• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የምናውቀውን አብይ እንፈልጋለን!

August 18, 2018 08:05 am by Editor 1 Comment

“ህልም በሥራ ብዛት ይታያል። እንዲሁም የሰነፍ ድምፅ በቃሉ ብዛት ይሰማል”

“ብዙ ህልም ባለበት ዘንድ እንዲሁም ደግሞ ብዙ ቃል ባለበት ሥፍራ በዚያ ብዙ ከንቱ ነገር አለ።” መፅሀፈ መክብብ ምዕ 5 ቁጥር 3 እና 7

አስቀድሞ ቃል ተነገረ፤ ቃሉም የአብይ ነበረ፤ ቃሉም ኢትዮጵያዊነትን ከወደቀበት ማንሳት ነበረ፤ ቃሉም በእኛ ዘንድ ህያው ሆነ፤ እነሆ ኢትዮጵያዊነትን ከመሪዋ ጎን ቆመን ከፍ አደረግን፤ ከአፅናፍ አፅናፍ ሆ! ብለን ተነሳን፤ በያደባባዩ ተመምን፤ መሪያችንን አብይን እንደ ጨው በተበተንባት ምድር ሁሉ ስሙን ጠራን፤ እነሆ ኢትዮጵያ መሪዋን ሙሴን አገኘች ስንል ብሥራት ተናገርን፤ እርሱም አላሳፈረንም፤ ሙሴነቱን እጃችንን ይዞን አቅፎንና ስሞን እንባችንንም አብሶና ደሙንም ለግሶን አልቅሶና አንሰቅስቆን ከሰቆቃና ከግርፋት ከእስርና ከስደት ነፃ አውጥቶን ወደ ነገይቷ ኢትዮጵያ መንገድ በመደመር ጉዞ መጋቢት 24 ቀን 2010 አስጀምሮን እስከ ሐምሌ መገባደጃው ከጎናችን ለቅፅበት ሳይጠፋ፤ ስንጀግን እየተደሰተ፤ ስናጠፋ እየወቀሰ፤ ስናኮርፍ እየመከረ፤ ስንበድል ይቅር እያለ፤ ወደ ሁዋላ ስናፈገፍግ እያበረታን፤ ስንቃወመውም እያዳመጠን ማዕበሉን እየቀዘፈና ባሻገርም እየተመለከተ ከጎናችንና ከፊታችን ከቶም ሳናጣውና ሳይጠፋብን ሳይርቀንና ሳንራራቅ መራን። ለአራት ወር ገደማ የምናውቀውና የሚያውቀን አብይ መሪያችን ይህ ነው።

ከእኛ ጋር ለመነጋገር፤ ችግራችንን ለመስማት በደላችንን ለመጋራት፤ ሀዘናችንን ለማፅናናት የምናውቀው መሪያችን አብይ ቀጠሮ አይዝም። ሀገር ስትታመስ፤ ገንጣይ ሲረባረብ፤  የዕምነት ቤቶች ሲጋዩ፤ ቀሳውስት ሲፈጁ፤ የሚወደው ህዝብ በጭንቅ ማጥ ውስጥ ገብቶ ሲዳክር፤ መውጫ መግቢያው ሲጨንቀው የምናውቀው አብይ ዝም አይልም። የምናውቀው አብይ ከተፎ ነው። በፈገግታ በታጀበ ፊቱ ፍካትን ፍቅርንና መቻቻልን እየናኘ፤ እንደ ሌሊት ተወርዋሪ ኮከብ በሚበራው አይኑ ብርሃንን ተስፋንና ዕምነትን እያሳየ አቧራ የቃመ ፀጉራችንን፤ እድፍ የተሸከመ ልብሳችንን የሻከረ እጃችንን ሳይጠየፍ የሚዳስሰን ሳይቀፈው የሚያቅፈንና የሚጨብጠን የምናውቀው ሙሴያችን አብይ መሪያችን የሩቅ ሰው ከሆነብን ሰነበተ። የምናውቀው አብይ መሪያችን የቅርብ እሩቅ ሆነብን። ብዙ መናገር ወይም ብዙ መፃፍ በወደድን። ሆኖም አሁን ላይ የኢትዮጵያን ህመም በብዕር ምጥ በቃላት ንግግርም ለዘመናት ሲያስተጋቡ የኖሩ ‘የታወቀ’ ስም ወይም የፖለቲካ ድርጅት ሥልጣን የሌላቸው ከመፃፍም ሆነ ከመናገርም ለመታቀብ የተገደዱበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ እኛም የዚሁ አካል ነንና ከዚህ በላይ ብዙም አንል። የኢትዮጵያ ጭንቅ የሚያስጨንቀው ሁሉ ግና ይገባዋልና እንግባባለን።

ይህ የመደመር ጉዞ ጠቢቡ መክብብ ‘ብዙ ቃል ባለበት ሥፍራ ብዙ ከንቱ ነገር አለ’ እንዳለው ዛሬ በኢትዮጵያችን በተለይም አብያችን ከአሜሪካ ጉዞው ከተመለስ ወዲህ  አብይ በሌለበት ምድሪቱ በብዙ ከንቱና አብያዊ ጉዟችንን በሚያጨናግፉ ዲስኩሮችና የድል አጥቢያ አርበኝነት አባዜ ተወርራለች። ከቦሌ እስከ ሚለንየም አዳራሽ የሚሰማው ፉከራና ትርምስ አስደንግጦናል። የሁሉም ተቃዋሚ ‘ተፎካካሪ’ ድርጅት/ፓርቲ ዝግጅት ለዚህ ከቦሌ እስከ ሚለንየም አዳራሽ ለሚደረግ የአቀባበልና የዲስኩር ‘ገድል’ ሆኗልና ወይም ይመስላልና። ኢትዮጵያንና አብይን እንዴት ‘እንታደግ?’ የሚል ዝግጅትና መንፈስ የውይይትና የተግባር መድረክም አይታይም። ሁሉም ለየራሱ ገድልና ታሪክ ጥድፊያ ላይ ነው!! ከወዲያ ማዶም ነጋሪቱ ከጥቂት ወራት በፊት ባልታየ ድምፀት በህወሃት አጋፋሪዎች እየተጎሰመብንና እየተፎከረብን ይገኛል። በዚህ ሁሉ ሆያሆዬ የምናውቀው አብይ ከጎናችን የለም። አለ ብለው ከቤተመንግሥት በአፈቀላጤዎቹ በኩል (እንደ በፊቱ በቀጥታ አይደለም) የሚያሳዩን የፎቶ ምስሉን እንጂ የምናውቀውንና የሚያውቀንን አብረን የተጓዝነውን ሰዋዊውን አብይ መሪያችንን አብይ ወንድማችንን አብይ ልጃችንን አይደለም።

እኛ ቀቢፀ ተስፈኞች አይደለንም። በሃያ ሰባት አመት የስደትና የፅናት ዘመን፤ ለአንዲትም ደቂቃ ለህወሃትና ህወሃታውያን ለጎጠኞችና ለሀገር በታኞች አጎብድደን አልያም ተመሳስለን ኖረን አናውቅም። የሴራ ፖለቲካም የእኛ ቁማር አይደለም። አብይን የደገፍነው ጎርፉ ሲያስገመግምም አይደለም። ‘አያያዙን አይተህ ጭብጦውን ቀማው’ እንዲሉ እኒያ አብናቶቻችን የለማንና የአብይን ጉዞ ገና ከጠዋቱ በአደባባይ የደገፍነው አያያዝና አካሄዱን ለይተንና አይተን  የህወሃትን ‘ጭብጦ’ (ሥልጣን) ለመንጠቅም ብቸኛው መንገድ የእነርሱ መሆኑን ተረድተን እንጂ። እና እኛ ሴረኞች ወይም የሴራ ፖለቲካ አራማጆች አይደለንም። በነፈሰበትም አንወዛወዝም። ግን ደግሞ ሰሞኑን ከምኒሊክ ቤተ መንግሥት የሚተላለፈውን ‘ድብብቆሽ’ ለማወቅና ለመረዳት ደግሞ የህይወት ተሞክሮ ብቻ በቂ ነው። ከዚህ በላይ ብዙ ማለት አያሻንም። እና ድብብቆሹ ይብቃ!!! አብይ ናፍቆናል!! የምናውቀውን አብይ ማግኘትና ማነጋገር እንፈልጋለን!!! ወደ ጨለማው ዘመን እንዳንመለስ ከተፈለገ አብይ፤ የምናውቀው አብይ፤ በነፃነት የሚፍለቀለቀው አብይ አደባባይ ወጥቶ እንዲመራንና ከጎኑም እንድንቆም በነፃነት ልናገኘው እንፈልጋለን!!! የሚሰማ ጆሮ የሚያስተውል ልብ ያለው ይስማ ያስተውልም!! ጊዜው ሳይሄድ ምልሽ እንፈልጋለንና!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይባርክ!

ነሀሴ 2010 ዓ/ም
ኦገስት 2018
ሲድኒ አውስትራሊያ
mmtessema@gmail.com 


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Adoniyas says

    August 23, 2018 12:15 am at 12:15 am

    ይቺ ሃገር ቀዳዳዋ ብዙ ነው ብሏል እሱ ራሱ
    ….ስማ የውልህ አብይን በረባ ባልረባው በመቅረጸ መስኮት መጠበቁን ብንተው ነው የሚሻለን ብዙ ከማውራት ትንሽ ዝም ብሎ መስራት ያዋጣል ስሜታችንን ሁልጊዜ እያከከ መኖር አይችልም ፡፡ መስራት ማደራጀት መምራት አለበት፡፡ እንደሚታወቀው በአሁን ጊዜ ከውስጥ በኩል ከፍተኛ የማጨናገፍ ግፊት እየተደረገበት ነው ለእያንዳንዱ ነገር መልስ ለእኛ መስጠት አይኖርበትም እንደ መንግስት የሚሰሩ አሰራሮች አሉ፡፡

    Reply

Leave a Reply to Adoniyas Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ May 16, 2022 03:07 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule