• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

March 6, 2013 09:29 am by Editor Leave a Comment

“ሐብቴ ቢያንስ 20ቢሊዮን ፓውንድ ነው”

የዓለማችንን ባለጠጋዎች ዝርዝር በማውጣት የሚታወቀው ፎርብስ የተሰኘው መጽሔት የሳውዲ ንጉሥ አብዱላ ወንድም ልጅ የሆኑትን ልዑል አልዋሊድ ቢን ጣላል ያላቸውን ሃብት ዝቅ አድርጎ በመናገሩ ልዑሉ እጅግ ተቆጥተዋል፡፡

የሐብታቸው መጠን ቢያንስ 20ቢሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ እንደሚደርስ የተናገሩት ልዑል በደንብ ከተሰላ መጠኑ 29.6ቢሊዮን ፓውንድ እንደሚደርስ አስታውቀዋል፡፡ ሮልስ ሮይስን፣ ፌራሪን እና ላምበርጊኒስን ጨምሮ ከ200 መኪናዎች በላይ ያሏቸው የ57ዓመቱ ልዑል ጣላል፤ በአውሮጳ እጅግ ውድ የሆኑ ሆቴሎችን ባለቤት ከመሆናቸው አልፎ እጅግ ትልልቅ የሆኑ ሁለት መርከቦች እና የዓለም ትልቁ የግል አውሮፕላን ጀት ባለቤትም ናቸው፡፡ በለንደኑ ሳቮይ ሆቴል፣ በአፕል ኩባንያ፣ በሲቲግሩፕ እና ኒውስ ኮርፕ ያላቸው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ዋጋው ዝቅ ተደርጎ እንደተገመተ ያስረዱት ልዑል ለሁኔታው ተጠያቂ ነው ያሉትን የመጽሔቱ ዋና አዘጋጅ ከሥራው እንዲባረር ጠይቀዋል፡፡ ጉዳዩንም ፎርብስ ለመካከለኛው ምስራቅ ባለሃብቶች ያለውን የተጣመመ አመለካከት የሚያሳይ ነው በማለት ወንጅለውታል፡፡

በርካታ የዓለማችን ባለጠጋዎች የሃብታቸውን መጠን በይፋ ለመናገር ፈጽሞ የማይፈልጉ መሆናቸው እየታወቀ ባለበት ሁኔታ የልዑሉ ግልጽነት በርካታዎችን አስደምሟል፡፡ እርሳቸው እንደሚሉት ሃብታቸው በትክክል ቢመዘን ኖሮ ከ26ኛ ደረጃ ወደላይ ከፍ በማለት ከሎሪዬል (የሽቶና ማስዋቢያ አምራች) ወራሽ ሊሊያን ቤተንኩር ቀጥሎ የ10ኛ ደረጃ ይጎናጸፉ ነበር፡፡

ከእስርቤት ወደ ሆቴልቤት

ቦታው ከዚህ በፊት ሰዎች የተቻላቸውን ሁሉ አድርገው ቢቻል መውጣት የሚመኙት ነው፡፡ አንድ ቀን እንኳን ማደር የማይፈልጉበት ነበር፡፡ ከፍተኛ ወንጀል የፈጸሙ እስረኞች የሚታሰሩበትና ላለፉት 150ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው በኔዘርላንድ የሚገኝ እስርቤት ፍጹም ማሻሻያ ተደርጎበት ወደ ሆቴልነት ከተቀየረ ወዲህ ግን ሰዎች በርካታ ቀናት የሚያድሩበትና ቢቻላቸውም ጨምረው መቆየት የሚፈልጉበት ቦታ ሆኗል፡፡

105 የእስረኛ ክፍሎች የነበሩት ወደ 40 ሰፋፊ ያጌጡ የሆቴል ክፍሎች ተቀይረው በክፍሎቻቸው ዘመን አመጣሽ ቲቪዎች፣ ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት፣ … ከውብ መኝታዎቻቸው ጋር አገልግሎት ይሰጣሉ፡፡ ተጠቃሚዎችም ዳጎስ ያለ ገንዘብ በመክፈል ያድሩባቸዋል፡፡

ልማት፣ ሕዳሴ፣ … እያለ ሕዝባችንን የሚያደነቁረው ኢህአዴግ ከልማትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ውስጥ የእስርቤት ግንባታውን ጉዳይ ቢሰርዘው ከሰማን እንነግረዋለን፡፡ በተለይ አሁን ደግሞ ሙስሊሞችን ጥያቄ አቀረባችሁ በማለት በገፍ እስርቤት እያስገባ ከሚያሰቃይና ተጨማሪ እስርቤቶችን ከሚሠራ ጥያቄያቸውን ቢመልስና ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች ለቅቆ የኔዘርላንድን ፈለግ መከተል ከሁሉ የላቀው ህዳሴ ነበር፡፡

“ኪርዛኪስታን” – አዲሷ የጆን ኬሪ አገር

የአሜሪካ ፖለቲከኞች ለሌላው ዓለም ስምና አጠራር እምብዛም አይጨነቁም፡፡ አጣምመው፤ አወላግደው፤ … የአገር፣ የቦታዎችን፣ የመሪዎችን ስም ሲጠሩ ይሰማሉ፡፡

በቅርቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ጆን ኬሪ ሥልጣን ከመያዛቸው አንድ ወር ባነሰ ጊዜ አዲስ አገር ፈጥረዋል – “ኪርዛኪስታን” የምትባል! በቅርቡ በቨርጂኒያ ዩኒቨርሲቲ ባደረጉት ንግግር የአሜሪካ ወዳጅ የሆነችውን ኪርጊስታንን እና የሰሜን ጎረቤቷ የሆነችው ካዛኪስታንን በመቀላቀል ኪርጊስታንን የጠሩ መስሏቸው ኪርዛኪስታን በማለት ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አዲስ አገር አስተዋውቀዋል፡፡ እንደዚህ አይነት ስህተቶችን በመስራት የሚታወቁት ጆን ኬሪ ከስድስት ዓመት በፊት በኢራቅ የሚገኙትን የአሜሪካ ወታደሮችን ዝቅ የሚያደርግ ቃል ተናግረው አያሌ ሕዝብ ተከፍቶባቸው ነበር፡፡ “ትምህርታችሁን በደንብ ከተከታተላችሁ፤ እንደሚገባው ካጠናችሁ፤ የቤት ስራችሁን ከሰራችሁ ጎበዝ ተማሪ ትሆናላችሁ፤ አለበለዚያ ግን ኢራቅ ተቀርቅራችሁ ነው የምትቀሩት” በማለት ነበር በወቅቱ ለመቀለድ የሞከሩት፡፡ በመጪዎቹ አራት ዓመታት ብዙ ሲሉ እንሰማቸዋለን፡፡

1.6 ሜትር የጾታ ግድግዳ በየሱቁ

ሳውዲአረቢያ በምትከተለው ጥብቅ ሃይማኖታዊ ሕግ ምክንያት የቅርበት ዝምድና የሌላቸው ወንድና ሴት በሙሉ ተለያይተው ሥራቸውን እንዲያከናውኑ ሰፋፊ ሱቆች 1.6ሜትር (5ጫማ ከ3ኢንች) ከፍታ ያለው ግድግዳ እንዲያቆሙ ታዝዘዋል፡፡ ወንድና ሴት ሠራተኞችን የሚቀጥሩ ሱቆች ይህንን ትዕዛዝ እንዲተገብሩና ሁኔታውንም ሃይማኖታዊ ፖሊሶች (ሙታዋ) እንዲያስፈጽሙ ተነግሯቸዋል፡፡

ሆኖም ጉዳዩ አሉባልታ ነው በማለት ምላሽ የሰጡት የመንግሥት ባለሥልጣን ወንድና ሴት ሠራተኞች የሚቀጥሩ ሱቆች ሁኔታው እንዳመቻቸው የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ በማለት ጉዳዩን አጥላልተውታል፡፡ እስላማዊው ግዛተአጼ በሚከተለው ዋሃባዊ የሻሪያ ሕግ ምክንያት በሳውዲአረቢያ ሴቶች መኪና መንዳት የማይፈቀድላቸው ሲሆን በባንኮችና ቢሮዎች የራሳቸው የመግቢያ በር የሚጠቀሙ እንዲሁም በአለባበስ በኩል ጥብቅ ሥርዓት መከተል ይጠበቅባቸዋል፡፡

በሰሜን አፍሪካ የአረብ ጸደይ የለውጥ ማዕበል ለዘመናት በሥልጣን የቆዩ መሪዎች ከሥልጣን ካስወገደ በኋላ የአሜሪካ ጥብቅ ወዳጅ በሆነችው ሳውዲአረቢያ እጅግ መጠነኛ ለውጦች እየተካሄዱ ይገኛል፡፡ ባለፈው ወር ንጉሥ አብዱላ በምክርቤታቸው አወቃቀር ላይ ማሻሻያ ካደረጉ በኋላ 150 አባላት ከሚገኙበት የሹራ ምክርቤት 30 የሚሆኑት ሴቶች መቀላቀል ችለዋል፡፡

“ሒትለር በአመጋገቡ እጅግ ጠንቃቃ ነበር” ምግብ ቀማሹ

የአዶልፍ ሒትለርን ምግብ ለዓመታ ሲቀምሱ የነበሩ የ95ዓመቷ ጀርመናዊት ሒትለር በአመጋገቡ በኩል እንዴት ጠንቃቃና አትክልትና ፍራፍሬን በታማኝነት ይመገብ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ሒትለር በምግብ መርዝ እንዳይሞት ከፍተኛ ጥበቃ እንዲካሄድ በማስፈለጉ ይህንኑ የምግብ መቅመስ ጉዳይ እንዲያከናውኑ ከተመደቡት 12ሴቶች መካከል አንዷ የነበሩት አዛውንት ሲናገሩ “ከእኩለቀን በፊት ከ5 እስከ 6ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ሁላችንም ምግቡን እንቀምሳለን፤ ከዚያም ምግቡ ወደኤስ ኤስ ጠቅላይ ጽ/ቤት ይወሰዳል” ብለዋል፡፡ ምግቡ በሙሉ አትክልት እንደነበረና የሥጋ ምግብና አሣ ሲቀርብ እንደማያስታውሱም ገልጸዋል፡፡ ባሳለፏቸው ዓመታት ከባድ ፍርሃት ላይ ወድቀው እንደነበር የተናገሩት ሴት በሆነ አጋጣሚ ምግቡ ተመርዞ ቢሆን ኖሮ እንኳን የመቅመስ ግዴታ ስለነበረባቸው ቀምሰው ሊሞቱ ይችሉ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

የጀርመን ሕዝብ የአትክልት ተመጋቢ እንዲሆን ከፍተኛ ምኞት የነበረው ሒትለር ጦርነቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ዓላማውን ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ ነድፎ እንደነበር ይነገርለታል፡፡ የአትክልትን ብቻ ምግብነት የሚደግፉ ቡድኖች በተለይ በአሁኑ ጊዜ የሥጋ ውጤቶች በኬሚካልና በሌሎች ሆርሞኖች እየተበላሸ በመምጣቱ የእንስሳትንም ሆነ የዶሮ ሥጋ ለምግብነት መጠቀም ለበርካታ በሽታዎች እንደሚያጋልጥ ይመክራሉ፡፡

“ስለ እናት”

ከዚህ በታች ያለውን ጽሁፍ ያገኘነው ከዮሐንስ ሞላ ፌስቡክ (Yohanes Molla) ነው፡፡ ስለእናቱ የጻፈውን አጭርና እጅግ መሳጭ ጽሁፍ እንዳለ አቅርበነዋል፡፡ ዮሐንስ ለጽሁፉ ርዕስ ባለመስጠቱ “ስለ እናት” ብለን ሳናስፈቅድ ርዕስ በመስጠታችን እንደማይቀየመን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ምስጋናችንም የላቀ ነው፡፡

“… በልጅነቴ ተድሬ ልጅነቴን ሳላውቀው አለፈኝ። ከዚያ በኋላ ግን ከጓደኞቼ ጋር… አሻሮ እየቆላን፣ እንኩሮ እያነኮርን እንጫወት ነበር። ስራችንን ከጨረስን ዝም ብለን እየተቀላለድን እንጫወታለን። እንዘፍናለን። እንጨፍራለን። ልጆች ነን፥ ዝም ብሎ መሳቅ መቀለድ ነው። ግን የግድ ማስተዋልም አለ።… ታዲያ ሁሉም ነገር መሽቶ ባሎቻችን ቤት እስኪመጡ ነው።… ከመሬት ተነስተው ስለሚመቱን እንፈራለን።

ያኔ ሳንቲም እንዳያጥረኝ መሸታ እጠምቅ ነበር። … መጥመቁን ከእናቴ የተማርኩት ነው። እናቴ ትነግዳለች፤ መሸታ ስለምትጠምቅ ብር አይቸግራትም ነበር። እኔም አንድ ልጇ ስለሆንኩ አይከብዳትም መሰለኝ በጣም ትንከባከበኝ ነበር። በልጅነቴ – 9 ዓመት ሲሆነኝ – ሞተች። ታዲያ ግን እርሷ የምትለውን ያምታደርገውን ሁሉንም አስታውሳለሁ። እንደሷ መሆን እፈልግ ነበር።…

ባለቤቴ የቀን ወጪ 30 ሳንቲም ይሰጠኛል። 30 ሳንቲም ብዙ ነው። ቡናውን፣ የቡና ቁርሱን፣ ወጡን፣ እንጀራውን፣ እንጨቱን፣ ሁሉንም በዚያው በ30 ሳንቲም ነው። እርሱን አብቃቅተን እንበላበትና ያልቃል።… ከሆድ አያልፍም ነበር። እንግዳ ቢመጣብኝ እንኳን አንድ ጣሳ ጠላ ገዝቼ ላስተናግድ ብል ስለማልችል ተጨማሪ ፍራንክ እፈልግ ነበር። ለዚያ ነው ጠላ የምጠምቀው። እንደዛ ስለማደርግ ሳንቲም አይቸግረኝም።

የብር ከሃምሳ ጠላ ብጠምቅ፣ ብር ከሃምሳ ትርፍ ያመጣልኝ ነበር። እንግዳ ቢመጣ አላፍርም፤ በደንብ ነው የማስተናግደው። ከጓደኞቼም ጋር አምስት አምስት ሳንቲም እናዋጣና እንጀራ፣ ጠላ ቆሎ ሁሉን ነገር ገዝተን እየበላን እየጠጣን እንጫወታለን። ጨዋታ ሳንጨርስ ስላገባን ዝም ብሎ መጫወት ያምረን ነበር። በየቀኑ ጨዋታ ነው።… እንደዚያም ሆኖ ግን ቤት አለ። የቤት ስራው አለ። ባል ይማታል። ልጅ ማሳደግ አለ።…

በ21 ዓመቴ 3 ልጆች ወልጃለሁ። ራሴ ግን ልጅ ነበርኩኝ። (ትስቃለች) እንኳን ልጅ ላሳድግ ጨዋታም ያምረኝ ነበር። መጀመሪያም ሳልፈልግ ስላገባሁ ሁሌ መፋታት እፈልግ ነበር። አባቴን በመጡ ቁጥር እጨቀጭቃቸው ነበር። ዛሬም አስፈቱኝ። ነገም አስፈቱኝ ነው። እርሳቸውም ‘ልጅነት ነው። ልጅ ስትወልድ ትተወዋለች።’ እያሉ በቀጠሮ ያራዝሙብኛል።

ብልህ ነበሩ፥ ቆይ ለፋሲካ፣ ቆይ ለመስቀል ይሉኛል። እኔም አልረሳም። እውነት መስሎኝ አስታውሼ እጠይቃቸዋለሁ። ለመስቀል ስጠይቃቸው – ‘ቆይ ለፋሲካ’ ይሉኛል። ለፋሲካ ሳስታውስ – ‘ቆይ ለገና’ ይሉኛል። እኔም ሳልረሳ እጠይቃለሁ። ታዲያ ሁለት ልጅ ተከታታይ ሞቶብኝ ሶስተኛውን ልጄ ሳይ የትም መሄድ አስጠላኝ። እንኳን አፋቱኝ ልል ከዚያ ቤት ሞት ይንቀለኝ አልኩኝ። ብማረርም መፋታቱን ማሰብ ተውኩኝ።

ታዲያ ተፋትቼ ቢሆን ኖሮ ይፀፅተኝ ነበር። ይሄን ሁሉ አላይም ነበር። ሳልፈልግ አግብቼ ከእግዚአብሄር ጋር ቤት ሙሉ ልጅ አሳደግሁኝ። … ፀጋው አይጓደል። ምን አጣሁ? ባጣም የማላውቀውን ነው።… ” ~ My Mom ♥


ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule