• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የምናውቀውን አብይ እንፈልጋለን!

August 18, 2018 08:05 am by Editor 1 Comment

“ህልም በሥራ ብዛት ይታያል። እንዲሁም የሰነፍ ድምፅ በቃሉ ብዛት ይሰማል”

“ብዙ ህልም ባለበት ዘንድ እንዲሁም ደግሞ ብዙ ቃል ባለበት ሥፍራ በዚያ ብዙ ከንቱ ነገር አለ።” መፅሀፈ መክብብ ምዕ 5 ቁጥር 3 እና 7

አስቀድሞ ቃል ተነገረ፤ ቃሉም የአብይ ነበረ፤ ቃሉም ኢትዮጵያዊነትን ከወደቀበት ማንሳት ነበረ፤ ቃሉም በእኛ ዘንድ ህያው ሆነ፤ እነሆ ኢትዮጵያዊነትን ከመሪዋ ጎን ቆመን ከፍ አደረግን፤ ከአፅናፍ አፅናፍ ሆ! ብለን ተነሳን፤ በያደባባዩ ተመምን፤ መሪያችንን አብይን እንደ ጨው በተበተንባት ምድር ሁሉ ስሙን ጠራን፤ እነሆ ኢትዮጵያ መሪዋን ሙሴን አገኘች ስንል ብሥራት ተናገርን፤ እርሱም አላሳፈረንም፤ ሙሴነቱን እጃችንን ይዞን አቅፎንና ስሞን እንባችንንም አብሶና ደሙንም ለግሶን አልቅሶና አንሰቅስቆን ከሰቆቃና ከግርፋት ከእስርና ከስደት ነፃ አውጥቶን ወደ ነገይቷ ኢትዮጵያ መንገድ በመደመር ጉዞ መጋቢት 24 ቀን 2010 አስጀምሮን እስከ ሐምሌ መገባደጃው ከጎናችን ለቅፅበት ሳይጠፋ፤ ስንጀግን እየተደሰተ፤ ስናጠፋ እየወቀሰ፤ ስናኮርፍ እየመከረ፤ ስንበድል ይቅር እያለ፤ ወደ ሁዋላ ስናፈገፍግ እያበረታን፤ ስንቃወመውም እያዳመጠን ማዕበሉን እየቀዘፈና ባሻገርም እየተመለከተ ከጎናችንና ከፊታችን ከቶም ሳናጣውና ሳይጠፋብን ሳይርቀንና ሳንራራቅ መራን። ለአራት ወር ገደማ የምናውቀውና የሚያውቀን አብይ መሪያችን ይህ ነው።

ከእኛ ጋር ለመነጋገር፤ ችግራችንን ለመስማት በደላችንን ለመጋራት፤ ሀዘናችንን ለማፅናናት የምናውቀው መሪያችን አብይ ቀጠሮ አይዝም። ሀገር ስትታመስ፤ ገንጣይ ሲረባረብ፤  የዕምነት ቤቶች ሲጋዩ፤ ቀሳውስት ሲፈጁ፤ የሚወደው ህዝብ በጭንቅ ማጥ ውስጥ ገብቶ ሲዳክር፤ መውጫ መግቢያው ሲጨንቀው የምናውቀው አብይ ዝም አይልም። የምናውቀው አብይ ከተፎ ነው። በፈገግታ በታጀበ ፊቱ ፍካትን ፍቅርንና መቻቻልን እየናኘ፤ እንደ ሌሊት ተወርዋሪ ኮከብ በሚበራው አይኑ ብርሃንን ተስፋንና ዕምነትን እያሳየ አቧራ የቃመ ፀጉራችንን፤ እድፍ የተሸከመ ልብሳችንን የሻከረ እጃችንን ሳይጠየፍ የሚዳስሰን ሳይቀፈው የሚያቅፈንና የሚጨብጠን የምናውቀው ሙሴያችን አብይ መሪያችን የሩቅ ሰው ከሆነብን ሰነበተ። የምናውቀው አብይ መሪያችን የቅርብ እሩቅ ሆነብን። ብዙ መናገር ወይም ብዙ መፃፍ በወደድን። ሆኖም አሁን ላይ የኢትዮጵያን ህመም በብዕር ምጥ በቃላት ንግግርም ለዘመናት ሲያስተጋቡ የኖሩ ‘የታወቀ’ ስም ወይም የፖለቲካ ድርጅት ሥልጣን የሌላቸው ከመፃፍም ሆነ ከመናገርም ለመታቀብ የተገደዱበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ እኛም የዚሁ አካል ነንና ከዚህ በላይ ብዙም አንል። የኢትዮጵያ ጭንቅ የሚያስጨንቀው ሁሉ ግና ይገባዋልና እንግባባለን።

ይህ የመደመር ጉዞ ጠቢቡ መክብብ ‘ብዙ ቃል ባለበት ሥፍራ ብዙ ከንቱ ነገር አለ’ እንዳለው ዛሬ በኢትዮጵያችን በተለይም አብያችን ከአሜሪካ ጉዞው ከተመለስ ወዲህ  አብይ በሌለበት ምድሪቱ በብዙ ከንቱና አብያዊ ጉዟችንን በሚያጨናግፉ ዲስኩሮችና የድል አጥቢያ አርበኝነት አባዜ ተወርራለች። ከቦሌ እስከ ሚለንየም አዳራሽ የሚሰማው ፉከራና ትርምስ አስደንግጦናል። የሁሉም ተቃዋሚ ‘ተፎካካሪ’ ድርጅት/ፓርቲ ዝግጅት ለዚህ ከቦሌ እስከ ሚለንየም አዳራሽ ለሚደረግ የአቀባበልና የዲስኩር ‘ገድል’ ሆኗልና ወይም ይመስላልና። ኢትዮጵያንና አብይን እንዴት ‘እንታደግ?’ የሚል ዝግጅትና መንፈስ የውይይትና የተግባር መድረክም አይታይም። ሁሉም ለየራሱ ገድልና ታሪክ ጥድፊያ ላይ ነው!! ከወዲያ ማዶም ነጋሪቱ ከጥቂት ወራት በፊት ባልታየ ድምፀት በህወሃት አጋፋሪዎች እየተጎሰመብንና እየተፎከረብን ይገኛል። በዚህ ሁሉ ሆያሆዬ የምናውቀው አብይ ከጎናችን የለም። አለ ብለው ከቤተመንግሥት በአፈቀላጤዎቹ በኩል (እንደ በፊቱ በቀጥታ አይደለም) የሚያሳዩን የፎቶ ምስሉን እንጂ የምናውቀውንና የሚያውቀንን አብረን የተጓዝነውን ሰዋዊውን አብይ መሪያችንን አብይ ወንድማችንን አብይ ልጃችንን አይደለም።

እኛ ቀቢፀ ተስፈኞች አይደለንም። በሃያ ሰባት አመት የስደትና የፅናት ዘመን፤ ለአንዲትም ደቂቃ ለህወሃትና ህወሃታውያን ለጎጠኞችና ለሀገር በታኞች አጎብድደን አልያም ተመሳስለን ኖረን አናውቅም። የሴራ ፖለቲካም የእኛ ቁማር አይደለም። አብይን የደገፍነው ጎርፉ ሲያስገመግምም አይደለም። ‘አያያዙን አይተህ ጭብጦውን ቀማው’ እንዲሉ እኒያ አብናቶቻችን የለማንና የአብይን ጉዞ ገና ከጠዋቱ በአደባባይ የደገፍነው አያያዝና አካሄዱን ለይተንና አይተን  የህወሃትን ‘ጭብጦ’ (ሥልጣን) ለመንጠቅም ብቸኛው መንገድ የእነርሱ መሆኑን ተረድተን እንጂ። እና እኛ ሴረኞች ወይም የሴራ ፖለቲካ አራማጆች አይደለንም። በነፈሰበትም አንወዛወዝም። ግን ደግሞ ሰሞኑን ከምኒሊክ ቤተ መንግሥት የሚተላለፈውን ‘ድብብቆሽ’ ለማወቅና ለመረዳት ደግሞ የህይወት ተሞክሮ ብቻ በቂ ነው። ከዚህ በላይ ብዙ ማለት አያሻንም። እና ድብብቆሹ ይብቃ!!! አብይ ናፍቆናል!! የምናውቀውን አብይ ማግኘትና ማነጋገር እንፈልጋለን!!! ወደ ጨለማው ዘመን እንዳንመለስ ከተፈለገ አብይ፤ የምናውቀው አብይ፤ በነፃነት የሚፍለቀለቀው አብይ አደባባይ ወጥቶ እንዲመራንና ከጎኑም እንድንቆም በነፃነት ልናገኘው እንፈልጋለን!!! የሚሰማ ጆሮ የሚያስተውል ልብ ያለው ይስማ ያስተውልም!! ጊዜው ሳይሄድ ምልሽ እንፈልጋለንና!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይባርክ!

ነሀሴ 2010 ዓ/ም
ኦገስት 2018
ሲድኒ አውስትራሊያ
mmtessema@gmail.com 


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Adoniyas says

    August 23, 2018 12:15 am at 12:15 am

    ይቺ ሃገር ቀዳዳዋ ብዙ ነው ብሏል እሱ ራሱ
    ….ስማ የውልህ አብይን በረባ ባልረባው በመቅረጸ መስኮት መጠበቁን ብንተው ነው የሚሻለን ብዙ ከማውራት ትንሽ ዝም ብሎ መስራት ያዋጣል ስሜታችንን ሁልጊዜ እያከከ መኖር አይችልም ፡፡ መስራት ማደራጀት መምራት አለበት፡፡ እንደሚታወቀው በአሁን ጊዜ ከውስጥ በኩል ከፍተኛ የማጨናገፍ ግፊት እየተደረገበት ነው ለእያንዳንዱ ነገር መልስ ለእኛ መስጠት አይኖርበትም እንደ መንግስት የሚሰሩ አሰራሮች አሉ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule