• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጀርመናዊው የገደላት ሰብለ ከአንድ አመት በኋላ በመኖርያ ቤትዋ ተቀብራ ተገኘች

July 19, 2015 10:38 pm by Editor Leave a Comment

ሰብለ (ሚሚ) ዲትሪች ለመጨረሻ ግዜ የታየችው እ.ኤ. አ. ጁላይ 10 2014 (ባለፈው አመት) ነበር።  የሶስት ልጆች እናት የነበረች  የዚህች ኢትዮጵያዊት በድንገት መሰወር ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ ሰንብቷል።  ለአመት የጠፋችው ይህች ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሴት በህይወት እንደማትኖር በርካቶች ቢጠረጥሩም፣ ማንንም ሳታማክር በድብቅ ወደ ሃገርዋ ገብታለች የሚሉ አልጠፉም።  አለም አቀፍ ፖሊስ በአለም ዙርያ ፍለጋውን ተያያዘው።

በካናዳ ኪችነር ከተማ ቫንኮቨር ድራይቭ የተገኘው አጽም ግን የሁሉንም እንቆቅልሽ ፈታው። ሰብለ ህይወትዋ አልፏል።  የሶስት ልጆችዋ አባት የነበረው ጀርመናዊው ስቴፋን ዲትሪች ገድሎ እዚያው መኖርያ ቤታቸው እንደቀበራት ፖሊስ ጠቁሟል።  በፖሊስ እና በሰለጠኑ ውሾች ጥቆማ የተገኘው የሰብለ አስከሬን በቶሮንቶ ኮርነርስ ኮምፕለክስ ለጥናት ተልኮ የተገኘው ውጤት ሰብለ በሰው እንደተገደለች ተረጋግጧል። ዋናው ተጠርጣሪም ጀርመናዊው ባለበትዋ ነው።

በመጀመርያ ደረጃ የግድያ ወንጀል የተከሰሰው የሚሚ ባለቤት ስቴፋን  ዲትሪች ፍርድ ቤት ቀርቦ በሰጠው ቃል ጉዳዩ በጀርመን ሃገር እንዲታይለት ጠይቋል። በእለቱ ኢትዮጵያውያን ፍርድ ቤቱን አጥለቅልቀውት ነበር።

ሰብለ ዲትሪች ተገድላ ከተሰወረች ከአመት በኋላ የቀብር ስርዓትዋ እለተ አርብ (ጁላይ 18) በካናዳ ቅዱስ ፓውሎስ ቤተ ክርስትያን ተፈጽሟል። በቀብሩ ላይ ወላጅ እናትዋን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል።

seble funeralስቴፋን  ዲትሪች የአዞ እንባ እያነባ ምስጢሩን ለአመት ከደበቀው በኋላ መኖርያ ቤቱን ለመሸጥ ማስታወቅያ አውጥቶ ነበር። ይህ ድርጊቱ የፖሊስን ጥርጣሬ እንዳጎላው ግልጽ ነው።

ሰብለ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ነበረች። የቤተ ክርስትያኑ ዘማሪም ናት። ባልዋ ዲትሪችም እንደዚሁ። ከጀርመን ሃገር ወደ ካናዳ ከተዘዋወሩ በሁዋላ እጅግ በጣም የተደላደለ ኑሮ እንደነበራቸው ይነገራል።  ሰብለ ከኢትዮጵያውያን የቤተ-ክርስትያን ሰዎች በተለይ ከፓስተሮች ጋር የምታደርገው የአገልግሎት ግንኙነት ግን ለስቴፋን ዲትሪች እንዳልተመቸው የሚመሰክሩ አሉ።  ይህም ቢሆን ክቡር ነብስን ለማጥፋት ምክንያት ሊሆን አይችልም። …. ስቴፋን ዲትሪች ሰብለን ለምን ገደላት? ገድሎስ ለምን ቤቱ ቀበራት? ይህንን ከፍርድ ቤቱ ሂደት የምናየው ይሆናል።

የሰብለ እናት የካናዳ የመኖርያ ፈቃድ አግኝተው የመጡ ሲሆን ሶስት ልጆቹን እሳቸው እንደሚንከባከቧቸው ከካናዳ መንግስት መረጃ አግኝቻለሁ።

Filed Under: News, Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule