• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው ተጀመረ!

June 3, 2013 08:34 am by Editor Leave a Comment

ሙስናው ላይ የተጀመረው ዘመቻ ሙስናን በስንጥር የሚያሰኝ ቢሆንም አቶ መለስ ያልደፈሩትን ሰፈር አቶ ሃይለማርያም ነክተውታልና በኢህአዴግ ታሪክ የሙስናን ሰፈር በማንኳኳት ግንባር ቀደሙ ሰው ያደርጋቸዋል። እኛም ጅምሩ መልካም ነው እንላለን። ግን ጥያቄም ማሳሰቢያም አለን። ለማንኛውም በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው የተጀመረ ይመስለናል።

በሙስና የተጠረጠሩ ነጋዴዎች፣ ደላሎች፣ አቀባባይ የተባሉና የመንግስት ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ከተሰማ ጀምሮ ህዝብ በስፋት እየተቸ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የተደላደለውን ሙስና ህዝብ ጠንቅቆ ከነባለቤቶቹ ያውቃል። ይረዳል። ያሸታል። ባለፈ ባገደመ ቁጥር ለድህነቱ ማስታገሻ ያላምጣቸዋል።

ሙስና ሲባል ሙስና ነው። ወንጀል ሲባል ወንጀል ነው። ህግ መተላለፍ ያስጠይቃል። አሁን እንደሚታየው ግን የጸረ ሙስናው ዘመቻ ሰፈር የለየ ይመስላል። ዋናዎቹ “ሻርኮች” አልተነኩም። ዋናዎቹ “የማበስበሻው ባህር” ፊታውራሪዎች አሁንም እያገሱ ነው። እነዚህ አገር ወዳድ የሚመስሉ  የሙስና መፈልፈያ ማሽን አምራቾች ለምን ዝም ተባሉ? የህዝብ ጥያቄ ነው? የምስኪን ዜጎች ጥያቄ ነው። በተለይም “ጠቁሙኝ እርምጃ እወስዳለሁ” በማለት ለተናገሩት አዲሱ መሪ፡፡

በኢትዮጵያ በትዕዛዝ ንብረታቸውን የተነጠቁ፣ በደል ደርሶባቸው ፍርድ እናገኛለን ብለው ወደ ህግ አምርተው በትዕዛዝ የተበየነባቸው፣ በባለጊዜዎች መመሪያ ቅርስና ርስታቸውን የተነጠቁ፣ ተራ የቀበሌ ጭቃ ቤት ሳይቀር የተዘረፉ፣ የነፍስና የወንጀል ጉዳዮች ውስጥ መዘፈቃቸው እየታወቀ ክስ የማይመሰረትባቸውና በወንጀል ተጨማልቀው አገሪቱ ላይ የነገሱ ስለመኖራቸው መነገር ከጀመረ ያው የኢህአዴግን የስልጣን ዘመን ያክል ቆይቷል።

ፍርድና ርትዕ እንዲጓደል ብር ከባንክ በትዕዛዝ ተበድረው በፌስታል የሚረጩ፣ እዳ በሚጮህበት ሆቴሎቻቸው ውስጥ አልኮሆል እያራጩ “የገበያ ወሲብ” የሚያሻቅጡ፣ የሰው ትዳር የሚደፍሩ፣ አስፈራርተውና አስገድደው አህቶችና እናቶችን ከትዳራቸው የሚለዩ፣ ቤተሰብ የሚበትኑ፣ ቀና ብላችሁ ለምን አያችሁን በሚል እስከ ነፍስ ማጥፋት የሚደርሱ ማፍያዎች ፍርድ ቤቱንና የፍትህ ደጅ ዙሪያ ገባውን ቁልፍ ተረክበው አገሪቱን እየጋለቡዋት ነው የሚለው ዜና ተብሎ፣ ተብሎ ያለቀለት የማይሸፈን የአደባባይ ጉዳይ ነው።

“ግብር ለምን ክፈሉ እንባላለን” በሚል የስርዓቱን ቁንጮዎች በመያዝ ባለስልጣናትን ከሃላፊነታቸው የሚያስነሱ፣ ግብር የሚጠየቁበትን ሰነድ ቢሮ እያሰበሩ የሚዘርፉ፣ ሰነድ የሚያጠፉ፣ ለሰሩት ወንጀል በህግ ሲጠየቁ የህግ አካሄዱን በመመሪያ የሚያሳግዱ፣ በራሳቸው ፊርማና ማህተም “በትዕዛዝ ክስ አዘጋን” ብለው ለየጋዜጣው መግለጫ የሚበትኑ ወረበሎች ስለመበራከታቸው መለፍለፍ ከተጀመረ አንድ ጠ/ሚኒስትር አልፈው ሁለተኛው ተተክተዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ደብዳቤ እያጻፉና ትዕዛዝ እንዲተላለፍላቸው እያደረጉ የንግድ ውድድሩን ያዛቡ፣ ህግ አክብረው የሚሰሩትን ዜጎች ከገበያና ከውድድር እንዲገለሉ ያስደረጉ፣ ኢትዮጵያን “ለጠቅላይ “ሊጫወቱባት የሚዳዳቸው ወረበሎችን ያላካተተ የጸረ ሙስና ዘመቻ ከቶውንም ተቀባይነት እንደሌለው ህዝብ እያወጋ ነው።

የፍትህ ሚኒስትሩ ከሃላፊነት መነሳታቸውን ተከትሎ የፍርድ ሂደት ያዛቡ፣ መረጃ የቀረበባቸውን ክሶች ያሳገዱ፣ በመመሪያና በተለያዩ ንክኪዎች ህግ እንዲሰቀል ያደረጉ አቃብያነህግ እንደሚታሰሩ ሰምተናል። ምርመራው በሰነድ የተደገፈ ስለመሆኑ ይፋ ሆኗል። ይህንን ዜና የሰሙ “አዋራው ጨሰ፤ በህዝብ አቆጣጠር ጨዋታው ተጀመረ” እያሉ ነው።

ፍትህ ተጓድሎባቸው የአቤቱታ ፋይላቸው የተዘጋባቸው የጨዋታውን መጀመር ሲጠብቁ ነበር። በህይወት ጉዳይ ሻርኮቹን ከሰው ፋይላቸው የተቀረቀረባቸው አሉ። ሻርኮቹን በህግ በመጠየቃቸው ብቻ እስር ቤት የተቀረቀሩ አሉ። ፍትህ እንዲዛባ አድርገው የራሳቸውን ያልሆነ ንብረት የወሰዱ አሉ። ንብረታቸውን ተዘርፈው ልመና የወጡ አሉ። ሚስቶቻቸውን ተቀምተው እጃቸውን አጣጥፈው የተቀመጡ አሉ። ብዙ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል የሰሩና የሚጠየቁበትን ፋይል ያሳገዱ መጨረሻቸው ምን ይሆን? በግፍ የሞቱ ደማቸው ይጮሃል። በግፍ በልማት ስም ቤቷ የፈረሰባትና ለባለጊዜ ስፍራ የለቀቀች ደቃቃ እናት የጣር ድምጽ ይሰማል። ህግ ጎድሎባቸው፣ አቤት የሚሉበት ያጡ ወገኖች ሮሮ ከልክ አልፏል። በፖሊስ፣ በአቃቤ ህግ፣ በዳኛ፣ ከዛም በላይ በ”ተላላኪ ባለስልጣኖች” ትዕዛዝ መብቶቻቸውን የተገፈፉ የፍትህ ያለህ እያሉ ዓመታት አስቆጥረዋል።

አሁን በእኛ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። በህዝብ ሰዓት አቆጣጠር ጨዋታው ተጀምሯል። ኳሷ አደገኛ ቀጣና ውስጥ ናት። የተነቁ ፋይሎች፣ የታገዱ ጉዳዮች፣ የታደፈኑ የፍትህ ጉዳዮች ከልክ በላይ ናቸው። አሳፋኞቹም እዛው ኢህአዴግ ደጅ አረፍ እንዲሉ የተደረጉትን ጨምሮ በየደረጃው አሉ። አብረው የሚነግዱም አሉ። እነዚህን ሁሉ አልፈው መሔድ ከተቻለ ጨዋታው በትክክል በህዝብ የሰዓት አቆጣጠር ተጀምሯል። አለበለዚያ ግን የህዝብና የመንግስት አቆጣጠር ተለያይቷል። አንዱ ሲተኛ አንዱ ይነቃል። ሳይገናኙ ይተላለፋሉ።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule