• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምህን ሳላነሳ፣ የተወጋ አይረሳ!

July 17, 2017 05:43 am by Editor 2 Comments

ስምህን ሳላነሳ፣ ምኑን ሆንከው ፀጋ
ለአብሮነት መኖር፣ እየሆንክ አደጋ፣
አድርገህ ከያዝከው፣ የሙሉቀን ሥራ
ለማቃባት ደም፣ ኦሮሞን ካማራ።

‘ጀሃዳዊ ሃረካት’፣ እና ‘አኬል ዳማ’
በለምለሟ አርሲ፣ በአኖሊ ከተማ
ወያኔ ያቆመው፣ የጥላቻ ሃውልት
የተሸከመው እጅ፣ የተቆረጠ ጡት
ሆነ ውጤት አልባ፣ አነሰ አሉህ እንዴ
አሽከርካሪዎችህ፣ ፍጠር ሌላ ዘዴ?
ጦርና ጎራዴ
ሕዝቡን ለማማዘዝ
ድንገት ቱግ ብለህ፣ የምትረጨው መርዝ።
ዕውቀት ነበርኮ፣ ወገንን ለመጥቀም
ተከባብሮ እንዲኖር፣ ተዋዶ በሰላም
አየ ያንተስ መማር፣ “በረከተ መርገም”!!

ተስፋ ለቆረጠ፣ ቀን ለጨለመበት
ለጭቁን ወገኑ፣ መላ ለጠፋበት
ታጭዶ ለሚወቃው፣ በአግዓዚ ጥይት
በአላሚ እሩምታ፣ በቅሊንጦ ታጥሮ
ዶጋመድ ለሆነው፣ በሳት ተንጨርጭሮ
ፍዳውን ለሚያየው፣ እሥር ቤት ታጉሮ
እርቃኑን ለቀረው፣ በግብር በግቦ
በኑሮ ውድነት፣ ለሚያድረው ተርቦ
ለተሸማቀቀው፣ ፍትህ ሰጥታው ጀርባ
ለተከናነበው፣ የስቆቃ ካባ
ባይታወር ለሆነው፣ በቀየው በደጁ
መከራውን አይቶ፣ ያስተማረው ልጁ
አንገቱን ቀና አርጎ
እንባውን ጠራርጎ
አለሁህ ካላለው፣ ካልተጋፈጠለት
ክፍል ቆጠረ እንጂ፣ አልገበየም ዕውቀት።

ስምህን ሳላነሳ
ሁሉም ስለሚያውቅህ፣ የተወጋ አይረሳ፤
ኧረ ለመሆኑ፣ ምን አለ ያንተ አባት
ሚስቱን እናትህን፣ ዋጋ ስታሳጣት?!
ስታብጠለጥላት፣ አይንቁ ስትንቃት
ፍፁም ስትነፍጋት፣ የናትነት ክብር
ቆልለህ ስትቀብራት፣ በወንጀል ክምር
ስለተወለደች፣ ከአማራ ዘር?
ግን – እንደወንጀለኛ መቆጠር ካለባት
ይገባታል ቢባል፣ ዋጋ ግምት ማጣት
ትወቅ ጉዷን ቢባል፣ ተገምድሎ ፍርዷ
አበቃ አጥፍታለች፣ አንተን በመውለዷ!!
እንደሚባለው፣ ፍየል ወልዳ እሣት
ትልሰው ትተወው፣ እንደቸገራት
ዕድሏ ሆነና፣ ያንተም እናት ጉዳይ
በምንም ቢለካ፣ ከዚህ ምሳሌ አይለይ።

ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ በስቃይ አምጣ፣
በሞትና ሽረት፣ መካከል ተንጣ
ወልዳ አሳድጋ፣ ትምህርት አስተምራ
ጠላት ስታደርጋት፣ በመሆኗ አማራ!
ያሰኛል – ምነው አጥንት ሆነህ፣ በቀረህላት
ከሆዷ ሳትወጣ፣ ሳትወልድህ በፊት።
አለች አይባልም፣ ካለች በሕይወት
ሳትሞት በቁሟ፣ ስለቀበርካት።
አወይ መታደሏ፣እንደሆነም ሙታ
ማህፀኗን ከምትረግም፣ የምትላትን ሰምታ።

እስኪ ልጠይቅህ ስምህን ሳላነሳ
አንተም ታውቀዋለህ፣ የተወጋ አይረሳ፣
ያባትህ ስም ትርጉም፣ ከሆነ “አስታራቂ”
አልከበደህም ወይ፣ ስትሆን “አራራቂ”?

ከእንግዲህ ወዲህ፣ በአንተ ምክንያት
ግሥ ይሁን ያንተ ስም፣ መግለጫ “ክህደት”
የሱ ስም ያላችሁ፣ ባዲስ ስም ተጠሩ
ወገን ከሚያራርቅ፣ ስም ከምትጋሩ።

ትርጉሙ ምንድን ነው፣ ከቶ ያንተ ሥደት
ዘረኛ እስከሆንክ፣ ልክ እንደሕወሃት?
ምንድን ይሆን ጠብህ፣ ከወያኔ ጋር
እኩል ከጠላኸው፣ የአማራን ዘር?

ቢሸፍንህ እንጂ፣ ቢገልጽልህማ
አማራና ኦሮሞን፣ ማን ነበር ያስማማ፣
በሁለንተናው ውስጥ፣ እንዳንተ አዋህዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ማንነት ተገምዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ፍቅረኞች ተወልዶ።

የፈጀውን ቢፈጅ፣ ቢውልም ቢያድር
በሁለቱ ሕዝቦች፣ ጥብቅ ትሥስር
ሕዝባዊ አመፁ፣ ሲደርስ ከዳር
ማፈርህ አይቀርም፣ ጌታህ ሲገረሰስ
ተቆርቋሪ መሳይ፣ አንት “የትሮይ ፈረስ”።

ስምህን ሳላነሳ
የተወጋ አይረሳ!

(ከይሜ ወረደሮ) yworedero@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aytalnew Newzendro says

    August 31, 2017 09:52 pm at 9:52 pm

    It is really sad that some Ethiopian elites prolonging the suffering of their people by raising questions that does not reflect the situation on the ground. If Ethiopia disintegrates, these elites may be presidents, ambassadors of their tiny states but that does not necessarily benefit the interest of their people whom they claim to represent.

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    December 30, 2017 11:52 pm at 11:52 pm

    ጸጋየ አራርሳ እኮ የሰራው ወንጀል ካለ ይዘክዘክ! ጥያቄው ግን ሌላውን የሚጎዳ አልነበረም:: የብሄሩን መብትና እኩልነት እንጂ ያብራራ መሰለኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule