• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሽብርተኛ ከሳሹ ሽብርተኛው የወያኔ መንግስት

March 8, 2013 02:11 am by Editor Leave a Comment

የመጨረሻ ግባቸው የእስልምናን መንግስት ማቆም ነው ብሎ የወያኔ አስተዳደር ያቀረበውን የተቀነባበረ ፊልም ( ጃሃዳዊ ሐረካ) በመደነቅ አየሁት። ወያኔ ማለቴ እስካሁን እራሱን ነጣ አውጪ እያለ የሚጠራው የትግራይ ቡድን ኢሃድግ የሚል ማወናበጃ ስም በመረከቡ ነው፡

የተሰጠው መረጃ ውሸት ለመሆኑ ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ ባልችልም የመረጃ አቅራቢው ውሸታምነት በመረጃ በማስደገፍ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

መረጃቸውን በቴሌቭዥን የሚያቀርቡት አማን አሰፋ፣ አቡበከር አህመድ፣ ከሚል ሸምሱ፣ያሲን ኑሩ፣ ሙፍቲ አህመድ … የሚዘረዝሩት ታሪክ ወያኔ ራሱ ጥፎ ያቀረበላቸው ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ከዚህ በፊት እነ ብርትኳን ሚደቅሳ፣ ፐርፌሰር መስፍን፤ ዶ/ር ያዕቆብ… ታላላቅ ልናከብራቸው የሚገቡ ጋዜጠኞች እንደነ እስክንድር ነጋ የመሳሰሉ ሁሉ በሽብርተኛነት በመታሰራቸው፤ ወያኔ የሚቃወመውን ሁሉ ያለህግ ለማጥፋት ሲያስብ ይህንን ውንጀላ መጠቀም ከጀመረ ውሎ በማደሩ ይህኛውም ውንጀላ ከዚህ ያልተለየ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም፡ ከሳሽ ፈራጅና ቀጪም ወያኔ ራሱ ነው አቀነባባሪውም የብሄራዊ መረጃ አገልግሎት ነው። በአገሪቱ ውስጥም የሕግ የበላይነት ባለመኖሩ ሁኔታውን መርምሮ ለሕዝብ ማቅረብም አይቻልም። የጸረ ሽብርተኛ ሕግ በማለት ወያኔ ከወነጀላቸው ጋር (ያለምንምንም መረጃ) ግኑኝነት ማድረግ ከ 10 እስከ 15 ዓመት ያስቀጣል ይላል።

ያወጣውን ሕገ መንግስት በመናድ ተወዳዳሪ የሌለው ወያኔ፤ በራሱ ሕገመንግስትና ባለራዕዩ መሪ ደጋግመው ፊልሙም ላይ እንዳስረዱት መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም እየተባለ ቢደሰኩርም በክርስቲያኑም ሆነ በእስልምናው ሃይማኖት ገብተው ሲፈተፍቱ እናያለን።

በክርስትናው ሃይማኖት ጳጳሱን ከአገር አባረው የራሳቸው ቢሾሙም ተሿሚው ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩም ሌላ ጳጳስ ለወያኔ የሚያጎበድድ እስኪገኝ ሽር ጉድ እየተባለ ነው፡ “ አባይ ጸሐዬም የቀድሞውን ጳጳስ ማምጣት መንግስቱን እንደማምጣት ነው” ይህ አባባል ከመንግስት ተወካይ የተሰጠ ነው!! ሌላው የወያኔ ቁንጮ ሽማግሌው ስብሃት ነጋ “ የአማራና የክርስትያን አገዛዝ ቀብረነዋል ብሏል” እነዚህን መረጃዎች ይዘን መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም ማለት የዋህነት ነው።

የአዲሱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የጳጳስ ምርጫ ካጤነው ስለመንግስት ያለንን ግንዛቤ ያጠናክርልናል።

መንግስት ሰለሚሰራቸው የፊልም መረጃዎች ለመጥቀስ

በሐውዜን (ረቡዕ june 1988) እንጀምር ፤ ይህ ጭፍጨፋ ሲካሄድ ወያኔ ለፖለቲካ ትርፍ ሲል ወገኔ የሚላቸውን የትግራይን ሕዝቦች፤ ከከተማ እንዳይወጡ መውጫውን ዘግቶ፤ ለደርግ ቀኑን አስታውቆ ለፊልም ቀረጻ ያዘጋጃቸውን ፊልም ቀራጮች ቁልፍ ቦታ ካስያዘ በሗላ የደረሰውን የቦምብ ድብደባ በዕለቱ ከሱዳን እንዲተላለፍ አድርጓል።

ሁለተኛው ድራማ አኬልዳማ የተሰኘው ነው (2011)፡ ( አኬልዳማ በደም የተበከለ ምድር ማለት ነው) የቃሉን መሰረት ወንጌል ላይ የሐዋርያት ስራና ማቴዎስ ወንጌል ላይ ይመልከቱ፡ ወያኔ ግን ይህንን ፊልም የሰራው አንዳንድ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹን እስር ለመክተትና ህገወጥ ድርጊቱን ሕጋዊ ልብስ ለማልበስ ነው።-….የኦነግ የሽብር ቅጣት በበደኖ 1984፣ በሐረር የወያኔ አካል በነበረው የኦሮሞ ተገንጣይ ቡድን አማራው ላይ ጭፍጨፋ ሲያካሄድ፣ እርጉዝ ሴቶች ከነሕይወታቸው ሆዳቸው እየተቀደደ ሽሉ ሲወጣና ከዚያም በሗላ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ መመሪያ ሲሰጥና ፊልም ሲያነሳ ከርሞ፤ ያንኑ ፊልም ከዓመታት በሓላ አሸባሪዎች እንዲህ አደረጉ ብሎ አሳይቶናል። ከዚህ ትያትር በሗላ እነ አርቲስት ደበበ እሸቱ፣ አቶ ስለሺ ሃጎስ….በሽብርተኝነት ተፈርጀዋል። አቶ ዲማ ነገኦም የግዜው የኦነግ መሪ ስለበደኖ ጉዳይ ገለልተኛ ምርመራ እንዳይካሄድ ወያኔ መከልከሉን አሳውቀዋል። ( ሽግግር ምክር ቤት ጉዳዩ ተነስቶ ኦነግ እንዲጣራ ቢጠይቅም ጉዳዩ እንዳይጣራ ወያኔ ከለከለ ይላሉ) አርሲ እስላሞች ክርስታያኖችን ጨፈጨፉ ብሎ በቀረበው ዜና የእስላም ሽርጥ ያሸረጡ የወያኔ ወታደሮች ክርስትኖችን እያሳደዱ ሲገድሉ ታይተዋል ከሞቱትም ላይ የወያኔ የፖሊስ መታወቂያ ከኪሳቸው ተገኝቷል፡

ወያኔ ከ424 በላይ የተማሩ አኙዋኮችን መሬታችን እየተዘረፈ ለውጭ ሰዎች መቸብቸብ የለበትም ስለ አሉ ለአረብና ለሕንድ መሬቱን ለመቸብቸብ አይመቹኝም ሌላውንም ያስነሱብናል በሚል ያደረገባቸውን ጭፍጨፋ መረጃው በጄኖሳይድ ዎች እጅ ይገኛል፤ ይህን ያህል ሽብር የፈጠረ ሽብርተኛ ከወያኔ በስተቀር ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ ቡድን የለም።

በማንኛውም መመዘኛ በመንግስት ደረጃ ስልጣን ይዞ ሰላማዊ ሕዝብን እንደ እንስሳ ካልተገዛችሁልኝ የሚል ሽብርተኛ መንግሰት፤ የራሱን ወገን አንዱን ጎሳ ከሌላው ጎሳ በፖሊሲ የሚያጋጭ፣ ያ ሳይሳካ ሲቀር አሁን ደግሞ በሃይማኖት ሊያተራምስ የተቀመጠ መንግሰት ነው፤ ለስልጣኑ እስከተመቸው ድረስ ማንኛውንም ወንጀል ከመስራት ወደሗላ የሚል መንግስትም አይደለም።

መልዕክቴ መንግስት በሚያሰራጨው ከአሉባልታ ያልተሻለ መርዘኛ ዜና እርስ በርስ ልንጠራጠር አይገባም። መታገል ያለብን ይህንን ሽብርተኛ መንግስት ለማስወገድ ስለሆነ፤ በዘር፣በጎሳ በሃይማኖት…ልንከፋፈል አይገባም፤ ኢትዮጵያችን ሁላችንንም ልታስተናግድ የምትችልና ስታስተናግድም የኖረጭ አገር ናት።

ታዛቢው

ከሆላንድ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule