• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት!

June 8, 2013 01:21 am by Editor Leave a Comment

ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡-

1ኛ – ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣

2ኛ – መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን መገንዘቡና ፓርቲውም የተጠየቀውን ዋጋ ከፍሎ ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድለት መብቱን ከደጋፊዎቹ ጋር ከማራመድ ወደኋላ እንደማይል (that those guys were not bluffing) እየመረረው መረዳቱ።

“መንግሥት” አማራጭ እንዳልነበረው ሌላው ተጨባጭ ማስረጃ ደግሞ በሚያስደንቅ ቅንጅት፣ ኅብር፣ ምጥነት፣ ጨዋነት እና ሰላም የተካሄደውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚ/ር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እና የሕወሓት/ኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ሁሴን የሰጡት ከድንጋጤ የመነጨ የተፋለሰ መግለጫ ነው። በነገራችን ላይ እንደተለመደው “የኢትዮጵያ” ቴሌቪዥን አንድም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል ወይንም የሰልፉ ተሳታፊ ዜጋ አላነጋገረም፣ ወይንም አላቀረበም – በወፍ-በረር ቅኝት በመበተን ላይ ያለና ዘርዘር ያለ የሕዝብ ስብስብ ጠብቆ በካሜራው ከመቅረፅና ማቅረብ በስተቀር።

የ”መንግሥት” ወገኖችን አተያይ ስንቃኝ፤

በመጀመሪያ ከ”ኢትዮጵያ” ቴሌቪዥን ብንጀምር ከክስ አዘል ዘገባዎቹ መካከል፡- “የሰልፈኞቹ ጥያቄ በፍርድ ቤት በተያዘው የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የሸባሪነት ክስ ላያ አተኩሯል፣ በኢቲቪ እና በመንግሥት ላይ ያላቸውን ቅሬታ ገልፀዋል፣ አትነሳም ወይ ይሄ ባንዲራ ያንተ አይደለም ወይ ሲሉ ነበር፣ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት ዕውቅና የተሰጠው የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ እንዳይታይ ሲከለክሉም ተስተውለዋል፣ በተቃውሞ ሰልፉ ማጠናቀቂያ የእስልምና ተከታዮች የስግደት ሥነ-ስርዓት ፈጽመዋል።”

በመቀጠል አቶ ሽመልስ ከማል ከሰነዘሩዋቸው ውስጥ ደግሞ፡- “….መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አለመግባት የሚለውን ሕገ-መንግሥት አጥብቆ ያከብረዋል……..በተደረገው ሰልፍ በፖለቲካና በሃይማኖት መካከል ሕገ-መንግሥቱ ያሰመረው መስመር ሲደረመስ የሚታይበት ሁኔታ አለ፣ በሃይማኖት ሽፋን ሽብርተኝነት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ያለውን ግለሰቦች የተከሳሾቹ ጠበቃዎች ከፍርድ ቤት ውጪ በሆነ ሂደት የፍርድ ሂደቱን ለማጨናገፍ መሞከር ሕግ አይፈቅድላቸውም፣ ከቤኒንሻንጉል ገምዝ የተፈናቀሉትን ሰዎች አስመልክቶ የዛሬዎቹ ሰዎች ኡኡታ ከማሰማታቸው አስቀድሞ መንግሥት ሁኔታውን አይቶ ፈጣን እርምጃና እርምት የወሰደበት ጉዳይ ነው ፣ ከዚህ ባለፈ እንዲህ ዓይነቶቹን ጉዳዮች….exceptions ወይም እንደ በስተቀር የሚወሰደውን ነገር (እጅግ በጣም አልፎ አልፎ የሚከሰት ነገር ማለታቸው ነው) ዋና መደበኛ አሠራር አስመስሎ ያንን አጉልቶ ከዚያ ፖለቲካዊ ትርፍ አስልቶ ለማግኘት የሚኬድ ነገር ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል መታወቅ ይኖርበታል።”

በሌላ ወሬ የሕወሓት/ኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ሁሴን “ሰማያዊ ፓርቲ ከአሸባሪዎች ጋር ፖለቲካዊ ጋብቻ መፈፀሙን እሁድ ለት በጠራው ሰልፍ በግልፅ አሳይቷል…” ብለዋል፡፡

ይህ ምን ይነግረናል? ምስክር በሦስት ይፀናል እንዲሉ አበው፤ ሦስት የመንግሥት ከፍተኛ አካላት (ኢቲቪ፣ አቶ ሽመልስ እና አቶ ሬድዋን) ከላይ የተጠቀሱትን መሠረተ-ቢስ ውንጀላዎች አካሂደዋል። በእነሱ ስሌት የበለጠ ጉዳትን ለማስቀረት በአጣብቂኝ ዕውቅና የሰጡት ሰላማዊ ሰልፍ ስኬታማነት ያስደነገጣቸውና ያበሳጫቸው የአገዛዙ ባለሥልጣናት የሰጡት  ይፋዊ መግለጫ የሚያሳየው፤ ቀድሞውኑ አማራጭ አጥተው የተስማሙበት ጉዳይ መሆኑን ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊትም ተመሳሳይ ጥያቄ ላለማስተናገድ ሰማያዊ ፓርቲን፣ አመራሩንና፣ ተቃዋሚ ሕዝቡን እንደተለመደው “በሽብርና ሕገ-መንግሥት ለመናድ መሞከር” በመወንጀል (framing the opposition forces by criminalizing peaceful dissent) የመፃዒ የቤት ሥራቸውን መሠረት ጥለዋል።

ስለዚህ ቀድሞውኑም “መንግሥት” የምርጫ ‘97 ዓይነቱን የፖለቲካ ክፍተት ፈቀደ፣ ዲሞክራሲያዊ ብልጭታ አሳየ ወዘተርፈ በማለት ለሺህኛ ጊዜ በየዋህነት ለተታለሉ የዋህ ዜጎች እላለሁ – በእኔ አመለካከት ሕወሓት/ኢህአዴግ መፈናፈኛ አጥቶ ነው ይህቺ የፖለቲካ ክፍተት የተፈጠረችበት እንጂ ሃገሪቱን ወደየት እየመራት እንደሆነ ለማንኛውም የሚያመዛዝን አዕምሮ ግልጽ ነው።

“መንግሥት” አሁን በያዘው አካሄድ አገዛዙ እንዲህ ያለ የፖለቲካ አዎንታዊነት መፍጠር ማለት ወደ ጠፈር በመተኮስ ላይ ያለን ሮኬት ጠምዝዞ ወደምድር የመመለስ ያህል ይመስለኛል። በዚህም ምክንያት እላለሁ – ትግሉ መራራ ነው። የተኛ መንቃት፣ የተናጠለ መደራጀት፣ የበቃው ቁርጠኝነት ይሻዋል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule