የፍኖተ ነፃነት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው 33ቱ ፓርቲዎች ዛሬ የመግባቢያ ስምምነት ይፈራረማሉ የኦህዴድ አመራሮች ከአባ ገዳዎች ላይ ከ400 ሺ ብር በላይ መመዝበራቸው ተገለጸ በሙስሊሙ ሕብረተሰብ ላይ እየደረሰያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ያሳስበናል (ሙሉው ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ፍኖተ ነጻነት
What is wrong with us?
The bulk of the following contribution was written some 4 years back. Things have gone even worse than anticipated. ETHIOPIA without political prisoners remains still a dream beyond reach; more and more political opponents, alas, even including religious leaders and believers are suffering and languishing behind bars, in the hands of the regional-nationalist regime, under a pseudo-legal pretext of “terrorism”. Indeed, the situation is more depressing than ever. After the death of the dictator … [Read more...] about What is wrong with us?
ኢህአዴግ አሣ አስጋሪዎችን ጨፈጨፈ
የመከላከያ ሰራዊት በድንገተኛ ከበባ ከገደላቸው ንጹሃን ዜጎች መካከል የአሜሪካ ዜግነት ያላቸውን የአቶ ኡሞት ኡዶል ግድያ አስመልክቶ የአሜሪካ መንግስት አስፈላጊውን ሁሉ ምርመራ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ግድያው ከተፈጸመ በኋላ የሰራዊቱ አባላት አስከሬን አደባባይ በማውጣት ለህዝብ እያሳዩ ደስታቸውን ሲገልጹ የተመለከቱ የጋምቤላ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ክፉኛ መበሳጨታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በጋምቤላ የደረቁን ወቅት ወይም በጋውን በወንዞች ዳር ውሃ ተንተርሶ መኖር የተለመደ ነው። ከቋሚ የመኖሪያ ቀዬ ወደ ወንዝ ዳርቻ በመሄድ አድኖ መመገብና አሳ አስግሮ ዕለትን ማሳለፍ የባህል ያህል ነው። በአገሬው ልምድ መሰረት ከቋሚ መኖሪያቸው ወደ ውሃ ዳር የሚሄዱት ወንዶች ሲሆኑ ጉዞውም የሚደረገው በቡድን ነው። በዚሁ መሰረት በጋምቤላ ክልል የጎክዲፓች ነዋሪዎች የደረቁን ወቅት ለማሳለፍ … [Read more...] about ኢህአዴግ አሣ አስጋሪዎችን ጨፈጨፈ
ከእሁድ እስከ እሁድ
“የሙስሊሙ እንቅስቃሴ ከመንግስት እጅ እየወጣ ነው …” የሙስሊሙ ጥያቄ ከመንግስት እጅ እየወጣ ስለመሆኑ የሚያመላክት ሁኔታ መታየቱን ኢሳት የካቲት 22 ቀን 2005 ዓ ም ዘገበ። ኢሳት እንዳለው የድምጻችን ይሰማ አስተባባሪዎች በነደፉት መርሐግብር መሰረት በአገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች ተቃውሞዎች ተደርገዋል። በመቀሌ፣ በመቱ፣ በጅጅጋ፣ በአፋር፣ በጅማ፣ ወልቂጤ፣ ጎንደር፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ተቃውሞዎች ተነስተዋል። በአዲስ አበባ ሙስሊሙ ማህበረሰብ “መሪዎቻችን ይፈቱ ድምጻችን ይሰማ በቤታችን ሰላም ስጡን” የሚሉ መፈክሮችን ማሰማታቸውን ያስታወቀው ኢሳት አሁን ባለው ሁኔታ የሙስሊሙ ጥያቄ ከመንግስት እጅ እየወጣ ለመሆኑ አመላካች እንደሆነ ገልጿል። የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ለመከፋፈል መንግስት በእየለቱ የሚያሰራጨው ፕሮፓጋንዳ ሙስሊሙን በቁጭት እንዲነሳ እያደረገው … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
“በኤርትራ መፈንቅለ መንግስት ይገመታል!”
ኤርትራ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ሁኔታና ወቅታዊው የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ልዕልና መላላት ተከትሎ የፖለቲካ ጨዋታው ጦዟል። በበርካቶች ዘንድ ኢሳያስ እንዳበቃላቸው ተደርጎም እየተወሰደ ነው። ኤርትራ ውስጥ ለውጥ ከተካሄደ ምን ሊከሰት ይችላል የሚለው አጓጊ ጉዳይ የሁሉንም ትኩረት የሳበ አጀንዳ ሆኗል። ኢሳያስ ያሉበት የ"ፖለቲካ ኮማ" ድብታ ውስጥ የከተታቸውም ጥቂት አይደሉም። ኢሳያስን የደረሱበት የኮማ ጣጣ መቀመጫቸውን ኤርትራ ያደረጉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ የፖለቲካ ሃይሎችና ወታደሮቻቸው የመጨረሻ እድል ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል የጠራ መረጃ ባይሰጥም ሌላውና ዋናው የጡዘቱ አካል እንደሚሆን በርካቶች ይስማማሉ። በቅድሚያ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት የሚጠቁሙም አሉ። ግን ምን አይነት ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት መፍትሄ የሚያቀርቡ የሉም። ዙሪያው ዝግ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኤርትራ ውስጥ … [Read more...] about “በኤርትራ መፈንቅለ መንግስት ይገመታል!”
ቤት መኖሩን እንመን፤ ከዚያ እንግባ!
በአውሮጳውያኑ አቆጣጠር በ1960ዎቹ በአሜሪካ የተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ጠንካራ ፉክክር የተደረገበት ነበር፡፡ ጆን ኤፍ ኬኔዲና ሪቻርድ ኒክሰን እጅግ ከፍተኛ ውድድር ካደረጉ በኋላ ኬኔዲ አሸነፉና ሥልጣኑን ተቆናጠጡ፤ ኒክሰን የሽንፈትን ጽዋ ጠጡ፡፡ ከኒክሰን ደጋፊዎች መካከል ቀዳሚ የነበረው የፊልም ተዋናይ ጆን ዌይን ነበር፡፡ የካው ቦይ ጫማውን አጥልቆ፤ ፈረሱ እየጋለበ፤ ሽጉጡ እያሽከረከረ፤ ጠላቶቹ በፊልም ይረፈርፍ የነበረው ጆን ዌይን ከሚከተለው የጸና የፖለቲካ አመለካከት አኳያ ሪቻርድ ኒክሰንን በመደገፍ ለማሸነፍ እንዲችሉ የተቻለውን እገዛ ያደረገ ነበር፡፡ ሆኖም ያሰበው አልተሳካም፤ የተመኘው መሪ ነጩ ቤተመንግሥት አልገባም፤ በሕገመንግሥቱ መሠረትም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ አልሆነም፡፡ ጆን ዌይን ኬኔዲ ማሸነፋቸውን በተረዳ ጊዜ ግን አገር ወዳድነቱንና አርበኝነቱን … [Read more...] about ቤት መኖሩን እንመን፤ ከዚያ እንግባ!
ሞት በምልጃ፤ የበረሃ ጣዕር!
“አቧራ ይጨሳል። ከዚያ ያፈኑትን ይዘው ይሰወራሉ" አስደንጋጩ ታሪክ ውስጥ ያለው ስዕላዊ ገለጻ ነው። አንድ ወቅት አዲስ አበባ የህጻናት ሌቦች ተበራክተው ነበር። በወቅቱ በርዳታ ስም ተመዝግበው የፈጣሪ ስም እየጠሩ ህጻናትን በመነገድ የከበሩ ወረበሎች በደንብ የተደራጁና የሚቀናቀናቸውን የማስወገድ አቅም ስለነበራቸው "አቧራው ጨሰ" የሚል ስያሜ የኮድ ስም ተሰጥቷቸው ነበር። አሁንም አሉ። "ህጻን እናሳድጋለን" እያሉ በዘረጉት ሰንሰለት የህጻናትን ደም የሚጠጡ "አንቱ" የተባሉ ሰዎች!! የውጪ አገር ዜጎች ጭምር … በሱዳን ሰዎችን በማፈን ሲና በረሃ የሚሰውሯቸው ራሻይዳዎች የተደራጁ ናቸው። ከአረብ ምድር የፈለሱ ናቸው የሚባልላቸው እነዚህ ጎሣዎች በሱዳንና በኤርትራ የሚገኙ ሲሆን በተለይ በኤርትራ ያሉቱ ከዘጠኙ ጎሣዎች መካከል የሚቆጠሩ ናቸው፡፡ አኗኗራቸው የዘላን በመሆኑ ከኤርትራ … [Read more...] about ሞት በምልጃ፤ የበረሃ ጣዕር!
Debretsion Church and the Ethiopians.
http://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v=W32z928rkdk#at=197 Please follow the link above and watch the YouTube video before reading this article. This is Debretsion Ethiopian Orthodox Church in London England. The picture seems to have been taken on a cold winter day. It is such a beautiful church. Doesn’t it look so serene and peaceful? I am sure it is that most of the time. But according to this video it was nothing but serene a few weeks back. The best way to express the … [Read more...] about Debretsion Church and the Ethiopians.
ከኔ ወዲያ
ዛሬ ጊዜ መቼም ሳጥን የሚወዱ ዓይነታቸው ብዙ ነው። አንድ ዓይነት ሁሉንም የሚያደርጋቸው ግን አንድ ጉዳይ አለ። ሳጥን ውስጥ መቅረት ስለሚፈልጉ፣ ሁሉም ከኔ ወዲያ ባዮች መሆናቸው ነው። እስቲ አማርኛችንም ወደ ሳጥን (1 ከመላኩ በፊት፣ የለም እንዳውም እንዳይላክ ስንል እንናገርበት፥ * ከኔ ወዲያ ነጋ ጠባ እኔ ማለት ትልቅ ምንጩ ፍርሃት ሆኖ እኮ ነው ብቸኝነት፤ የሚ-ኖረው ለጥፋት፣ በጥፋት፤ በድክመት፣ ያለምነት፤ ላይቀር ሞት። ከኔ ወዲያ ማ-ይሙት እየማለ ሲገዘት ምኑን አወቆ ስለ መብት፤ ግማሽ ጽዋው የሚ-ሞላው መች ባወቀው ይኸኛው፣ ለመሆኑ በዛ ማዶው በ-ዚያ ሌ-ላው። መች አ-ርቆ አሰበው፣ ከኔ ባዩ የጎደለው ግማሽ ጎኑ አምላኩ ነው፤ ባምባው ብቻ የማይገነው፤ ከኔ ወዲያ የማ-ይለው፣ በሁሉም ቤት … [Read more...] about ከኔ ወዲያ
ከእሁድ እስከ እሁድ
“ጁነዲን ሳዶ ሳዑዲ ገብተዋል” የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩትና በቅርቡ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው የተነሱት አቶ ጁነዲን ሳዶ ወደ አረብ አገር ማምራታቸውን አውቃለሁ ሲሉ አንድ ጎልጉል ተከታታይ ተናግረዋል። ነዋሪነታቸው ሳዑዲ አረቢያ የሆነው እኚሁ ሰው ላቀረቡት ጥቆማ ማረጋገጫ አላቀረቡም። የሆነ ሆኖ አቶ ጁነዲን ኬንያ የፖለቲካ መጠየቃቸውን ኢትዮቻናል የሚባለው የመንግስት አንደበት የሆነው ጋዜጣ ይፋ አድርጓል። ኢትዮቻናልን በመጥቀስ ዜናውን በርካታ ሚዲያዎች የዘገቡት ሲሆን እስካሁን ድረስ ማስተባበያ አልቀረበም። አቶ ጁነዲን በትክክል ኬንያ የሚገኙ ከሆነ ኢህአዴግ ሊይዛቸው ስለሚችል ወደ ሌላ አገር ባስቸኳይ እንደሚያመሩ ከግምት በላይ አስተያየት ተሰጥቷል። ወደ አውሮፓና አሜሪካ ለማምራት አስቸጋሪ ሁኔታ ስለሚገጥማቸው ምን አልባትም የደንበኛችን ጥቆማ ትክክል … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ