የጉዲፈቻ ታሪክ በኢትዮጵያ በባህላዊ መንገድ ሲደረግ የቆየ ነው መቼ እንደተጀመረ በእርግጠኝነት ለማወቅ ባይቻልም በ18 ክፍለ ዘመን በኦሮሞ ብሔረሰብ እንደተጀመረ ይታሰባል። ጉዲፈቻ የሚለው ቃል የመጣው ከኦሮሚኛ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜውም ተፈጥሮዓዊ የወላጅነትና የልጅነት የሥጋ ዝምድና ሳይኖር ከሌላ ሰው አብራክ የተወለደን ልጅ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ጥቅሙን ጠብቆ እንደ አብራክ ክፋይ ልጅ ማሳደግ ማለት ነው። በኢትዮጵያ የጉዲፈቻ ሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1952 ዓ.ም በወጣው የፍትሐብሔር ሕግ ማዕቀፍ ተሰጥቶታል ይህም ሕግ የሕፃኑን መብት የሚያስጠብቅ ሆኖ የተዘጋጀ ነው። የጉዲፈቻ ዓላማ ከውርስ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የዘር ሃረግን ለመቀጠል፤ የዝምድና ትስስር ለማጠናከር፤ ፖለቲካዊ ሃይማኖታዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ለማግኝት፤ … ጥቂቶቹ ናቸው። ለምሳሌ በሀገራችንም የተለያዩ ጦርነቶች በጎሳዎች … [Read more...] about በጉዲፈቻ ስም የህፃናት የውጭ ንግድ
የጎልጉል ቅምሻ
ለቢንላደን ቀብር ምስካሪ የባህር ኃይል የለም በሚያዚያ ወር 2003ዓም ድንገተኛ ወረራ ተካሂዶበት ቀብሩም ወዲው ተጠናቅቆዋል የተባለው ኦሳማ ቢንላደን ባህር ውስጥ ሲቀበር የተመለከተ አንድም የአሜሪካ የባህር ኃይል አባል እንደሌለ ተገለጸ፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ “የመረጃ ነጻነት ሕግን” ጠቅሶ በጠየቀውና ባገኘው መረጃ መሠረት “ባልታወቀ ባህር” ተቀበረ የተባለው ቢንላደን ሲቀበር ምስካሪ እንደሌለ የዘገበ ሲሆን ከፓኪስታን ወደ ካርል ቪንስ የአሜሪካ የጦር መርከብ በተጫነበት ወቅት የተነሳ ፎቶግራፍም ሆነ ቪዲዮ የመከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) ማግኘት እንዳልቻለ ጨምሮ አስታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የድህረሞት ምርመራ፣ የሞት ሠርቲፊኬት፣ የዲኤንኤ ምርመራ፣ … እንዳልተካሄደና ይህንኑ የሚያሳይ መረጃ የመከላከያ ሚ/ር ማቅረብ እንዳልተቻለ ተገልጾዋል፡፡ የቢንላደን ሬሣ ከታጠበና በነጭ ጨርቅ … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
ከእሁድ እስከ እሁድ
የእስክንድር ነጋ ጉዳይ ለመንግሥታቱ ድርጅት ቀረበ የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላግባብ የታሠሩ ሰዎችን ጉዳይ ለሚያጠናው ግብረኃይል መቅረቡን ለህሊና እስረኞች የሚሟገተው ፍሪደም ናው “Freedom Now” ስራ አስፈጻሚ ዋና ዳይሬክተር ማርዳ ተርነር ለአሜሪካ ሬዲዮ አስታውቀዋል። ዳይሬክተሯ እንዳሉት ድርጅታቸው የእስክንድር ነጋን ጉዳይ በጥልቀት ከመረመረ በኋላ የጋዜጠኛነት ስራውን ብቻ ሲያከናውን እንደነበር ሙሉ አረጋግጠዋል። የታሰረውም ያለ አግባብ እንደሆነ ታምኖበታል። በእስር ቤት ከአያያዝ ጀምሮ በርካታ ጥሰቶች እንደተፈጸሙበት አመልክተዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለዓለም አቀፍ ህግጋት የገባውን ኪዳንና ግዴታ በመጣሱ የእስክንድር ጉዳይ በተባበሩት መንግስታት ያለ አግባብ የታሰሩ ሰዎችን ጉዳይ ለሚመረምረው አካል ባለፈው ሚያዚያ ቀርቧል። … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
በሽብርተኝነት የተከሰሱ 29 ተጠርጣሪዎች በነፃ እንዲሰናበቱ ተጠየቀ
- የተከሰሱበት ሕግ ለትርጉም ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይላክ ተባለ - የአቶ ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ክስ ተለይቶ እንዲቀርብ ተጠይቋል የሽብር ድርጊቶችን በመፈጸም፣ ሕገ መንግሥቱንና መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፈራረስ ሙከራ ወንጀልና ለሽብርተኝነት ድጋፍ በመስጠት ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ የተመሠረተባቸው 29 ግለሰቦችና ሁለት ድርጅቶች፣ የተከሰሱት ሕገ መንግሥቱን ጥሶ በወጣ ወይም በሚቃረን ሕግ በመሆኑ በነፃ እንዲሰናበቱ ጠበቆቻቸው ጠየቁ፡፡ ከሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ተጠርጣሪ ወይዘሮ ሐቢባ መሐመድ መሐሙድ በስተቀር፣ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በጋራ አሥር ጠበቆችን ያቆሙ ሲሆን፣ ክሱን እየመረመረው ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ የወንጀል ችሎት የክስ መቃወሚያ ሐሳባቸውን ኅዳር 13 ቀን 2005 ዓ.ም. አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ተከፋፍለው … [Read more...] about በሽብርተኝነት የተከሰሱ 29 ተጠርጣሪዎች በነፃ እንዲሰናበቱ ተጠየቀ
“የኢሳያስ ልጅ አይከዳም! አናምንም”
ከኤርትራ ሰሞኑን የሚወጡ መረጃዎች ከጉዳዩ ባለቤቶች ማረጋገጫ ወይም ማስተባበያ ባይቀርብበትም ከኤርትራ ጋር በተያያዘ የተለያዩ አቋምና ተስፋ ባላቸው ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት የሳበ ጉዳይ ሆኗል። አንዳንድ በብሎግ ሂሳብ የሚጫወቱ የኤርትራ መንግሥት አገልጋዮች ለጉዳዩ ጆሮ ዳባ ቢሉም በዋና በተቃዋሚነት የሚታወቁት የኢሳያስ ባላንጣዎች ለወሬዎቹ ሽፋን በመስጠት ግንባር ቀደም ሆነዋል። የ1997 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው አለመረጋጋት “ህወሃት ሰራዊቴን በመያዝ ጓዜን ጠቅልዬ ወደ ትግራይ ምድር እገባለሁ” ማለቱን አስነብቦ የነበረው ኢንዲያን ኦሽን ኒውስ ሌተር ሰሞኑን የህወሃት ሊቀመንበርን ጠቅሶ ኤርትራ ላይ ጦርነት የማወጅ ፍላጎት እንዳለ ይፋ አድርጓል። ኢንዲያን ኦሽን ከውስጥ አዋቂዎች አገኘሁ በማለት ሌላ ያሰነበበው ዜና የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ አሊ አብዶ ካናዳ ጥገኝነት … [Read more...] about “የኢሳያስ ልጅ አይከዳም! አናምንም”
Statue of bishop, Abune Petros, to be removed
“My countrymen… do not believe the fascists if they tell you that the patriots are bandits. The patriots are people who yearn for freedom from the terrors of fascism...” (Read more) … [Read more...] about Statue of bishop, Abune Petros, to be removed
ኢህአዴግ ኢህአዴግን ማፈን ጀመረ!
የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ስም ሲነሳ አቶ በረከት ስምዖን በግንባር ቀደም ይጠቀሳሉ። የአቶ በረከት ንብረት ሆኖ የመለስን አመራር በታማኝነት ሲያገለግል የኖረው ይህ ተቋም ቆርጦ በመቀጠል፣ የዜጎችን ሃሳብ በማዛባት፣ ወሬን ባለማመጣጠንና የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በማስተላለፍ የሚታወቅ ነው። ስለሚጠየፉት የማይመለከቱት እንዳሉ አፍ አውጥተው የሚናገሩም አሉ። ለሙያው ቅርብ የሆኑ አስተያየት ሰጪዎች “ወገንተኛ እንኳን ቢኾን መሰረታዊ የሙያው ግዴታ ሳይጣስ ሊሆን ይገባል። አንድ መገናኛ ማመጣጠን ካልቻለ በራሱ ሙት ነው። እያደር ብቻውን ይቀራል” ሲሉ ኢቲቪን ይገልጹታል። እንደነሱ አባባል ኢቲቪ ከህዝብ ሳይሆን ከራሱ ጌቶችም ጋር ተነጥሎ የአንድ ወገን (ግለሰብ) ሎሌ የሆነ በድርጅት ቅርጽ የሚከላወስ ሱቅ በደረቴ አይነት ነው። ኢቲቪ ሃሳባቸውን፣ ንግግራቸውን፣ አቋማቸውን፣ ጥቆማቸውንና … [Read more...] about ኢህአዴግ ኢህአዴግን ማፈን ጀመረ!
ሽ – ሽ – ት …!
ሽ - ሽ - ት …! እንደዋዛ ሲከንፍ ዕድሜዬ እኔን ጥሎ ስም ያልዘራሁበትን ወኔዬን ጠቅልሎ እንደ ቀልድ ፤ እንደ ህልም ፤ ሲከስም ወዘናዬ ብ … ን … ! ሲል የኋሊት ጠጉሬ ከላዬ እንደው እንደ ዘበት ልጆች ሲሉኝ ጋሼ መናገር ያምረኛል ዕድሜዬን ቀንሼ፡፡ ይህንንም ግጥም ያገኘነው ከፌስቡክ ላይ ሲሆን ታዋቂው ገጣሚ አብዲ ሰኢድ ነው የገጠመው፡፡ ምስጋናችንን እንቸረዋለን፡፡ በሥራ መደራረብ እንደታሰበው በወቅቱ የግጥም ጨዋታችንን በማዘግየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ ባለፈው “ህልመኛው” በሚል ርዕስ ላወጣነው ግጥም አጸፋ መልስ የሰጣችሁ የዘወትር ገጣሚዎቻችንን yeKanadaw kebede፣ inkopa፣ Tsinat፣ እና አሥራደው ከፈረንሳይ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ስለ “ሽሽት” ምን ትላላችሁ? ሽሹ! ሽሹ! ወይስ …? እስቲ ጨዋታውን አምጡት? … [Read more...] about ሽ – ሽ – ት …!
ከዚህም ከዚያም
በአለባበሳችሁ አትፈታተኑ በሜኔሶታ ጠቅላይ ግዛት የሜኔቶንካ ሁለተኛ ደረጃ ሴት ተማሪዎች የመቀመጫና የኋላ ክፍላቸውን የሚያሳይ አለባበስ እንዲያቆሙ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል፡፡ የት/ቤቱ ርዕሰ መምህር የሆኑት ዴቪድ አድኔይ ለወላጆች በላኩት የኢሜይል (የጾዳቤ) መልዕክት ወላጆች ሴት ልጆቻቸውን እንዲመክሩና የመቀመጫ ክፍላቸውን አወጣጥሮ እንዲሁም እግራቸውን በብዛት የሚያሳይ አለባበስ ሌሎችን የሚረብሽ በመሆኑ እንዳይለብሱ እንዲያደርጉ በማሳሰቢያው ጠቁመዋል፡፡ ርዕሰመምህሩ ለወሰዱት እርምጃ ከወረዳው ትምህርትቤት አስተዳደር፣ ከበርካታ ወላጆችና ከሌሎች ት/ቤቶች ድጋፍን አግኝተዋል፡፡ ውሳኔውን የተቃወሙ ተማሪዎች ሲኖሩ አንዳንድ ወላጆች ደግሞ “በየማስታወቂያው፣ በየቲቪው፣ በየመጽሔቱ፣ በሙዚቃው፣ … የሚሰራጨው የአለባበስ ዓይነት በየሱቁ ሲኬድ ከሚገኘው ጋር አንድ በመሆኑ ሰውነትን የማያሳይና … [Read more...] about ከዚህም ከዚያም
ከእሁድ እስከ እሁድ
የዋቄፈታ እምነት ተከታዮች በማህበር ተደራጅተው እውቅና ጠየቁ! ባለአወልያዎችም ተደራጅተዋል በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የዋቄፈታ እምነት ተከታዮች በማህበር ተደራጅተው ህጋዊ ፈቃድና የህጋዊነት ማረጋገጫ የምሰክር ወረቀት የጠየቁት “ይበራል ይከንፋል፣ አይሞትም ያርጋል” እየተባለ ሲመለክ የነበረው ታምራት ገለታ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተከትሎ ነበር። የእምነቱ መሪዎች በ2002 ዓ ም ወልመራ ከተማ ቆቦ በምትባል ቀበሌ መስራች ስብሰባ አካሂደው እንደነበረ ያስታውሳሉ። ከሁለት ዓመት በፊት የወልመራ ወረዳ ከተማ በሆነችው ሆለታ የተደራጁት የዋቄፈታ ስርዓተ አምልኮ ተከታዮች የህጋዊነት ጥያቄ ያቀረቡት ለኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ መሆኑን የሚጠቅሱት እነዚህ የእምነቱ ተከታዮች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንደገለጹለት ከሆነ ጥያቄያቸው ተቀባይነት አግኝቷል። መንግሥት በተደጋጋሚ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ