• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምህን ሳላነሳ፣ የተወጋ አይረሳ!

July 17, 2017 05:43 am by Editor 2 Comments

ስምህን ሳላነሳ፣ ምኑን ሆንከው ፀጋ
ለአብሮነት መኖር፣ እየሆንክ አደጋ፣
አድርገህ ከያዝከው፣ የሙሉቀን ሥራ
ለማቃባት ደም፣ ኦሮሞን ካማራ።

‘ጀሃዳዊ ሃረካት’፣ እና ‘አኬል ዳማ’
በለምለሟ አርሲ፣ በአኖሊ ከተማ
ወያኔ ያቆመው፣ የጥላቻ ሃውልት
የተሸከመው እጅ፣ የተቆረጠ ጡት
ሆነ ውጤት አልባ፣ አነሰ አሉህ እንዴ
አሽከርካሪዎችህ፣ ፍጠር ሌላ ዘዴ?
ጦርና ጎራዴ
ሕዝቡን ለማማዘዝ
ድንገት ቱግ ብለህ፣ የምትረጨው መርዝ።
ዕውቀት ነበርኮ፣ ወገንን ለመጥቀም
ተከባብሮ እንዲኖር፣ ተዋዶ በሰላም
አየ ያንተስ መማር፣ “በረከተ መርገም”!!

ተስፋ ለቆረጠ፣ ቀን ለጨለመበት
ለጭቁን ወገኑ፣ መላ ለጠፋበት
ታጭዶ ለሚወቃው፣ በአግዓዚ ጥይት
በአላሚ እሩምታ፣ በቅሊንጦ ታጥሮ
ዶጋመድ ለሆነው፣ በሳት ተንጨርጭሮ
ፍዳውን ለሚያየው፣ እሥር ቤት ታጉሮ
እርቃኑን ለቀረው፣ በግብር በግቦ
በኑሮ ውድነት፣ ለሚያድረው ተርቦ
ለተሸማቀቀው፣ ፍትህ ሰጥታው ጀርባ
ለተከናነበው፣ የስቆቃ ካባ
ባይታወር ለሆነው፣ በቀየው በደጁ
መከራውን አይቶ፣ ያስተማረው ልጁ
አንገቱን ቀና አርጎ
እንባውን ጠራርጎ
አለሁህ ካላለው፣ ካልተጋፈጠለት
ክፍል ቆጠረ እንጂ፣ አልገበየም ዕውቀት።

ስምህን ሳላነሳ
ሁሉም ስለሚያውቅህ፣ የተወጋ አይረሳ፤
ኧረ ለመሆኑ፣ ምን አለ ያንተ አባት
ሚስቱን እናትህን፣ ዋጋ ስታሳጣት?!
ስታብጠለጥላት፣ አይንቁ ስትንቃት
ፍፁም ስትነፍጋት፣ የናትነት ክብር
ቆልለህ ስትቀብራት፣ በወንጀል ክምር
ስለተወለደች፣ ከአማራ ዘር?
ግን – እንደወንጀለኛ መቆጠር ካለባት
ይገባታል ቢባል፣ ዋጋ ግምት ማጣት
ትወቅ ጉዷን ቢባል፣ ተገምድሎ ፍርዷ
አበቃ አጥፍታለች፣ አንተን በመውለዷ!!
እንደሚባለው፣ ፍየል ወልዳ እሣት
ትልሰው ትተወው፣ እንደቸገራት
ዕድሏ ሆነና፣ ያንተም እናት ጉዳይ
በምንም ቢለካ፣ ከዚህ ምሳሌ አይለይ።

ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ በስቃይ አምጣ፣
በሞትና ሽረት፣ መካከል ተንጣ
ወልዳ አሳድጋ፣ ትምህርት አስተምራ
ጠላት ስታደርጋት፣ በመሆኗ አማራ!
ያሰኛል – ምነው አጥንት ሆነህ፣ በቀረህላት
ከሆዷ ሳትወጣ፣ ሳትወልድህ በፊት።
አለች አይባልም፣ ካለች በሕይወት
ሳትሞት በቁሟ፣ ስለቀበርካት።
አወይ መታደሏ፣እንደሆነም ሙታ
ማህፀኗን ከምትረግም፣ የምትላትን ሰምታ።

እስኪ ልጠይቅህ ስምህን ሳላነሳ
አንተም ታውቀዋለህ፣ የተወጋ አይረሳ፣
ያባትህ ስም ትርጉም፣ ከሆነ “አስታራቂ”
አልከበደህም ወይ፣ ስትሆን “አራራቂ”?

ከእንግዲህ ወዲህ፣ በአንተ ምክንያት
ግሥ ይሁን ያንተ ስም፣ መግለጫ “ክህደት”
የሱ ስም ያላችሁ፣ ባዲስ ስም ተጠሩ
ወገን ከሚያራርቅ፣ ስም ከምትጋሩ።

ትርጉሙ ምንድን ነው፣ ከቶ ያንተ ሥደት
ዘረኛ እስከሆንክ፣ ልክ እንደሕወሃት?
ምንድን ይሆን ጠብህ፣ ከወያኔ ጋር
እኩል ከጠላኸው፣ የአማራን ዘር?

ቢሸፍንህ እንጂ፣ ቢገልጽልህማ
አማራና ኦሮሞን፣ ማን ነበር ያስማማ፣
በሁለንተናው ውስጥ፣ እንዳንተ አዋህዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ማንነት ተገምዶ
ካማራ ከኦሮሞ፣ ፍቅረኞች ተወልዶ።

የፈጀውን ቢፈጅ፣ ቢውልም ቢያድር
በሁለቱ ሕዝቦች፣ ጥብቅ ትሥስር
ሕዝባዊ አመፁ፣ ሲደርስ ከዳር
ማፈርህ አይቀርም፣ ጌታህ ሲገረሰስ
ተቆርቋሪ መሳይ፣ አንት “የትሮይ ፈረስ”።

ስምህን ሳላነሳ
የተወጋ አይረሳ!

(ከይሜ ወረደሮ) yworedero@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aytalnew Newzendro says

    August 31, 2017 09:52 pm at 9:52 pm

    It is really sad that some Ethiopian elites prolonging the suffering of their people by raising questions that does not reflect the situation on the ground. If Ethiopia disintegrates, these elites may be presidents, ambassadors of their tiny states but that does not necessarily benefit the interest of their people whom they claim to represent.

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    December 30, 2017 11:52 pm at 11:52 pm

    ጸጋየ አራርሳ እኮ የሰራው ወንጀል ካለ ይዘክዘክ! ጥያቄው ግን ሌላውን የሚጎዳ አልነበረም:: የብሄሩን መብትና እኩልነት እንጂ ያብራራ መሰለኝ!!!

    Reply

Leave a Reply to Mulugeta Andargie Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule