• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት!

June 8, 2013 01:21 am by Editor Leave a Comment

ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡-

1ኛ – ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣

2ኛ – መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን መገንዘቡና ፓርቲውም የተጠየቀውን ዋጋ ከፍሎ ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድለት መብቱን ከደጋፊዎቹ ጋር ከማራመድ ወደኋላ እንደማይል (that those guys were not bluffing) እየመረረው መረዳቱ።

“መንግሥት” አማራጭ እንዳልነበረው ሌላው ተጨባጭ ማስረጃ ደግሞ በሚያስደንቅ ቅንጅት፣ ኅብር፣ ምጥነት፣ ጨዋነት እና ሰላም የተካሄደውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚ/ር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እና የሕወሓት/ኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ሁሴን የሰጡት ከድንጋጤ የመነጨ የተፋለሰ መግለጫ ነው። በነገራችን ላይ እንደተለመደው “የኢትዮጵያ” ቴሌቪዥን አንድም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል ወይንም የሰልፉ ተሳታፊ ዜጋ አላነጋገረም፣ ወይንም አላቀረበም – በወፍ-በረር ቅኝት በመበተን ላይ ያለና ዘርዘር ያለ የሕዝብ ስብስብ ጠብቆ በካሜራው ከመቅረፅና ማቅረብ በስተቀር።

የ”መንግሥት” ወገኖችን አተያይ ስንቃኝ፤

በመጀመሪያ ከ”ኢትዮጵያ” ቴሌቪዥን ብንጀምር ከክስ አዘል ዘገባዎቹ መካከል፡- “የሰልፈኞቹ ጥያቄ በፍርድ ቤት በተያዘው የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የሸባሪነት ክስ ላያ አተኩሯል፣ በኢቲቪ እና በመንግሥት ላይ ያላቸውን ቅሬታ ገልፀዋል፣ አትነሳም ወይ ይሄ ባንዲራ ያንተ አይደለም ወይ ሲሉ ነበር፣ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት ዕውቅና የተሰጠው የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ እንዳይታይ ሲከለክሉም ተስተውለዋል፣ በተቃውሞ ሰልፉ ማጠናቀቂያ የእስልምና ተከታዮች የስግደት ሥነ-ስርዓት ፈጽመዋል።”

በመቀጠል አቶ ሽመልስ ከማል ከሰነዘሩዋቸው ውስጥ ደግሞ፡- “….መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አለመግባት የሚለውን ሕገ-መንግሥት አጥብቆ ያከብረዋል……..በተደረገው ሰልፍ በፖለቲካና በሃይማኖት መካከል ሕገ-መንግሥቱ ያሰመረው መስመር ሲደረመስ የሚታይበት ሁኔታ አለ፣ በሃይማኖት ሽፋን ሽብርተኝነት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ያለውን ግለሰቦች የተከሳሾቹ ጠበቃዎች ከፍርድ ቤት ውጪ በሆነ ሂደት የፍርድ ሂደቱን ለማጨናገፍ መሞከር ሕግ አይፈቅድላቸውም፣ ከቤኒንሻንጉል ገምዝ የተፈናቀሉትን ሰዎች አስመልክቶ የዛሬዎቹ ሰዎች ኡኡታ ከማሰማታቸው አስቀድሞ መንግሥት ሁኔታውን አይቶ ፈጣን እርምጃና እርምት የወሰደበት ጉዳይ ነው ፣ ከዚህ ባለፈ እንዲህ ዓይነቶቹን ጉዳዮች….exceptions ወይም እንደ በስተቀር የሚወሰደውን ነገር (እጅግ በጣም አልፎ አልፎ የሚከሰት ነገር ማለታቸው ነው) ዋና መደበኛ አሠራር አስመስሎ ያንን አጉልቶ ከዚያ ፖለቲካዊ ትርፍ አስልቶ ለማግኘት የሚኬድ ነገር ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል መታወቅ ይኖርበታል።”

በሌላ ወሬ የሕወሓት/ኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ሁሴን “ሰማያዊ ፓርቲ ከአሸባሪዎች ጋር ፖለቲካዊ ጋብቻ መፈፀሙን እሁድ ለት በጠራው ሰልፍ በግልፅ አሳይቷል…” ብለዋል፡፡

ይህ ምን ይነግረናል? ምስክር በሦስት ይፀናል እንዲሉ አበው፤ ሦስት የመንግሥት ከፍተኛ አካላት (ኢቲቪ፣ አቶ ሽመልስ እና አቶ ሬድዋን) ከላይ የተጠቀሱትን መሠረተ-ቢስ ውንጀላዎች አካሂደዋል። በእነሱ ስሌት የበለጠ ጉዳትን ለማስቀረት በአጣብቂኝ ዕውቅና የሰጡት ሰላማዊ ሰልፍ ስኬታማነት ያስደነገጣቸውና ያበሳጫቸው የአገዛዙ ባለሥልጣናት የሰጡት  ይፋዊ መግለጫ የሚያሳየው፤ ቀድሞውኑ አማራጭ አጥተው የተስማሙበት ጉዳይ መሆኑን ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊትም ተመሳሳይ ጥያቄ ላለማስተናገድ ሰማያዊ ፓርቲን፣ አመራሩንና፣ ተቃዋሚ ሕዝቡን እንደተለመደው “በሽብርና ሕገ-መንግሥት ለመናድ መሞከር” በመወንጀል (framing the opposition forces by criminalizing peaceful dissent) የመፃዒ የቤት ሥራቸውን መሠረት ጥለዋል።

ስለዚህ ቀድሞውኑም “መንግሥት” የምርጫ ‘97 ዓይነቱን የፖለቲካ ክፍተት ፈቀደ፣ ዲሞክራሲያዊ ብልጭታ አሳየ ወዘተርፈ በማለት ለሺህኛ ጊዜ በየዋህነት ለተታለሉ የዋህ ዜጎች እላለሁ – በእኔ አመለካከት ሕወሓት/ኢህአዴግ መፈናፈኛ አጥቶ ነው ይህቺ የፖለቲካ ክፍተት የተፈጠረችበት እንጂ ሃገሪቱን ወደየት እየመራት እንደሆነ ለማንኛውም የሚያመዛዝን አዕምሮ ግልጽ ነው።

“መንግሥት” አሁን በያዘው አካሄድ አገዛዙ እንዲህ ያለ የፖለቲካ አዎንታዊነት መፍጠር ማለት ወደ ጠፈር በመተኮስ ላይ ያለን ሮኬት ጠምዝዞ ወደምድር የመመለስ ያህል ይመስለኛል። በዚህም ምክንያት እላለሁ – ትግሉ መራራ ነው። የተኛ መንቃት፣ የተናጠለ መደራጀት፣ የበቃው ቁርጠኝነት ይሻዋል።

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule