• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መለኮታዊ ጥያቄ

September 26, 2016 11:34 pm by Editor Leave a Comment

“ኤርምያስ ሆይ ምን ታያለህ” (ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 1፡11)፡፡

እ.አ.አ 1519 ቤተሰቦች ልጆቻቸውን አሥርቱን ትእዛዛትና (አቡነ ዘሰማያት) በጥልቀት እንዲያጠኑ በማስተማራቸው (በርካታ ክርስቲያኖች በአውሮጳ) በእሳት ተቃጥለው ተገድለዋል፡፡ እ.አ.አ በ1536 ቲንደል የሚባል የእግዚአብሔር ሰው መጽሐፍ ቅዱስን ከላቲን ወደ እንግሊዘኛ በመተርጎሙ በእንጨት ላይ ታስሮ በእሳት ተቃጥሎ ተገድሎአል፡፡ ጆን ዊኪሊፍ መጽሐፍ ቅዱስን ከላቲን በመተርጎሙ ተወግዞአል፤ ከሞተ ከ44 ዓመት በኋላ አጥንቱ ወጥቶ እንዲቃጠል ተድርጎአል፡፡

እንዲህ ዓይነት እኩይ ድርጊት እንዲከናወን ያደረጉት የቤተ ክርስቲያን ጳጳሳትና ጨካኝ የሆኑ በዘመኑ የነበሩ የፖለቲካ ሰዎች አማካኝነት እንደሆነ ታሪክ ምስክር ነው፡፡

ከላይ የተመለከትነው እግዚአብሔር ነቢዩ ኤርምያስን የጠየቀበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው፡፡

አስተውሉ! ምንጊዜም፣ እግዚአብሔር ከመጠየቅ ወደ ኋላ ብሎ አያውቅም፡፡

ለመሆኑ እግዚአብሔር ለምን ይጠይቃል? የሰዎችን የልብ ዝንባሌ ለማወቅ ፈልጎ ይጠይቃል፡፡ ሆኖም እግዚአብሔር የሚጠይቀው ነገሩን ስለማያውቅ ሳይሆን መለኮታዊ መሥፈርትን ለማሳወቅ ይጠይቃል፡፡

እግዚአብሔር አዳምን “ወዴት ነህ? (ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 3፡8) ሲል ጠይቆት ነበር፡፡ ቀደም ሲል እንደተመለከትነው ነቢዩ ኤርምያስን፣ “ምን ታያለህ? (ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 1፡11) ሲል ጠይቆታል፡፡ ሙሴን ደግሞ፣ “በእጅህ ያለው ምንድነው? (ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ 4፡2) ሲል ጠይቆታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ሰዎች ስለ እርሱ ምን እንደሚሉ ጠይቆአቸው ነበር (የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 16፡13)፡፡

እግዚአብሔር ዛሬም ይጠይቃል!

እግዚአብሔር ለምን ይጠይቃል? ፍርድ ሲዛባ፣ አንዱ ብሔር በሌላው ብሔር ላይ ሲነሳ፣ ብርቱ ነኝ የሚል ደካማውን ሲገዛ፣ ጥቂቱ ብዙሃኑን ሲገዛ፣ በመንግሥታት መካከል ያለው ጥላቻ፣ ሽኩቻ፣ ይበልጥ እየሰፋና እያደገ ሲሄድ፣ ፍትሕ ጠፍቶ ማህበረሰብ ሲንከራተት፣ ሽብርተኝት ዓለምን ሲያናውጥ፣ ዓለም በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋ ስትጨነቅ፣ ዜጎች ምግብና መጠለያ አጥተው ሲንከራተቱ፣ መልካም አስተዳደር ሲጠፋ፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት በሙስና ሲጨማለቁ፣ እርግማን ከመጠን በላይ በዝቶ፣ የአየር መዛባት፣ በድርቅ ምክንያት በርካታዎች በረሃብ አለንጋ ሲረግፉ፣ ሲገረፉ፣ የአገዛዝ ቀንበር በሰዎች ላይ ሲከብድ፣ ስደት ከመቼውም ጊዜ በላይ በዝቶ፣ ትውልድ ሲጠፋ፣ የሰዎች ደም በየቦታው በከንቱ ሲፈስ፣ ለጋ ወጣቶች ከወላጆቻቸው ዘንድ ተሰድደው የዓሳ ቀለብ ሲሆኑ፣ በክፉ ሰዎች እጅ ወድቀው አንገታቸው ሲቀላ፣ በጥይት ተደብድበው ሲሞቱ፣ መጠለያና መጠጊያ አጥተው ሲንከራተቱ፣ በባዕድ አገራት በወህኒ ሲጣሉ፣ አገርና ወገን እንደሌላቸው ተቆጥረው በዓለም ላይ ተበትነው ሲንከራተቱ፣ የክፉ ሰዎች መጫወቻ፣ መሰደቢያ፣ መዘበቻና መዘባበቻ ሲሆኑ፣ጨካኝና አምባገነን መሪዎች ሕዝቦቻቸውን ሲያስጨንቁ፣ ሲያንገላቱ፣ ሲያስሩ፣ የዜግነት መብት ሲያሳጡ፣ አሁንም፣ ሁሌም እግዚአብሔር ይጠይቃል!!

እግዚአብሔር ዛሬም እንደ ቀድሞ ይጠይቃል!

“ምን ታያለህ”!!?

እውነቱን ለመናገር ጥያቄው ዛሬ ለእኔ ቢቀርብ፣ ምላሼ የሚከተለውን ይመስላል፡፡

እኔ የማየውና የምሰማው፣ የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የኮንሶ፣ የጋምቤላ፣ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ደም በከንቱ በየቦታው ሲፈስ፣ ወጣቶች ከየመንገዱና ከየቤቱ ታፍሰው በየወህኒ ቤት ሲታጎሩ፣ የጎንደርና የባሕር ዳር ልጆች ደም ሲፈስ፣ የወለጋ ልጆች ደም ሲፈስ፣ ልጆች ወላጅ አልባ ሲሆኑ፣ ወላጆች ጧሪ አጥተው ሲጨነቁ፣ በልቅሶ ብዛት ዓይናቸው ደክሞ ከሰውነት ተራ ወጥተው ሲጨነቁ፣ ባሕር ዳር ላይ የፈሰሰው የጨቅላ ወጣቶች ደም፣ በአወዳይ ላይ የፈሰሰው ንጹሕ ደም፤ በደምቢዶሎ የፈሰሰው የወጣቶች ደም፣ በነቀምቴ የፈሰሰው ንጹሕ ደም፣ ያለ ምንም ወንጀላቸው ሞት የተፈረደባቸው፣ በጨካኙ የወያኔ መንግሥት ዛቻ፣ ማስፈራሪያና ክትትል ምክንያት አገር የለቀቁ፣ ለስደት የተዳረጉ፣ ሰዎች ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው በመንከራተት ላይ የሚገኙትን ዜጎች፣ አጋዚ ተብሎ የሚጠራው የወያኔ ቀኝ እጅ ቅጥረኛና ነፍሰ ገዳይ ቡድን ብዙዎችን ሲገድል፣ ሲያፈናቅል፣ ሲያሳድድ …. አያለሁ፤ እያየሁ ነው፡፡

እናንተስ ምን እያያችሁ ይሆን? ምን እየሰማችሁ ነው?

እግዚብሔር ዛሬም ይጠይቃል!

ነገር ግን ሕዝቦች ሆይ! ታላቅ ተስፋ አለን፡፡ እግዚአብሔር እንደ መዥገር በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተጣበቁትን ወያኔዎች እስከ ወዲያኛው ያራግፍልናል፤ ይበትንልናል፡፡ ወያኔ ከተወገደ በኋላ ሥጋት፣ ጥላቻ፣ መለያየት፣ መገፋፋት፣ በብሔረሰቦች መካከል ያለው ሽኩቻ፣ ልዩነት፣ ዘረኝነት፣ ብሔርተኝነት፣ ጎጠኝነት የማይኖርባት ኢትዮጵያ ትኖረናለች፡፡ ሕዝቦች በመቻቻል፣ በመፈቃቀድ፣ በመከባበር፣ ፍትሐዊ የሆነ የሀብት ክፍፍል ኖሮአቸው፣ በመተባበር ላይ የተመሠረተ አንዲት ኢትዮጵያ ትኖረናለች፡፡

እውነተኛ የሆነ ዲሞክራሲ፣ ቅጥረኛ ያልሆነ የምርጫ ኮሚሽንና ሕዝብን የሚፈራና የሚያከብር የአገር መሪ ይኖረናል፡፡ መልካም አስተዳደር የሰፈነበት፣ ሙስና የማይኖርበት፣ ጥቂቱ ብዙሃኑን የማይገዛበት ሥርዓት ይመጣል!

የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እኩይ የሆኑ የኢትዮጵያ ጠላቶችን እስከ ወዲያኛው ሲያራግፋቸው ወያኔዎች ከተጠያቂነት ማምለጥ አይችሉም፡፡

የአቤል ደም ከምድር ወደ እግዚአብሔር እንደ ጮኸ ሁሉ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የኮንሶ፣ የጋምቤላ፣ የሶማሌና የሌሎችም ብሔረሰቦች ደም ወደ እግዚአብሔር በመጮኽ ላይ ይገኛል፡፡ እግዚአብሔር ሆይ ፍረድልን ይላሉ፡፡ ሰው የሚዘራው ያንኑ ያጭዳል፡፡ ስለዚህ ወያኔዎች ሞት ዘርተዋል፤ ሞት ያጭዳሉ፡፡ ክፉ ዘርተዋል፤ ክፉ ያጭዳሉ፡፡ ንጹሐንን በወህኒ አጉረዋል፤ እነርሱም አንድ ቀን በወህኒ ይታጎራሉ፡፡

እግዚአብሔር ዛሬም፣ ነገም፣ ሁሌም፣ … ይጠይቃል!!

ደጉ ዘመን ከአዲስ አበባ – ኢትዮጵያ

E-mail: deguzemen@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule