ፕ/ር አስራት አስራት ወልደየስን ሞተ ያለው ማነው? በረከቱን ያጣ የሞተ መለስ ነው፣ ፕ/ር አስራት አልሞተም ውሸት ነው፣ ኢትዮጵያን ሲቆርሷት ቁጭብየ እንደ ግርማ አላይም ነው ያለው፣ ታሞነው የሞተው? ማነው የገደለው? ያለ ይመስለኛል ስሙን ቀይረውት አለማየሁ ብለው፡፡ ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል … [Read more...] about ሞተ ያለው ማነው?
“ኦባማ መጀን” ወይስ “በእውቀት” መደራጀት?
የአሜሪካ ምርጫ ሲጠናቀቅ ተሸናፊው ሚት ሮምኒ ደጋፊዎቻቸው በተሰበሰቡበት አዳራሽ ምስጋና ካቀረቡ በኋላ እንዲህ አሉ፡- “… ሁለታችንም ለምንወዳት አገራችን የምንመኘውን ለማድረግ በተለያየ አቅጣጫ ሞከርን፤ … ሕዝባችን ደግሞ የሚፈልገውን መሪ መረጠ፤ … ስለዚህ ፕሬዚዳንቱን ደውዬ አነጋሬያቸዋለሁ፤ ባገኙትም ድል እንኳን ደስ አለዎ ብያቸዋለሁ፤ … በተለይ ለእርሳቸው፣ ለቀዳማዊ እመቤት እና ለልጆቻቸው ሁሉ መልካሙን እመኛለሁ፤ … አገራችን ከባድ ፈተናዎች ተጋርጠውባታል፤ … ባለቤቴና እኔ ለፕሬዚዳንቱና ቤተሰባቸው ከልብ እንጸልያለን፤ በሥራቸው ስኬት እንዲያገኙና ታላቋን አገራችንን በመምራት የሚያከናውኑት ሁሉ የተሳካ እንዲሁን እመኛለሁ፡፡” ይህንን ካሉ በኋላ ወደተለመደው ህይወታቸው ሄዱ - የፖለቲካ ገዳም ገቡ፡፡ ይህ ንግግር ወደራሳችን እንድንመለከት የሚያደርግ ነው፡፡ የእኛስ ፖለቲከኞች … [Read more...] about “ኦባማ መጀን” ወይስ “በእውቀት” መደራጀት?
ወ/ሮ አዜብ የባለቤታቸውን ምስጢር ይፋ አደረጉ
“የሙስና መርከብ” በሚል ስያሜ የሚጠሩት አሉ። ከተቋቋመ ጀምሮ አንድም ቀን ስለንብረቱ መጠን ለህዝብ ተገልጾ አያውቅም። ከአገሪቱ ባንኮች ትልቁ ተበዳሪ ነው።የወጋጋን ባንክ ትልቁ ባለድርሻ ነው። በአንዳንድ ከፍተኛ የንግድ ተቋማት ውስጥ የንግድ ሽርክና እንዳለው ይታማል። የወርቅ ማዕድን ፍለጋው ሰምሮለታል። የግል አስመጪዎችን በመፈታተን አነካክቶ ጥሏቸዋል። አገሪቱ ላይ የገነባው የንግድ ኢምፓየር በበርካቶች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል። በሌሎች ክልሎች በተመሳሳይ የተቋቋሙትን የንግድ ተቋማት በመደፍጠጥ በፖለቲካው የበላይነቱ ሳቢያ ልዩ ተጠቃሚ በመሆኑ አይወደድም። ይህ ታላቅ የህወሃት የንግድ ግዛት ኤፈርት ነው። የትግራይ ህዝብ “ያንተ ነው” ስለሚባለው ታላቅ የንግድ ኢምፓየር የሚያውቀው ነገር እምብዛም የለም። አስራ ሶስት ሰፋፊና ስትራቴጂክ ኩባንያዎችን ያቀፈው ኤፈርት በቅርቡ የእህት … [Read more...] about ወ/ሮ አዜብ የባለቤታቸውን ምስጢር ይፋ አደረጉ
ከፖለቲካ ተሃድሶ በፊት [የእውቀት] ተሃድሶ በአስቸኳይ!!
ታዋቂው የጋና ምሁር ጆርጅ አዪቴ በተደጋጋሚ እንደሚሉት ከአምባገነናዊ ስርዓት ወደ ዴሞክራሲ በሚደረገው ሽግግር የትኛውንም ዓይነት ተሃድሶ ከማድረግ በፊት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው የእውቀት ተሃድሶ ነው፡፡ ሕዝብ እንደሚገባው በእውቀት ከነቃ የዴሞክራሲና የመብቱን ጉዳይ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ይህንን ተከትሎ የሚከሰተው የእውቀት ተሃድሶ ወደ ፖለቲካዊ፣ ተቋማዊ፣ ሕገመንግሥታዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ … ተሃድሶ ይመራል፡፡ የእውቀት ተሃድሶ ሳይደረግ ከአምባገነናዊ ሥርዓት ወደ ዴሞክራሲ የሚደረግ ሽግግር አንዱን አምባገነን በሌላ የመተካት ሂደት እንጂ ዘላቂ ለውጥ የሚያመጣ አይደለም ይላሉ፡፡ ሕዝብ የእውቀት ተሃድሶ ካካሄደ በሥልጣን ላይ ከተቀመጠው አምባገነን ያልተሻሉትን የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ማንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይችላል፡፡ በፖለቲካ ብልጣብልጥነት ሊያካሂዱበት የሚችሉትን አሻጥር አስቀድሞ ያውቃል፤ … [Read more...] about ከፖለቲካ ተሃድሶ በፊት [የእውቀት] ተሃድሶ በአስቸኳይ!!
ማን ጸሎት ያሳርግ
ወ/ሮ ለምለም ጸጋው በእስልምና ሃይማኖትም ሆነ መብታቸውን ለማስጠበቅ በመናገራቸው በእስር ቤት ለሚማቅቁ ሁሉ በፎቶ አስደግፈው የጻፉትን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ … [Read more...] about ማን ጸሎት ያሳርግ
“በአገራችን ባይተዋር ከመሆን በላይ ውርደት የለም”
ይህንን ዘገባ ሳሰናዳ በ1997 ምርጫ ወቅት አዲሱ ገበያ አካባቢ አልሞ ተኳሾች የገደሉባቸውን ልጃቸውን ስም እየጠሩ “ምን አደረካቸው? ምን አጠፋህ? አንተኮ ትንሽ ነህ? ማንን ልጠይቅ? ማንን ላናግር? ልጄ … የኔ ባለተስፋ፣ እኔ ልደፋ፣ እኔ መንገድ ላይ ልዘረር፣ ምነው ለኔ ባደረገው? የማን ያለህ ይባላል…” የሚሉ ልብን ዘልቆ የሚገባ ሃረግ እየደጋገሙ እብደት የተቀላቀለው ለቅሶ አልቅሰው ያስለቀሱን እናት ታወሱኝ፤ ብዙዎች በተመሳሳይ አንብተዋል።ደረታቸውን ደቅተዋል። አሁን ድረስ የልጅ፣ የአባት፣ የወንድም፣ የእህት፣ የዘመድና ወዳጅ ብሎም የአገር ልጅ ሃዘን የሚያቃጥላቸውን ቤታቸው ይቁጠራቸው። “ኢትዮጵያ ለእኛ አስፈላጊ አገር ናት። ኢትዮጵያዊ በመሆናችን ለአገራችን ትልቅ ቦታ መስጠት አለብን። ምክንያቱም አስፈላጊ ናትና። እዚያ እስከተወለድን ድረስ /መሰረታችን ኢትዮጵያ እስከሆነች … [Read more...] about “በአገራችን ባይተዋር ከመሆን በላይ ውርደት የለም”
ከሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች
የአዲግራት ወህኒ ቤት ተደረመሰ በትግራይ ክልል ካሉት እስር ቤቶች መካከል ከ1‚300 በላይ የሚሆኑ የሕግ እስረኞችን የያዘው የአዲግራት ወህኒ ቤት ባለፈው ረቡዕ ተደርምሶ 14 እስረኞች ሲሞቱ፣ ከ35 በላይ ደግሞ በከባድ ሁኔታ መጎዳታቸውን ሪፖርተር ምንጮች እንደነገሩት ጠቅሶ አስታወቀ። እስር ቤቱ በምን ምክንያት እንደተደረመሰ ያልገለጸው ሪፖርተር እስረኞቹን ለማትረፍ ሦስት ሎደሮችና በርካታ ወታደሮች ሲረባረቡ ማየታቸውን አመልክቷል። አደጋው ቀን ረፋድ ላይ መድረሱ በጀ እንጂ አደጋው የከፋ ሊሆን እንደሚችል ተዘግቧል። ተረፉ የተባሉት 35 ሰዎች ክፉኛ በመጎዳታቸው አዲግራት ሆስፒታል ተኝተዋል። ህይወታቸው ያለፈው 14 እስረኞች ግን ከፍርስራሹ መቀበራቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስረዳል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ያደረጉት በዶዘር የተደገፈ ርብበርብ በህይወት የተረፉትን ነፍስ እንደታደገ … [Read more...] about ከሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች
“አትነሳም ወይ?!”
"አትነሳም ወይ" በሚል በሰማያዊ ፓርቲ ድረገጽ አናንያ ሶሪ ባስነበቡት ጽሁፍ ስለ “መነሳት” የተለያዩ ሃሳቦችን በማንሳት እይታቸውን አስፍረዋል። መነሳትን ከህይወት፣ ከህይወት ክንውኖች፣ ከህይወት ስንብትና ከመቃብር እስከመውጣት ባሉ ጉዳዮች በማዋዛት አሳይተዋል።በተለይም "አትነሳም ወይ" በማለት ኢህአዴግንም ፈክረውለታል። ጎልጉል በቀጥታ ከጽሁፉ የወሰደውን በማቃመስ ዋናውን ጽሁፍ በድረገጹ ላይ ታነቡ ዘንድ ይጋብዛል። “ ... አትነሳም ወይ?! ከእንቅልፍ ነው? ከሞት ነው? ከሞት ከበረታ ድንዛዜ ነው? ፎቶ ነው? ራጂ ነው? ክርስትና ነው? … በክፉ ነው የምትነሳው? በደግ ነው የምትነሳው? በትንሳዔ-ሙታን ነው የምትነሳው? በምንድነው የምትነሳው? ለምንድነው የምትነሳው? ወዴት ነው የምትነሳው? መቼ ነው የምትነሳው? እንዴትስ ነው የምትነሳው?... “… መቼም ኢትዮጵያውያን … [Read more...] about “አትነሳም ወይ?!”
“ገበሬው ነጻ እስካልወጣ ችጋር ይቀጥላል”
ሰማያዊ፡- የሰማያዊ ፓርቲ ምሰሶ የሚባሉ ዋና ዋና የሚያራምዳቸው ፖለቲካዊ አቋሞች ምንድናቸው? ኢ/ር፡ ይልቃል፡- ፖለቲካ በየጊዜው እንደሁኔታው የሚለወጥ& የሚሻሻልና የሚያድግ ቢሆንም! ሰማያዊ ፓርቲ ከአጠቃላይ የኢትዮጵያ ታሪክና ካሉብን ችግሮች በመነሳት ዋና ዋና የምንላቸው ነገሮች የሚከተሉት ናቸው፡- አንደኛ፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ለረጅም ጊዜ አብረው የኖሩ የተለያየ ልማድ& ባህል& ቋንቋ እና እምነት ያላቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የጋራ የወል ስነ-ልቦና አዳብረው በአንድነት የሚኖሩበት አገር ነው ብለን እናምናለን፡፡ ይህም ስለሆነ፡- የኢትዮጵያ ፖለቲካ በመሠረቱ ማተኮርና መነሳት ያለበት ከዜግነት እና ከግለሰብ መብት ላይ መሆን አለበት ብለን እናምናለን፡፡ እነዚህም የዜግነት እና ሰብዓዊ መብቶች እስከተከበሩ ድረስ የማይከበር የመብት ዓይነት የለም! ብሎ ነው … [Read more...] about “ገበሬው ነጻ እስካልወጣ ችጋር ይቀጥላል”
“የአረብ ጸደይ” ለኢትዮጵያ “የቆላ ቁስል” ይሆን?
ሶርያን ጊዜያዊ ማረፊያው አድርጎ አገሪቱን እያዳሸቀ፣ ህዝቡን እየበላ፣ ያለው የ“አረብ ጸደይ” ብዙዎች እንደሚሉትና የመፈክር ያህል እንደሚስተጋባው መነሻው የቱኒዚያ ምድር ሳይሆን ቆመች ስትባል መልሳ በምትናጠው ጎረቤታችን ሶማሊያ ነው። ይኸው የለውጥ “ቀይ” ነፋስ በሊቢያ ጋዳፊን እንደምናምንቴ በውሻ አይነት አሟሟት እስከወዲያኛው አሰናብቷል። ጋዳፊ ላይ ከተፈጸመው ጋር በንጽጽር ላስተዋለው አሁን በሶሪያ እየተከናወነ ያለው የዚያ ግልባጭ መሆኑን ለመረዳት የሚያዳግት አይደለም፡፡ በአገራችን አባባል “የቆላ ቁስል” እንደምንለው! ዓለምአቀፍ የግንኙነት ቡድን ተፈላጊ የሆነው አገር ስም እየተሰጠው በዓለምአቀፉ ኅብረተሰብ (በምዕራባውያን ወኪልነት) የሚቋቋመው ዓለምአቀፍ የግንኙነት ቡድን (International Contact Group) እየተባለ የሚጠራው አካል ለሶማሊያ የተመሠረተው እኤአ … [Read more...] about “የአረብ ጸደይ” ለኢትዮጵያ “የቆላ ቁስል” ይሆን?