• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የምናውቀውን አብይ እንፈልጋለን!

August 18, 2018 08:05 am by Editor 1 Comment

“ህልም በሥራ ብዛት ይታያል። እንዲሁም የሰነፍ ድምፅ በቃሉ ብዛት ይሰማል”

“ብዙ ህልም ባለበት ዘንድ እንዲሁም ደግሞ ብዙ ቃል ባለበት ሥፍራ በዚያ ብዙ ከንቱ ነገር አለ።” መፅሀፈ መክብብ ምዕ 5 ቁጥር 3 እና 7

አስቀድሞ ቃል ተነገረ፤ ቃሉም የአብይ ነበረ፤ ቃሉም ኢትዮጵያዊነትን ከወደቀበት ማንሳት ነበረ፤ ቃሉም በእኛ ዘንድ ህያው ሆነ፤ እነሆ ኢትዮጵያዊነትን ከመሪዋ ጎን ቆመን ከፍ አደረግን፤ ከአፅናፍ አፅናፍ ሆ! ብለን ተነሳን፤ በያደባባዩ ተመምን፤ መሪያችንን አብይን እንደ ጨው በተበተንባት ምድር ሁሉ ስሙን ጠራን፤ እነሆ ኢትዮጵያ መሪዋን ሙሴን አገኘች ስንል ብሥራት ተናገርን፤ እርሱም አላሳፈረንም፤ ሙሴነቱን እጃችንን ይዞን አቅፎንና ስሞን እንባችንንም አብሶና ደሙንም ለግሶን አልቅሶና አንሰቅስቆን ከሰቆቃና ከግርፋት ከእስርና ከስደት ነፃ አውጥቶን ወደ ነገይቷ ኢትዮጵያ መንገድ በመደመር ጉዞ መጋቢት 24 ቀን 2010 አስጀምሮን እስከ ሐምሌ መገባደጃው ከጎናችን ለቅፅበት ሳይጠፋ፤ ስንጀግን እየተደሰተ፤ ስናጠፋ እየወቀሰ፤ ስናኮርፍ እየመከረ፤ ስንበድል ይቅር እያለ፤ ወደ ሁዋላ ስናፈገፍግ እያበረታን፤ ስንቃወመውም እያዳመጠን ማዕበሉን እየቀዘፈና ባሻገርም እየተመለከተ ከጎናችንና ከፊታችን ከቶም ሳናጣውና ሳይጠፋብን ሳይርቀንና ሳንራራቅ መራን። ለአራት ወር ገደማ የምናውቀውና የሚያውቀን አብይ መሪያችን ይህ ነው።

ከእኛ ጋር ለመነጋገር፤ ችግራችንን ለመስማት በደላችንን ለመጋራት፤ ሀዘናችንን ለማፅናናት የምናውቀው መሪያችን አብይ ቀጠሮ አይዝም። ሀገር ስትታመስ፤ ገንጣይ ሲረባረብ፤  የዕምነት ቤቶች ሲጋዩ፤ ቀሳውስት ሲፈጁ፤ የሚወደው ህዝብ በጭንቅ ማጥ ውስጥ ገብቶ ሲዳክር፤ መውጫ መግቢያው ሲጨንቀው የምናውቀው አብይ ዝም አይልም። የምናውቀው አብይ ከተፎ ነው። በፈገግታ በታጀበ ፊቱ ፍካትን ፍቅርንና መቻቻልን እየናኘ፤ እንደ ሌሊት ተወርዋሪ ኮከብ በሚበራው አይኑ ብርሃንን ተስፋንና ዕምነትን እያሳየ አቧራ የቃመ ፀጉራችንን፤ እድፍ የተሸከመ ልብሳችንን የሻከረ እጃችንን ሳይጠየፍ የሚዳስሰን ሳይቀፈው የሚያቅፈንና የሚጨብጠን የምናውቀው ሙሴያችን አብይ መሪያችን የሩቅ ሰው ከሆነብን ሰነበተ። የምናውቀው አብይ መሪያችን የቅርብ እሩቅ ሆነብን። ብዙ መናገር ወይም ብዙ መፃፍ በወደድን። ሆኖም አሁን ላይ የኢትዮጵያን ህመም በብዕር ምጥ በቃላት ንግግርም ለዘመናት ሲያስተጋቡ የኖሩ ‘የታወቀ’ ስም ወይም የፖለቲካ ድርጅት ሥልጣን የሌላቸው ከመፃፍም ሆነ ከመናገርም ለመታቀብ የተገደዱበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ እኛም የዚሁ አካል ነንና ከዚህ በላይ ብዙም አንል። የኢትዮጵያ ጭንቅ የሚያስጨንቀው ሁሉ ግና ይገባዋልና እንግባባለን።

ይህ የመደመር ጉዞ ጠቢቡ መክብብ ‘ብዙ ቃል ባለበት ሥፍራ ብዙ ከንቱ ነገር አለ’ እንዳለው ዛሬ በኢትዮጵያችን በተለይም አብያችን ከአሜሪካ ጉዞው ከተመለስ ወዲህ  አብይ በሌለበት ምድሪቱ በብዙ ከንቱና አብያዊ ጉዟችንን በሚያጨናግፉ ዲስኩሮችና የድል አጥቢያ አርበኝነት አባዜ ተወርራለች። ከቦሌ እስከ ሚለንየም አዳራሽ የሚሰማው ፉከራና ትርምስ አስደንግጦናል። የሁሉም ተቃዋሚ ‘ተፎካካሪ’ ድርጅት/ፓርቲ ዝግጅት ለዚህ ከቦሌ እስከ ሚለንየም አዳራሽ ለሚደረግ የአቀባበልና የዲስኩር ‘ገድል’ ሆኗልና ወይም ይመስላልና። ኢትዮጵያንና አብይን እንዴት ‘እንታደግ?’ የሚል ዝግጅትና መንፈስ የውይይትና የተግባር መድረክም አይታይም። ሁሉም ለየራሱ ገድልና ታሪክ ጥድፊያ ላይ ነው!! ከወዲያ ማዶም ነጋሪቱ ከጥቂት ወራት በፊት ባልታየ ድምፀት በህወሃት አጋፋሪዎች እየተጎሰመብንና እየተፎከረብን ይገኛል። በዚህ ሁሉ ሆያሆዬ የምናውቀው አብይ ከጎናችን የለም። አለ ብለው ከቤተመንግሥት በአፈቀላጤዎቹ በኩል (እንደ በፊቱ በቀጥታ አይደለም) የሚያሳዩን የፎቶ ምስሉን እንጂ የምናውቀውንና የሚያውቀንን አብረን የተጓዝነውን ሰዋዊውን አብይ መሪያችንን አብይ ወንድማችንን አብይ ልጃችንን አይደለም።

እኛ ቀቢፀ ተስፈኞች አይደለንም። በሃያ ሰባት አመት የስደትና የፅናት ዘመን፤ ለአንዲትም ደቂቃ ለህወሃትና ህወሃታውያን ለጎጠኞችና ለሀገር በታኞች አጎብድደን አልያም ተመሳስለን ኖረን አናውቅም። የሴራ ፖለቲካም የእኛ ቁማር አይደለም። አብይን የደገፍነው ጎርፉ ሲያስገመግምም አይደለም። ‘አያያዙን አይተህ ጭብጦውን ቀማው’ እንዲሉ እኒያ አብናቶቻችን የለማንና የአብይን ጉዞ ገና ከጠዋቱ በአደባባይ የደገፍነው አያያዝና አካሄዱን ለይተንና አይተን  የህወሃትን ‘ጭብጦ’ (ሥልጣን) ለመንጠቅም ብቸኛው መንገድ የእነርሱ መሆኑን ተረድተን እንጂ። እና እኛ ሴረኞች ወይም የሴራ ፖለቲካ አራማጆች አይደለንም። በነፈሰበትም አንወዛወዝም። ግን ደግሞ ሰሞኑን ከምኒሊክ ቤተ መንግሥት የሚተላለፈውን ‘ድብብቆሽ’ ለማወቅና ለመረዳት ደግሞ የህይወት ተሞክሮ ብቻ በቂ ነው። ከዚህ በላይ ብዙ ማለት አያሻንም። እና ድብብቆሹ ይብቃ!!! አብይ ናፍቆናል!! የምናውቀውን አብይ ማግኘትና ማነጋገር እንፈልጋለን!!! ወደ ጨለማው ዘመን እንዳንመለስ ከተፈለገ አብይ፤ የምናውቀው አብይ፤ በነፃነት የሚፍለቀለቀው አብይ አደባባይ ወጥቶ እንዲመራንና ከጎኑም እንድንቆም በነፃነት ልናገኘው እንፈልጋለን!!! የሚሰማ ጆሮ የሚያስተውል ልብ ያለው ይስማ ያስተውልም!! ጊዜው ሳይሄድ ምልሽ እንፈልጋለንና!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይባርክ!

ነሀሴ 2010 ዓ/ም
ኦገስት 2018
ሲድኒ አውስትራሊያ
mmtessema@gmail.com 


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Adoniyas says

    August 23, 2018 12:15 am at 12:15 am

    ይቺ ሃገር ቀዳዳዋ ብዙ ነው ብሏል እሱ ራሱ
    ….ስማ የውልህ አብይን በረባ ባልረባው በመቅረጸ መስኮት መጠበቁን ብንተው ነው የሚሻለን ብዙ ከማውራት ትንሽ ዝም ብሎ መስራት ያዋጣል ስሜታችንን ሁልጊዜ እያከከ መኖር አይችልም ፡፡ መስራት ማደራጀት መምራት አለበት፡፡ እንደሚታወቀው በአሁን ጊዜ ከውስጥ በኩል ከፍተኛ የማጨናገፍ ግፊት እየተደረገበት ነው ለእያንዳንዱ ነገር መልስ ለእኛ መስጠት አይኖርበትም እንደ መንግስት የሚሰሩ አሰራሮች አሉ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule