• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምህን ሳላነሳ፣ የተወጋ አይረሳ!

July 17, 2017 05:43 am by Editor 2 Comments

ስምህን ሳላነሳ፣ ምኑን ሆንከው ፀጋ
ለአብሮነት መኖር፣ እየሆንክ አደጋ፣
አድርገህ ከያዝከው፣ የሙሉቀን ሥራ
ለማቃባት ደም፣ ኦሮሞን ካማራ።

‘ጀሃዳዊ ሃረካት’፣ እና ‘አኬል ዳማ’
በለምለሟ አርሲ፣ በአኖሊ ከተማ
ወያኔ ያቆመው፣ የጥላቻ ሃውልት
የተሸከመው እጅ፣ የተቆረጠ ጡት
ሆነ ውጤት አልባ፣ አነሰ አሉህ እንዴ
አሽከርካሪዎችህ፣ ፍጠር ሌላ ዘዴ?
ጦርና ጎራዴ
ሕዝቡን ለማማዘዝ
ድንገት ቱግ ብለህ፣ የምትረጨው መርዝ።
ዕውቀት ነበርኮ፣ ወገንን ለመጥቀም
ተከባብሮ እንዲኖር፣ ተዋዶ በሰላም
አየ ያንተስ መማር፣ “በረከተ መርገም”!!

ተስፋ ለቆረጠ፣ ቀን ለጨለመበት
ለጭቁን ወገኑ፣ መላ ለጠፋበት
ታጭዶ ለሚወቃው፣ በአግዓዚ ጥይት
በአላሚ እሩምታ፣ በቅሊንጦ ታጥሮ
ዶጋመድ ለሆነው፣ በሳት ተንጨርጭሮ
ፍዳውን ለሚያየው፣ እሥር ቤት ታጉሮ
እርቃኑን ለቀረው፣ በግብር በግቦ
በኑሮ ውድነት፣ ለሚያድረው ተርቦ
ለተሸማቀቀው፣ ፍትህ ሰጥታው ጀርባ
ለተከናነበው፣ የስቆቃ ካባ
ባይታወር ለሆነው፣ በቀየው በደጁ
መከራውን አይቶ፣ ያስተማረው ልጁ
አንገቱን ቀና አርጎ
እንባውን ጠራርጎ
አለሁህ ካላለው፣ ካልተጋፈጠለት
ክፍል ቆጠረ እንጂ፣ አልገበየም ዕውቀት።

ስምህን ሳላነሳ
ሁሉም ስለሚያውቅህ፣ የተወጋ አይረሳ፤
ኧረ ለመሆኑ፣ ምን አለ ያንተ አባት
ሚስቱን እናትህን፣ ዋጋ ስታሳጣት?!
ስታብጠለጥላት፣ አይንቁ ስትንቃት
ፍፁም ስትነፍጋት፣ የናትነት ክብር
ቆልለህ ስትቀብራት፣ በወንጀል ክምር
ስለተወለደች፣ ከአማራ ዘር?
ግን – እንደወንጀለኛ መቆጠር ካለባት
ይገባታል ቢባል፣ ዋጋ ግምት ማጣት
ትወቅ ጉዷን ቢባል፣ ተገምድሎ ፍርዷ
አበቃ አጥፍታለች፣ አንተን በመውለዷ!!
እንደሚባለው፣ ፍየል ወልዳ እሣት
ትልሰው ትተወው፣ እንደቸገራት
ዕድሏ ሆነና፣ ያንተም እናት ጉዳይ
በምንም ቢለካ፣ ከዚህ ምሳሌ አይለይ።

ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ በስቃይ አምጣ፣
በሞትና ሽረት፣ መካከል ተንጣ
ወልዳ አሳድጋ፣ ትምህርት አስተምራ
ጠላት ስታደርጋት፣ በመሆኗ አማራ!
ያሰኛል – ምነው አጥንት ሆነህ፣ በቀረህላት
ከሆዷ ሳትወጣ፣ ሳትወልድህ በፊት።
አለች አይባልም፣ ካለች በሕይወት
ሳትሞት በቁሟ፣ ስለቀበርካት።
አወይ መታደሏ፣እንደሆነም ሙታ
ማህፀኗን ከምትረግም፣ የምትላትን ሰምታ።

እስኪ ልጠይቅህ ስምህን ሳላነሳ
አንተም ታውቀዋለህ፣ የተወጋ አይረሳ፣
ያባትህ ስም ትርጉም፣ ከሆነ “አስታራቂ”
አልከበደህም ወይ፣ ስትሆን “አራራቂ”?

ከእንግዲህ ወዲህ፣ በአንተ ምክንያት
ግሥ ይሁን ያንተ ስም፣ መግለጫ “ክህደት”
የሱ ስም ያላችሁ፣ ባዲስ ስም ተጠሩ
ወገን ከሚያራርቅ፣ ስም ከምትጋሩ።

ትርጉሙ ምንድን ነው፣ ከቶ ያንተ ሥደት
ዘረኛ እስከሆንክ፣ ልክ እንደሕወሃት?
ምንድን ይሆን ጠብህ፣ ከወያኔ ጋር
እኩል ከጠላኸው፣ የአማራን ዘር?

ቢሸፍንህ እንጂ፣ ቢገልጽልህማ
አማራና ኦሮሞን፣ ማን ነበር ያስማማ፣
በሁለንተናው ውስጥ፣ እንዳንተ አዋህዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ማንነት ተገምዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ፍቅረኞች ተወልዶ።

የፈጀውን ቢፈጅ፣ ቢውልም ቢያድር
በሁለቱ ሕዝቦች፣ ጥብቅ ትሥስር
ሕዝባዊ አመፁ፣ ሲደርስ ከዳር
ማፈርህ አይቀርም፣ ጌታህ ሲገረሰስ
ተቆርቋሪ መሳይ፣ አንት “የትሮይ ፈረስ”።

ስምህን ሳላነሳ
የተወጋ አይረሳ!

(ከይሜ ወረደሮ) yworedero@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aytalnew Newzendro says

    August 31, 2017 09:52 pm at 9:52 pm

    It is really sad that some Ethiopian elites prolonging the suffering of their people by raising questions that does not reflect the situation on the ground. If Ethiopia disintegrates, these elites may be presidents, ambassadors of their tiny states but that does not necessarily benefit the interest of their people whom they claim to represent.

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    December 30, 2017 11:52 pm at 11:52 pm

    ጸጋየ አራርሳ እኮ የሰራው ወንጀል ካለ ይዘክዘክ! ጥያቄው ግን ሌላውን የሚጎዳ አልነበረም:: የብሄሩን መብትና እኩልነት እንጂ ያብራራ መሰለኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule