ንብረትነቱ የሕዝብ ቢሆንም አገልግሎቱ የኢህአዴግ የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ የሆነው ኢቲቪ በሰሞኑ የፍርድ ቤት ዕግድ ወደጎን በመግፋት ከተለያዩ ፊልሞች በመቀነጫጨብ ‹‹ጂሃዳዊ ሃረካት›› በማለት ጉዳያቸው በፍርድቤት እየታየ ባለው በእሥር ላይ የሚገኙት የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ያነጣጠረ ፊልም በተደጋጋሚ አሰራጭቶ ተከታትለናል፡፡ (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ) … [Read more...] about በጂሃድ ሃረካት ፊልም ላይ ከ33ቱ ፔቲሺን ፈራሚዎች የተሰጠ መግለጫ
የኦርቶዶክሱ “ክሩሴድ”/ “Crusade” የሚባል መርዝስ መች ይሆን የሚረጨው?
በታላቁ ኢትዮጵያዊያችን አንደበት፣ ኢትዮጵያ ዛሬም ያለችበትን ከፍተኛ የሕልውና አደጋን ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ያገናዝብ! እንደ ግራዝያኑ፣ ማለትም ያቃጣል! የዛሬው የኢትየጵያ መንግሥት ርሕራሄ የሌለውን በትሩን ያነሳው የተቃዋሚ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹ ብቻ ላይ ሳይሆን፣ ሃይማኖት ኃይል ፖለቲካ፣ ለሰብዓዊ መብታቸው የቆሙ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ ነው። ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር የቆየ ዕምነታቸውን ይዘው፣ ለሃይማኖት መብታቸው የሚሟገቱ ሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሆኑ፣ ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር የተያያዘው የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ምዕመናኖችም ጭምር ነው። ትላንት /05.02.13/ ጀሃዳዊ ሃረካት በሚል ስም ሃገር፣ ህግና ወገን የሚያሰድብ፣ የሚያሳፍር፣ ለዘመናት ተቻችለው የኖሩትን ትላልቅ ሃይማኖቶችን ለማጋጨት የቅስቀሳ መርዙን በረጨ ማግስት፣ ዛሬ /13.02.13/ ደግሞ ከያን ሰሞን ሳይታሰሩ … [Read more...] about የኦርቶዶክሱ “ክሩሴድ”/ “Crusade” የሚባል መርዝስ መች ይሆን የሚረጨው?
ኢህአዴግ ሌላ፤ ኢትዮጵያችን ሌላ!!
ሚዲያ ከስሜታዊነት፣ ከስጋና ደም ድምር፣ ከችኩል ውሳኔና ግብታዊነት ነጻ ለመሆን ሌት ተቀን መስራት እንዳለበት ባለሙያዎች አበክረው የሚናገሩት ዓቢይ ጉዳይ ነው። ሚዲያ ስንል ደግሞ ሁሉንም ነው - የኅትመት፣ የምስል፣ የድምጽ፣ የድረገጽ፣ የዲጂታል፣ የማኅበራዊ ድረገጽ፣ … ። ሁሉም ሚዲያዎች አሻግሮ በማየት ህዝብንና አገርን የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው። ጋዜጠኞች ወይም እንደ ጋዜጠኛ የሚሠሩ ሁሉ ከየትኛውም ሙያተኛ በላይ ሃላፊነት ሊሰማቸውም ግድ ነው። ለዚህም ነው በጋዜጠኝነት ሙያ "አመጣጥን፣ አሁንም አመጣጥን፣ አሁንም አመጣጥን … “ባላንስ” አድርግ" የሚባለው!! ከኢህአዴግ ዓይነ ያወጣ ውሸትና ዝግነት የተነሳ ሁሉንም መረጃዎች የማመጣጠኑ ሙያዊ ሃላፊነት ለመወጣት ፈተና ቢያጋጥምም በከፍተኛ ደረጃ ጥንቃቄ ልንወስድባቸው የሚገባን ጉዳዮች አሉ። ከነዚህ ጉዳዮች መካከል አንዱና ዋናው … [Read more...] about ኢህአዴግ ሌላ፤ ኢትዮጵያችን ሌላ!!
“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
/ዜና ጎልጉል/ ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት "የአስተዋይነት" ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል። ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል። በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት … [Read more...] about “ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
፪ኛው ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ
በኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል (ኢሴመማ) ፪ኛው ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ በዲያስፖራ የጉባኤው ቀዳሚ ቃል “የኢትዮጵያ ሴቶች በደል ማብቃት አለበት” ቅዳሜ መጋቢት ፲ ፮ ቀን ፳፻፭ዓም በዋሽንግተን ዲሲ 2nd ANNUAL INTERNATIONAL ETHIOPIAN WOMEN CONFERENCE IN THE DIASPORA Washington Marriott Hotel 1221 22nd Street, Washington, DC 20037 March 23, 2013 9 AM TO 5 PM … [Read more...] about ፪ኛው ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ
Immediate Press Release: Center for Rights of Ethiopian Women
February 14, 2013 The Center for the Rights of Ethiopian Women (CREW) appreciates Ethiopian Sport Federation of North America (ESFNA) for its decision to uphold the theme of “Celebrating Ethiopian Women” at its 30th year anniversary. Ethiopian women are known worldwide for their cultural diversity and beauty; but for far too long, their intelligence, tenacity, achievements as well as the tremendous hardships they face have not been part of the social dialogue adequately. Their heroic … [Read more...] about Immediate Press Release: Center for Rights of Ethiopian Women
ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ
እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ ሀገርንና ትውልድን የሚያጠፋ እኩይ አመለካከትና ምግባር ይዞ ተነስቶና ተሳክቶለትም የሚገዛ ከኢትዮጵያ ውጭ በአለም ላይ ያለ ሀገርም ሆነ የሚገዛ ህዝብ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግ የገዛ ወገኑንና ሀገሩን በጠላትነት ፈርጆ፣ ታጥቆና ተደራጅቶ የሚወጋና የሚያፈራርስ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ አገዛዝም ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊንን የማጥፋቱንና የመበታተኑን ምግባር እንዲያቆም እሽሩሩ የተባለና እየተለመነ ያለ የለም።..... በልመና ቢሆን..... ፍትህ - እኩልነት በልመና ቢሆን... ነጻነት - አንድነት በልመና ቢሆን.... ሰላምና ሕይወት፤ እመጣ ነበረ- አንች ካለሽበት ትመጭልኝ ነበር - እኔ ካለሁበት ዓለም ይሆን ነበር፣ የሁላችንም ቤት። እንደ ደርግ ያለ አምባገነን መንግስት ሀገሩን በክህደትና በጥላቻ ለተሞሉ፤ እንደ ሻአቢያዊንና እንደ … [Read more...] about ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ
በአልቃይዳ ሰበብ ቻይናን መቆጣጠር
የአገራቸውን አጠቃላይ ሁኔታ እና መጪው ጊዜ ምን እንደሚመስል፤ የአገራቸውን የወደፊት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ … ሁኔታ እንዲሁም አሜሪካ በቀጣይ ዓመታት የምትከተለውን የአጭርና የረጅም ጊዜ የውጪ ፖሊሲ ዕቅድ በተመለከተ ለሁለተኛ ጊዜ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ማክሰኞ ምሽት ለምክርቤቱ ንግግር ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኦባማ በርካታ ጉዳዮችን ዳስሰዋል፡፡ አፍሪካና ቻይናም የንግግራቸውን ሙሉ ቀልብ የሳቡ ነበሩ ባይባልም ሳይጠቀሱ አልታለፉም፡፡ በተለይ ስለአፍሪካ እንዲህ ብለዋል፤- ‹‹… የተለያዩ አፍቃሪ የአልቃይዳ ወኪሎችና አክራሪዎች ከአረብ ምድር እስከ አፍሪካ ብቅ እያሉ መጥተዋል፤ እነዚህ ቡድኖች ሊያመጡ የሚችሉት አደጋ እንደዚያው እያደገ መጥቷል፡፡ ይህንን አደጋ ለመቋቋምም በአስር ሺዎች የሚጠጉ ልጆቻችንን በመላክም ሆነ አገራትን መቆጣጠር አያስፈልገንም፡፡ ይልቁንም … [Read more...] about በአልቃይዳ ሰበብ ቻይናን መቆጣጠር
እንደ ሻማ
አንደ ሻማ ነው ማንባት፣ ቀልጦ ጠብ እንደሚለው፤ የነፍሳችንን ስቃይ፣ ይሉኝታ ሳይጋርደው፤ ማስመሰል ሳያርቀው፡፡ እንደ ሻማ ነው መቅለጥ፣ በነበልባል ነዶ በግኖ፤ ሰብእናን በህይወት ጣር፣ ሰርቶ በማደር ፈትኖ፡፡ እንደ ሻማ ነው መብራት፣ ማለቅም እንደ ሻማ፤ ለሌላም ባይሆን ለነፍስ፣ አብርቶ የእውነትን ፋና፡፡ በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ፣ /ፍካት ናፋቂዎች፤1999ዓ.ም/ ባለፈው ሁለት ግጥሞችን አቅርበን ነበር፡፡ “ቅኔ” እና “የማይጠፋ ፍቅር” በሚል ርዕሶች ለቀረቡት ግጥሞች ጨዋታውን በማድመቅ የተቀኛችሁትን እና ማብራሪያም የሰጣችሁትን ተሳታፊዎቻችንን በለው፤ YeKanadaw Kebede፤ አሥረዳው፤ እስከመቼ እና ዱባለ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡ ለዛሬው ደግሞ በግጥም ልተንፍሥ ከተባለ የፌስቡክ ገጽ ይህንን ግጥም አግኝተን ለጨዋታ አቅርበነዋል፡፡ “እንደ … [Read more...] about እንደ ሻማ
ለቅሶ ሳቅ – ሳቅ ለቅሶ
አቅቶን መለወጥ ለቅሶን በደስታ፤ ሃዘን ጠል አልብሶን ሳቅ ደርቦ ኩታ፤ ያንዱን ቤት ገንብቶ የሌላውን ሲያፈርስ፤ አንዱን ሳቅ አጅቦት ሌላው ከፍቶት ሲያለቅስ፤ ለቅሶ ሳቅ - ሳቅ ለቅሶ - እየደባለቀ፤ ግማሽ ጎኑ ሲያለቅስ - ግማሽ ጎኑ ሳቀ:: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ለቅሶ ሳቅ – ሳቅ ለቅሶ