• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው ተጀመረ!

June 3, 2013 08:34 am by Editor Leave a Comment

ሙስናው ላይ የተጀመረው ዘመቻ ሙስናን በስንጥር የሚያሰኝ ቢሆንም አቶ መለስ ያልደፈሩትን ሰፈር አቶ ሃይለማርያም ነክተውታልና በኢህአዴግ ታሪክ የሙስናን ሰፈር በማንኳኳት ግንባር ቀደሙ ሰው ያደርጋቸዋል። እኛም ጅምሩ መልካም ነው እንላለን። ግን ጥያቄም ማሳሰቢያም አለን። ለማንኛውም በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው የተጀመረ ይመስለናል።

በሙስና የተጠረጠሩ ነጋዴዎች፣ ደላሎች፣ አቀባባይ የተባሉና የመንግስት ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ከተሰማ ጀምሮ ህዝብ በስፋት እየተቸ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የተደላደለውን ሙስና ህዝብ ጠንቅቆ ከነባለቤቶቹ ያውቃል። ይረዳል። ያሸታል። ባለፈ ባገደመ ቁጥር ለድህነቱ ማስታገሻ ያላምጣቸዋል።

ሙስና ሲባል ሙስና ነው። ወንጀል ሲባል ወንጀል ነው። ህግ መተላለፍ ያስጠይቃል። አሁን እንደሚታየው ግን የጸረ ሙስናው ዘመቻ ሰፈር የለየ ይመስላል። ዋናዎቹ “ሻርኮች” አልተነኩም። ዋናዎቹ “የማበስበሻው ባህር” ፊታውራሪዎች አሁንም እያገሱ ነው። እነዚህ አገር ወዳድ የሚመስሉ  የሙስና መፈልፈያ ማሽን አምራቾች ለምን ዝም ተባሉ? የህዝብ ጥያቄ ነው? የምስኪን ዜጎች ጥያቄ ነው። በተለይም “ጠቁሙኝ እርምጃ እወስዳለሁ” በማለት ለተናገሩት አዲሱ መሪ፡፡

በኢትዮጵያ በትዕዛዝ ንብረታቸውን የተነጠቁ፣ በደል ደርሶባቸው ፍርድ እናገኛለን ብለው ወደ ህግ አምርተው በትዕዛዝ የተበየነባቸው፣ በባለጊዜዎች መመሪያ ቅርስና ርስታቸውን የተነጠቁ፣ ተራ የቀበሌ ጭቃ ቤት ሳይቀር የተዘረፉ፣ የነፍስና የወንጀል ጉዳዮች ውስጥ መዘፈቃቸው እየታወቀ ክስ የማይመሰረትባቸውና በወንጀል ተጨማልቀው አገሪቱ ላይ የነገሱ ስለመኖራቸው መነገር ከጀመረ ያው የኢህአዴግን የስልጣን ዘመን ያክል ቆይቷል።

ፍርድና ርትዕ እንዲጓደል ብር ከባንክ በትዕዛዝ ተበድረው በፌስታል የሚረጩ፣ እዳ በሚጮህበት ሆቴሎቻቸው ውስጥ አልኮሆል እያራጩ “የገበያ ወሲብ” የሚያሻቅጡ፣ የሰው ትዳር የሚደፍሩ፣ አስፈራርተውና አስገድደው አህቶችና እናቶችን ከትዳራቸው የሚለዩ፣ ቤተሰብ የሚበትኑ፣ ቀና ብላችሁ ለምን አያችሁን በሚል እስከ ነፍስ ማጥፋት የሚደርሱ ማፍያዎች ፍርድ ቤቱንና የፍትህ ደጅ ዙሪያ ገባውን ቁልፍ ተረክበው አገሪቱን እየጋለቡዋት ነው የሚለው ዜና ተብሎ፣ ተብሎ ያለቀለት የማይሸፈን የአደባባይ ጉዳይ ነው።

“ግብር ለምን ክፈሉ እንባላለን” በሚል የስርዓቱን ቁንጮዎች በመያዝ ባለስልጣናትን ከሃላፊነታቸው የሚያስነሱ፣ ግብር የሚጠየቁበትን ሰነድ ቢሮ እያሰበሩ የሚዘርፉ፣ ሰነድ የሚያጠፉ፣ ለሰሩት ወንጀል በህግ ሲጠየቁ የህግ አካሄዱን በመመሪያ የሚያሳግዱ፣ በራሳቸው ፊርማና ማህተም “በትዕዛዝ ክስ አዘጋን” ብለው ለየጋዜጣው መግለጫ የሚበትኑ ወረበሎች ስለመበራከታቸው መለፍለፍ ከተጀመረ አንድ ጠ/ሚኒስትር አልፈው ሁለተኛው ተተክተዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ደብዳቤ እያጻፉና ትዕዛዝ እንዲተላለፍላቸው እያደረጉ የንግድ ውድድሩን ያዛቡ፣ ህግ አክብረው የሚሰሩትን ዜጎች ከገበያና ከውድድር እንዲገለሉ ያስደረጉ፣ ኢትዮጵያን “ለጠቅላይ “ሊጫወቱባት የሚዳዳቸው ወረበሎችን ያላካተተ የጸረ ሙስና ዘመቻ ከቶውንም ተቀባይነት እንደሌለው ህዝብ እያወጋ ነው።

የፍትህ ሚኒስትሩ ከሃላፊነት መነሳታቸውን ተከትሎ የፍርድ ሂደት ያዛቡ፣ መረጃ የቀረበባቸውን ክሶች ያሳገዱ፣ በመመሪያና በተለያዩ ንክኪዎች ህግ እንዲሰቀል ያደረጉ አቃብያነህግ እንደሚታሰሩ ሰምተናል። ምርመራው በሰነድ የተደገፈ ስለመሆኑ ይፋ ሆኗል። ይህንን ዜና የሰሙ “አዋራው ጨሰ፤ በህዝብ አቆጣጠር ጨዋታው ተጀመረ” እያሉ ነው።

ፍትህ ተጓድሎባቸው የአቤቱታ ፋይላቸው የተዘጋባቸው የጨዋታውን መጀመር ሲጠብቁ ነበር። በህይወት ጉዳይ ሻርኮቹን ከሰው ፋይላቸው የተቀረቀረባቸው አሉ። ሻርኮቹን በህግ በመጠየቃቸው ብቻ እስር ቤት የተቀረቀሩ አሉ። ፍትህ እንዲዛባ አድርገው የራሳቸውን ያልሆነ ንብረት የወሰዱ አሉ። ንብረታቸውን ተዘርፈው ልመና የወጡ አሉ። ሚስቶቻቸውን ተቀምተው እጃቸውን አጣጥፈው የተቀመጡ አሉ። ብዙ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል የሰሩና የሚጠየቁበትን ፋይል ያሳገዱ መጨረሻቸው ምን ይሆን? በግፍ የሞቱ ደማቸው ይጮሃል። በግፍ በልማት ስም ቤቷ የፈረሰባትና ለባለጊዜ ስፍራ የለቀቀች ደቃቃ እናት የጣር ድምጽ ይሰማል። ህግ ጎድሎባቸው፣ አቤት የሚሉበት ያጡ ወገኖች ሮሮ ከልክ አልፏል። በፖሊስ፣ በአቃቤ ህግ፣ በዳኛ፣ ከዛም በላይ በ”ተላላኪ ባለስልጣኖች” ትዕዛዝ መብቶቻቸውን የተገፈፉ የፍትህ ያለህ እያሉ ዓመታት አስቆጥረዋል።

አሁን በእኛ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። በህዝብ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። ኳሷ አደገኛ ቀጣና ውስጥ ናት። የተነቁ ፋይሎች፣ የታገዱ ጉዳዮች፣ የታደፈኑ የፍትህ ጉዳዮች ከልክ በላይ ናቸው። አሳፋኞቹም እዛው ኢህአዴግ ደጅ አረፍ እንዲሉ የተደረጉትን ጨምሮ በየደረጃው አሉ። አብረው የሚነግዱም አሉ። እነዚህን ሁሉ አልፈው መሔድ ከተቻለ ጨዋታው በትክክል በህዝብ የሰዓት አቆጣጠር ተጀምሯል። አለበለዚያ ግን የህዝብና የመንግስት አቆጣጠር ተለያይቷል። አንዱ ሲተኛ አንዱ ይነቃል። ሳይገናኙ ይተላለፋሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule