ ተረክበው አገሪቱን እየጋለቡዋት ነው የሚለው ዜና ተብሎ፣ ተብሎ ያለቀለት የማይሸፈን የአደባባይ ጉዳይ ነው።

“ግብር ለምን ክፈሉ እንባላለን” በሚል የስርዓቱን ቁንጮዎች በመያዝ ባለስልጣናትን ከሃላፊነታቸው የሚያስነሱ፣ ግብር የሚጠየቁበትን ሰነድ ቢሮ እያሰበሩ የሚዘርፉ፣ ሰነድ የሚያጠፉ፣ ለሰሩት ወንጀል በህግ ሲጠየቁ የህግ አካሄዱን በመመሪያ የሚያሳግዱ፣ በራሳቸው ፊርማና ማህተም “በትዕዛዝ ክስ አዘጋን” ብለው ለየጋዜጣው መግለጫ የሚበትኑ ወረበሎች ስለመበራከታቸው መለፍለፍ ከተጀመረ አንድ ጠ/ሚኒስትር አልፈው ሁለተኛው ተተክተዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ደብዳቤ እያጻፉና ትዕዛዝ እንዲተላለፍላቸው እያደረጉ የንግድ ውድድሩን ያዛቡ፣ ህግ አክብረው የሚሰሩትን ዜጎች ከገበያና ከውድድር እንዲገለሉ ያስደረጉ፣ ኢትዮጵያን “ለጠቅላይ “ሊጫወቱባት የሚዳዳቸው ወረበሎችን ያላካተተ የጸረ ሙስና ዘመቻ ከቶውንም ተቀባይነት እንደሌለው ህዝብ እያወጋ ነው።

የፍትህ ሚኒስትሩ ከሃላፊነት መነሳታቸውን ተከትሎ የፍርድ ሂደት ያዛቡ፣ መረጃ የቀረበባቸውን ክሶች ያሳገዱ፣ በመመሪያና በተለያዩ ንክኪዎች ህግ እንዲሰቀል ያደረጉ አቃብያነህግ እንደሚታሰሩ ሰምተናል። ምርመራው በሰነድ የተደገፈ ስለመሆኑ ይፋ ሆኗል። ይህንን ዜና የሰሙ “አዋራው ጨሰ፤ በህዝብ አቆጣጠር ጨዋታው ተጀመረ” እያሉ ነው።

ፍትህ ተጓድሎባቸው የአቤቱታ ፋይላቸው የተዘጋባቸው የጨዋታውን መጀመር ሲጠብቁ ነበር። በህይወት ጉዳይ ሻርኮቹን ከሰው ፋይላቸው የተቀረቀረባቸው አሉ። ሻርኮቹን በህግ በመጠየቃቸው ብቻ እስር ቤት የተቀረቀሩ አሉ። ፍትህ እንዲዛባ አድርገው የራሳቸውን ያልሆነ ንብረት የወሰዱ አሉ። ንብረታቸውን ተዘርፈው ልመና የወጡ አሉ። ሚስቶቻቸውን ተቀምተው እጃቸውን አጣጥፈው የተቀመጡ አሉ። ብዙ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል የሰሩና የሚጠየቁበትን ፋይል ያሳገዱ መጨረሻቸው ምን ይሆን? በግፍ የሞቱ ደማቸው ይጮሃል። በግፍ በልማት ስም ቤቷ የፈረሰባትና ለባለጊዜ ስፍራ የለቀቀች ደቃቃ እናት የጣር ድምጽ ይሰማል። ህግ ጎድሎባቸው፣ አቤት የሚሉበት ያጡ ወገኖች ሮሮ ከልክ አልፏል። በፖሊስ፣ በአቃቤ ህግ፣ በዳኛ፣ ከዛም በላይ በ”ተላላኪ ባለስልጣኖች” ትዕዛዝ መብቶቻቸውን የተገፈፉ የፍትህ ያለህ እያሉ ዓመታት አስቆጥረዋል።

አሁን በእኛ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። በህዝብ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። ኳሷ አደገኛ ቀጣና ውስጥ ናት። የተነቁ ፋይሎች፣ የታገዱ ጉዳዮች፣ የታደፈኑ የፍትህ ጉዳዮች ከልክ በላይ ናቸው። አሳፋኞቹም እዛው ኢህአዴግ ደጅ አረፍ እንዲሉ የተደረጉትን ጨምሮ በየደረጃው አሉ። አብረው የሚነግዱም አሉ። እነዚህን ሁሉ አልፈው መሔድ ከተቻለ ጨዋታው በትክክል በህዝብ የሰዓት አቆጣጠር ተጀምሯል። አለበለዚያ ግን የህዝብና የመንግስት አቆጣጠር ተለያይቷል። አንዱ ሲተኛ አንዱ ይነቃል። ሳይገናኙ ይተላለፋሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule