• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መለኮታዊ ጥያቄ

September 26, 2016 11:34 pm by Editor Leave a Comment

“ኤርምያስ ሆይ ምን ታያለህ” (ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 1፡11)፡፡

እ.አ.አ 1519 ቤተሰቦች ልጆቻቸውን አሥርቱን ትእዛዛትና (አቡነ ዘሰማያት) በጥልቀት እንዲያጠኑ በማስተማራቸው (በርካታ ክርስቲያኖች በአውሮጳ) በእሳት ተቃጥለው ተገድለዋል፡፡ እ.አ.አ በ1536 ቲንደል የሚባል የእግዚአብሔር ሰው መጽሐፍ ቅዱስን ከላቲን ወደ እንግሊዘኛ በመተርጎሙ በእንጨት ላይ ታስሮ በእሳት ተቃጥሎ ተገድሎአል፡፡ ጆን ዊኪሊፍ መጽሐፍ ቅዱስን ከላቲን በመተርጎሙ ተወግዞአል፤ ከሞተ ከ44 ዓመት በኋላ አጥንቱ ወጥቶ እንዲቃጠል ተድርጎአል፡፡

እንዲህ ዓይነት እኩይ ድርጊት እንዲከናወን ያደረጉት የቤተ ክርስቲያን ጳጳሳትና ጨካኝ የሆኑ በዘመኑ የነበሩ የፖለቲካ ሰዎች አማካኝነት እንደሆነ ታሪክ ምስክር ነው፡፡

ከላይ የተመለከትነው እግዚአብሔር ነቢዩ ኤርምያስን የጠየቀበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው፡፡

አስተውሉ! ምንጊዜም፣ እግዚአብሔር ከመጠየቅ ወደ ኋላ ብሎ አያውቅም፡፡

ለመሆኑ እግዚአብሔር ለምን ይጠይቃል? የሰዎችን የልብ ዝንባሌ ለማወቅ ፈልጎ ይጠይቃል፡፡ ሆኖም እግዚአብሔር የሚጠይቀው ነገሩን ስለማያውቅ ሳይሆን መለኮታዊ መሥፈርትን ለማሳወቅ ይጠይቃል፡፡

እግዚአብሔር አዳምን “ወዴት ነህ? (ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 3፡8) ሲል ጠይቆት ነበር፡፡ ቀደም ሲል እንደተመለከትነው ነቢዩ ኤርምያስን፣ “ምን ታያለህ? (ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 1፡11) ሲል ጠይቆታል፡፡ ሙሴን ደግሞ፣ “በእጅህ ያለው ምንድነው? (ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ 4፡2) ሲል ጠይቆታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ሰዎች ስለ እርሱ ምን እንደሚሉ ጠይቆአቸው ነበር (የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 16፡13)፡፡

እግዚአብሔር ዛሬም ይጠይቃል!

እግዚአብሔር ለምን ይጠይቃል? ፍርድ ሲዛባ፣ አንዱ ብሔር በሌላው ብሔር ላይ ሲነሳ፣ ብርቱ ነኝ የሚል ደካማውን ሲገዛ፣ ጥቂቱ ብዙሃኑን ሲገዛ፣ በመንግሥታት መካከል ያለው ጥላቻ፣ ሽኩቻ፣ ይበልጥ እየሰፋና እያደገ ሲሄድ፣ ፍትሕ ጠፍቶ ማህበረሰብ ሲንከራተት፣ ሽብርተኝት ዓለምን ሲያናውጥ፣ ዓለም በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋ ስትጨነቅ፣ ዜጎች ምግብና መጠለያ አጥተው ሲንከራተቱ፣ መልካም አስተዳደር ሲጠፋ፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት በሙስና ሲጨማለቁ፣ እርግማን ከመጠን በላይ በዝቶ፣ የአየር መዛባት፣ በድርቅ ምክንያት በርካታዎች በረሃብ አለንጋ ሲረግፉ፣ ሲገረፉ፣ የአገዛዝ ቀንበር በሰዎች ላይ ሲከብድ፣ ስደት ከመቼውም ጊዜ በላይ በዝቶ፣ ትውልድ ሲጠፋ፣ የሰዎች ደም በየቦታው በከንቱ ሲፈስ፣ ለጋ ወጣቶች ከወላጆቻቸው ዘንድ ተሰድደው የዓሳ ቀለብ ሲሆኑ፣ በክፉ ሰዎች እጅ ወድቀው አንገታቸው ሲቀላ፣ በጥይት ተደብድበው ሲሞቱ፣ መጠለያና መጠጊያ አጥተው ሲንከራተቱ፣ በባዕድ አገራት በወህኒ ሲጣሉ፣ አገርና ወገን እንደሌላቸው ተቆጥረው በዓለም ላይ ተበትነው ሲንከራተቱ፣ የክፉ ሰዎች መጫወቻ፣ መሰደቢያ፣ መዘበቻና መዘባበቻ ሲሆኑ፣ጨካኝና አምባገነን መሪዎች ሕዝቦቻቸውን ሲያስጨንቁ፣ ሲያንገላቱ፣ ሲያስሩ፣ የዜግነት መብት ሲያሳጡ፣ አሁንም፣ ሁሌም እግዚአብሔር ይጠይቃል!!

እግዚአብሔር ዛሬም እንደ ቀድሞ ይጠይቃል!

“ምን ታያለህ”!!?

እውነቱን ለመናገር ጥያቄው ዛሬ ለእኔ ቢቀርብ፣ ምላሼ የሚከተለውን ይመስላል፡፡

እኔ የማየውና የምሰማው፣ የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የኮንሶ፣ የጋምቤላ፣ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ደም በከንቱ በየቦታው ሲፈስ፣ ወጣቶች ከየመንገዱና ከየቤቱ ታፍሰው በየወህኒ ቤት ሲታጎሩ፣ የጎንደርና የባሕር ዳር ልጆች ደም ሲፈስ፣ የወለጋ ልጆች ደም ሲፈስ፣ ልጆች ወላጅ አልባ ሲሆኑ፣ ወላጆች ጧሪ አጥተው ሲጨነቁ፣ በልቅሶ ብዛት ዓይናቸው ደክሞ ከሰውነት ተራ ወጥተው ሲጨነቁ፣ ባሕር ዳር ላይ የፈሰሰው የጨቅላ ወጣቶች ደም፣ በአወዳይ ላይ የፈሰሰው ንጹሕ ደም፤ በደምቢዶሎ የፈሰሰው የወጣቶች ደም፣ በነቀምቴ የፈሰሰው ንጹሕ ደም፣ ያለ ምንም ወንጀላቸው ሞት የተፈረደባቸው፣ በጨካኙ የወያኔ መንግሥት ዛቻ፣ ማስፈራሪያና ክትትል ምክንያት አገር የለቀቁ፣ ለስደት የተዳረጉ፣ ሰዎች ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው በመንከራተት ላይ የሚገኙትን ዜጎች፣ አጋዚ ተብሎ የሚጠራው የወያኔ ቀኝ እጅ ቅጥረኛና ነፍሰ ገዳይ ቡድን ብዙዎችን ሲገድል፣ ሲያፈናቅል፣ ሲያሳድድ …. አያለሁ፤ እያየሁ ነው፡፡

እናንተስ ምን እያያችሁ ይሆን? ምን እየሰማችሁ ነው?

እግዚብሔር ዛሬም ይጠይቃል!

ነገር ግን ሕዝቦች ሆይ! ታላቅ ተስፋ አለን፡፡ እግዚአብሔር እንደ መዥገር በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተጣበቁትን ወያኔዎች እስከ ወዲያኛው ያራግፍልናል፤ ይበትንልናል፡፡ ወያኔ ከተወገደ በኋላ ሥጋት፣ ጥላቻ፣ መለያየት፣ መገፋፋት፣ በብሔረሰቦች መካከል ያለው ሽኩቻ፣ ልዩነት፣ ዘረኝነት፣ ብሔርተኝነት፣ ጎጠኝነት የማይኖርባት ኢትዮጵያ ትኖረናለች፡፡ ሕዝቦች በመቻቻል፣ በመፈቃቀድ፣ በመከባበር፣ ፍትሐዊ የሆነ የሀብት ክፍፍል ኖሮአቸው፣ በመተባበር ላይ የተመሠረተ አንዲት ኢትዮጵያ ትኖረናለች፡፡

እውነተኛ የሆነ ዲሞክራሲ፣ ቅጥረኛ ያልሆነ የምርጫ ኮሚሽንና ሕዝብን የሚፈራና የሚያከብር የአገር መሪ ይኖረናል፡፡ መልካም አስተዳደር የሰፈነበት፣ ሙስና የማይኖርበት፣ ጥቂቱ ብዙሃኑን የማይገዛበት ሥርዓት ይመጣል!

የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እኩይ የሆኑ የኢትዮጵያ ጠላቶችን እስከ ወዲያኛው ሲያራግፋቸው ወያኔዎች ከተጠያቂነት ማምለጥ አይችሉም፡፡

የአቤል ደም ከምድር ወደ እግዚአብሔር እንደ ጮኸ ሁሉ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የኮንሶ፣ የጋምቤላ፣ የሶማሌና የሌሎችም ብሔረሰቦች ደም ወደ እግዚአብሔር በመጮኽ ላይ ይገኛል፡፡ እግዚአብሔር ሆይ ፍረድልን ይላሉ፡፡ ሰው የሚዘራው ያንኑ ያጭዳል፡፡ ስለዚህ ወያኔዎች ሞት ዘርተዋል፤ ሞት ያጭዳሉ፡፡ ክፉ ዘርተዋል፤ ክፉ ያጭዳሉ፡፡ ንጹሐንን በወህኒ አጉረዋል፤ እነርሱም አንድ ቀን በወህኒ ይታጎራሉ፡፡

እግዚአብሔር ዛሬም፣ ነገም፣ ሁሌም፣ … ይጠይቃል!!

ደጉ ዘመን ከአዲስ አበባ – ኢትዮጵያ

E-mail: deguzemen@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule