• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምህን ሳላነሳ፣ የተወጋ አይረሳ!

July 17, 2017 05:43 am by Editor 2 Comments

ስምህን ሳላነሳ፣ ምኑን ሆንከው ፀጋ
ለአብሮነት መኖር፣ እየሆንክ አደጋ፣
አድርገህ ከያዝከው፣ የሙሉቀን ሥራ
ለማቃባት ደም፣ ኦሮሞን ካማራ።

‘ጀሃዳዊ ሃረካት’፣ እና ‘አኬል ዳማ’
በለምለሟ አርሲ፣ በአኖሊ ከተማ
ወያኔ ያቆመው፣ የጥላቻ ሃውልት
የተሸከመው እጅ፣ የተቆረጠ ጡት
ሆነ ውጤት አልባ፣ አነሰ አሉህ እንዴ
አሽከርካሪዎችህ፣ ፍጠር ሌላ ዘዴ?
ጦርና ጎራዴ
ሕዝቡን ለማማዘዝ
ድንገት ቱግ ብለህ፣ የምትረጨው መርዝ።
ዕውቀት ነበርኮ፣ ወገንን ለመጥቀም
ተከባብሮ እንዲኖር፣ ተዋዶ በሰላም
አየ ያንተስ መማር፣ “በረከተ መርገም”!!

ተስፋ ለቆረጠ፣ ቀን ለጨለመበት
ለጭቁን ወገኑ፣ መላ ለጠፋበት
ታጭዶ ለሚወቃው፣ በአግዓዚ ጥይት
በአላሚ እሩምታ፣ በቅሊንጦ ታጥሮ
ዶጋመድ ለሆነው፣ በሳት ተንጨርጭሮ
ፍዳውን ለሚያየው፣ እሥር ቤት ታጉሮ
እርቃኑን ለቀረው፣ በግብር በግቦ
በኑሮ ውድነት፣ ለሚያድረው ተርቦ
ለተሸማቀቀው፣ ፍትህ ሰጥታው ጀርባ
ለተከናነበው፣ የስቆቃ ካባ
ባይታወር ለሆነው፣ በቀየው በደጁ
መከራውን አይቶ፣ ያስተማረው ልጁ
አንገቱን ቀና አርጎ
እንባውን ጠራርጎ
አለሁህ ካላለው፣ ካልተጋፈጠለት
ክፍል ቆጠረ እንጂ፣ አልገበየም ዕውቀት።

ስምህን ሳላነሳ
ሁሉም ስለሚያውቅህ፣ የተወጋ አይረሳ፤
ኧረ ለመሆኑ፣ ምን አለ ያንተ አባት
ሚስቱን እናትህን፣ ዋጋ ስታሳጣት?!
ስታብጠለጥላት፣ አይንቁ ስትንቃት
ፍፁም ስትነፍጋት፣ የናትነት ክብር
ቆልለህ ስትቀብራት፣ በወንጀል ክምር
ስለተወለደች፣ ከአማራ ዘር?
ግን – እንደወንጀለኛ መቆጠር ካለባት
ይገባታል ቢባል፣ ዋጋ ግምት ማጣት
ትወቅ ጉዷን ቢባል፣ ተገምድሎ ፍርዷ
አበቃ አጥፍታለች፣ አንተን በመውለዷ!!
እንደሚባለው፣ ፍየል ወልዳ እሣት
ትልሰው ትተወው፣ እንደቸገራት
ዕድሏ ሆነና፣ ያንተም እናት ጉዳይ
በምንም ቢለካ፣ ከዚህ ምሳሌ አይለይ።

ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ በስቃይ አምጣ፣
በሞትና ሽረት፣ መካከል ተንጣ
ወልዳ አሳድጋ፣ ትምህርት አስተምራ
ጠላት ስታደርጋት፣ በመሆኗ አማራ!
ያሰኛል – ምነው አጥንት ሆነህ፣ በቀረህላት
ከሆዷ ሳትወጣ፣ ሳትወልድህ በፊት።
አለች አይባልም፣ ካለች በሕይወት
ሳትሞት በቁሟ፣ ስለቀበርካት።
አወይ መታደሏ፣እንደሆነም ሙታ
ማህፀኗን ከምትረግም፣ የምትላትን ሰምታ።

እስኪ ልጠይቅህ ስምህን ሳላነሳ
አንተም ታውቀዋለህ፣ የተወጋ አይረሳ፣
ያባትህ ስም ትርጉም፣ ከሆነ “አስታራቂ”
አልከበደህም ወይ፣ ስትሆን “አራራቂ”?

ከእንግዲህ ወዲህ፣ በአንተ ምክንያት
ግሥ ይሁን ያንተ ስም፣ መግለጫ “ክህደት”
የሱ ስም ያላችሁ፣ ባዲስ ስም ተጠሩ
ወገን ከሚያራርቅ፣ ስም ከምትጋሩ።

ትርጉሙ ምንድን ነው፣ ከቶ ያንተ ሥደት
ዘረኛ እስከሆንክ፣ ልክ እንደሕወሃት?
ምንድን ይሆን ጠብህ፣ ከወያኔ ጋር
እኩል ከጠላኸው፣ የአማራን ዘር?

ቢሸፍንህ እንጂ፣ ቢገልጽልህማ
አማራና ኦሮሞን፣ ማን ነበር ያስማማ፣
በሁለንተናው ውስጥ፣ እንዳንተ አዋህዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ማንነት ተገምዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ፍቅረኞች ተወልዶ።

የፈጀውን ቢፈጅ፣ ቢውልም ቢያድር
በሁለቱ ሕዝቦች፣ ጥብቅ ትሥስር
ሕዝባዊ አመፁ፣ ሲደርስ ከዳር
ማፈርህ አይቀርም፣ ጌታህ ሲገረሰስ
ተቆርቋሪ መሳይ፣ አንት “የትሮይ ፈረስ”።

ስምህን ሳላነሳ
የተወጋ አይረሳ!

(ከይሜ ወረደሮ) yworedero@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aytalnew Newzendro says

    August 31, 2017 09:52 pm at 9:52 pm

    It is really sad that some Ethiopian elites prolonging the suffering of their people by raising questions that does not reflect the situation on the ground. If Ethiopia disintegrates, these elites may be presidents, ambassadors of their tiny states but that does not necessarily benefit the interest of their people whom they claim to represent.

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    December 30, 2017 11:52 pm at 11:52 pm

    ጸጋየ አራርሳ እኮ የሰራው ወንጀል ካለ ይዘክዘክ! ጥያቄው ግን ሌላውን የሚጎዳ አልነበረም:: የብሄሩን መብትና እኩልነት እንጂ ያብራራ መሰለኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule