• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ ጣና በለስን ለምን አፈራረሰው?

June 8, 2013 02:31 am by Editor 6 Comments

በግብጽ ረዳትነት፣ በሱዳን መሪነት መንግስት ለመሆን የበቃው ህወሃት/ኢህአዴግ ግዙፉን የጣና በለስ ፕሮጀክትና ንብረቱ እንዲዘረፍ ያደረገበትን ምክንያት በማንሳት መከራከር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ። የግብጽ ፕሬዚዳንት ሙርሲ እንዳደረጉት በአገር ጉዳይ ሁሉንም ያሳተፈ ግልጽ አቋም እንዲያዝና አጋጣሚውን በመጠቀም ብሔራዊ ህብረት እንዲፈጠር ኢህአዴግ በሩን ሊከፍት እንደሚገባ ተገለጸ።

በተለያዩ ጉዳዮች ምክንያት ስማቸው እንዳይጠቀስ በማሳሰብ ለጎልጉል አስተያየት የሚሰጡት የኢህአዴግ ሰው እንዳሉት በርካታ ጉዶች ያሉበትን የአባይን ግድብ ተከትሎ ከግብጽ ጋር የተነሳው ውዝግብ አስቀድሞ የሚታወቅ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ስልትና ውጤት ነው።

አሁን ድረስ አገር እየመራ በነጻ አውጪ ስም የሚጠራው ህወሃት/ኢህአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ “ዲሞክራሲ አመጣሁ” በማለት ኢትዮጵያን መምራት እንደጀመረ የሚያወሱት የኢህአዴግ ሰው፤ አቶ መለስ ብቻቸውን ይነዱት የነበረው ኢህአዴግ እንደፈለገ ቆዳውን እየቀያየረ የተጠቀመበትንና በእስስት በመመሰል “ከሽፏል የሚሉትን” ስልት ያብራራሉ።

በዲሞክራሲ ስም የተጀመረው የኢህአዴግ አገዛዝ ቆየት ብሎ “ልማታዊ ነኝ፣ ልማት ግቡን የሚመታው በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ቀመር ነው” በማለት ፕሮፓጋንዳውን አሰፋ። የልማት ህልመኛነቱ ሲነቃበት “የትራንስፎርሜሽን ዘመቻ” በማለት አዲስ የፕሮፓጋንዳ እቅድ ነድፎ ህዝብና አገር ሲያታልል ቆየ። ይህም አላራምድና በህዝብ የመታመን ድል ሊያስገኝለት እንደማይችል ሲታመን “የህዳሴያችን ግድብ” ተብሎ አባይ አጀንዳ እንደተደረገ ያመለከቱት ዲፕሎማት፤ “ኢህአዴግ አገር ውስጥ የሚያምታታባቸው መንገዶች ሲጠናቀቁበት የፕሮፓጋንዳውን ዘመቻ አንድ ደረጃ ከፍ አደርገው” በማለት አሁን ከግብጽ ጋር ስለተጀመረው ውዝግብ አስተያየታቸውን ይጀምራሉ።

አባይን በመገደብ ኢትዮጵያን በልማት ለማሳደግ እየተጋ እንደሆነ የሚናገረው ኢህአዴግ፤ አስቀድሞ በመላው የብአዴን የበታች አመራሮችና በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታና ቂም ስላስቋጠረው የጣና በለስ ሰፊ ፕሮጀክት ዝርፊያና ውድመት የጠራ መልስ ሊሰጥ እንደሚገባ ዲፕሎማቱ ይናገራሉ።

በጣሊያን መንግስት ሙሉ ድጋፍ አባይ ወንዝን መሰረት አድርጎ የተገነባውን የጣና በለስ ፕሮጀክት ህዝብ እያየ አፈራርሰው እንደወሰዱት፣ የተዘረፈው ንብረት ወደ ኤርትራ እንዲጓጓዝ መደረጉን ያመለከቱት እኚሁ ሰው፣ “ጣና በለስን አፈራርሶ ያስዘረፈ ፓርቲና አመራሮቹ አሁን አባይን ለመገደብ የተነሱበት መነሻ ለአብዛኛው የኢህአዴግ አባላት እንቆቅልሽ ነው” ባይ ናቸው። በማያያዝም በወቅቱ ዝርፊያው ሲካሄድ ህዝብ አካፋና ዶማ በመያዝ “ንብረቱ አይዘረፍም” በማለት መንገድ በመዝጋቱ ዝርፊያው በሌሊት እንዲካሄድ ያደረገ ድርጅት እንዴትስ ይታመናል የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።

“ኢህአዴግ የህይወት ዘመኑ የሚጠናቀቅበት ጠርዝ ላይ ስለሚገኝ፣ በአባይ ጉዳይ አመካኝቶ ህዝባዊ ማዕበል ለማቀጣጠል አቅዷል። የአባይ ጉዳይ ከዚህ የተለየ ተግባርና ዓላማ የለውም” የሚሉት አስተያየት ሰጪ፣ የጣና በለስ ፕሮጀክት እንዲወድም መመሪያ የተሰጠው ከግብጽ እንደነበር መረጃ እንዳላቸው አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ቀንደኛ ታሪካዊ ጠላት የሆነችው ግብጽ አባይ ላይ የሞትና የህይወት አቋም ቢኖራትም አሁን የተጀመረው ውዝግብ ከወሬ የዘለለ ግጭት እንደማያስነሳም ተናግረዋል።

በግብጽ አሁን ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት ለማስቀየር እየሰሩ ያሉት ፕሬዚዳንት ሙርሲ፣ የአባይን ጉዳይ ልቡን ከነፈጋቸው የአገራቸው ህዝብ ጋር ቃል ኪዳን ለማድረግ እንደሚጠቀሙበት ያመለከቱት አስተያየት ሰጪ፣ የአገራችን ተቃዋሚዎች እንደ ግብጽ ተቃዋሚዎች መጫወቻ እንዳይሆኑ ይመክራሉ። “ኢህአዴግ የሚቃወሙትን ፓርቲዎች አባይን ተንተርሶ በአገር ክህደትና የአገርን ብሔራዊ ጥቅምን በመጻረር ፈርጆ ከህዝብ ጋር ሊያጋጫቸው ተዘጋጅቷልና ከወዲሁ ዝግጅት አድርጉ” ሲሉ ይመክራሉ።

በሌላ በኩል ሙርሲ እንዳደረጉት ኢህአዴግ በወቅቱ ጉዳይ ላይ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ሊያነጋግር እንደሚገባ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል ተናግረዋል።

አቶ ኦባንግ እንደሚሉት “አገር የህዝብ ነው። ህዝብ በተለያየ መልኩ ይወከላል። ከሚወከልበት መንገድ አንዱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ናቸው። አገርን አስመልክቶ በየደረጃው ያሉ የህዝብ ወኪሎችን ማግለል ህዝብን የማግለል ያህል ነው። ይህን ማድረግ ይቅር የማይባል ወንጀል ይሆናል”

አገር ቤት ያሉትን ብቻ ሳይሆን በውጪ አገር ያሉትንም ፓርቲና ድርጅቶች በዚህ ጉዳይ ማነጋገር ግድ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ለዚህ አገራዊ ውይይት ማንኛውም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ ሊቀመጥ አይገባም” ብለዋል።

አጋጣሚው ለምንናፍቀውና ሁሉንም የአገሪቱን ህዝብ በእኩል ደረጃ ለማስተናገድ የሚያስችል ስርዓት ለመፍጠር እንደሚረዳ አቶ ኦባንግ ጠቁመዋል። የተለየ አመለካከት በማራመዳቸው ብቻ ዜጎችን እስር ቤት በማጎር እስከ ወዲያኛው መዝለቅ እንደማይቻል ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የውይይት በር በመክፈት የማያልፍ ታሪክ ሊሰሩ እንደሚገባ መክረዋል።

“ሙስሊም ወንድሞች ፍትህ የጠማቸው ኢትዮጵያዊ እንደሆኑ የሚያረጋግጡበትን መድረክ አቶ ሃይለማርያም በማመቻቸት የማይረሳ ታሪክ ሊሰሩ ይገባል” በማለት ጥሪ ያስተላለፉት አቶ ኦባንግ “አገር የህወሃት አይደለችም፤ አገር የኢህአዴግ አይደለችም፣ አገር የግለሰቦች አይደለችም። አገር የሁሉም ነው። ባገር ጉዳይ ባይተዋር ሊደረጉ የሚገባቸው ዜጎች ሊኖሩ አይገባም። ኢህአዴግ ይህን ጉዳይ ሊያስብበትና በሩን ለእርቅና ለውይይት በመክፈት ህዝብንና ራሱን ተጠቃሚ ሊያደርግ ይገባል” ብለዋል።

“ባድመ በተወረረች ጊዜ የተፈጠረው ህብረት በስተመጨረሻ በክህደት መጠናቀቁ፣ በዜጎች አጥንትና ደም ላይ የአገር ብሔራዊ ጥቅም ተላልፎ እንዲሰጥ መደረጉና በበርካታ ቁልፍ አገራዊ ጉዳዮች ኢህአዴግ በህዝብና በአባላቱ ጭምር እምነት ያጣ ፓርቲ ነው” በማለት ኢትዮጵያ የከፋ ችግር ቢያጋጥማት እንዴት ልትቋቋም ትችላለች የሚል ስጋት እንዳላቸው አቶ ኦባንግ አመልክተዋል።

ስርዓቱ በየደረጃው በችግር የተተበተበና በህዝብ የማይታመን፣ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖችን እስር ቤት ያጎረ፣ በሰብአዊ መብት ጥሰት ከፍተኛ ቂም የተቋጠረበት፣ ፍትህና ርትዕ የተጓደለባቸው ያዘኑበት፣ በየአቅጣጫው ጠላት ያከማቸ፣ አገርን የሚፈትን አደጋ ቢፈጠር ህዝብን አስተባብሮ አደጋውን ለመመከት የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን የገለጹት አቶ ኦባንግ “ኢህአዴግ አጋጣሚውን አሁንም ሊጠቀምበት ይገባል” ሲሉ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ኦባንግ የሰማያዊ ፓርቲ ያስተባበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ ኢህአዴግ ክስ ለመመስረትና ዜጎችን ለማሰር እያደረገ ያለውን ዝግጅት በመቃወም ሰሞኑን ለአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ግልጽ ደብዳቤ መጻፋቸው ይታወሳል። ከደብዳቤያቸው በተጨማሪ ከተለያዩ አካላት ጋር በመነጋገር ኢህአዴግ ዜጎችን ከማሰሩ በፊት ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጉዳዮች መግባባት ላይ መደረሱን ጨምረው ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ የአባይ ግድብን አስመልክቶ በከፍተኛ ደረጃ ውዝግብ ውስጥ የገቡት ኢትዮጵያና ግብጽ መጨረሻቸው ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ በርካታ አስተያየትና ትንተና እየቀረበበት ነው። ሁለቱ አገሮች ወደ ጦርነት አያመሩም፤ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ከመጠቀም ውጪ ሌላ አጀንዳ የላቸውም የሚሉ ያሉትን ያህል ግብጽ በጦር አቅሟ ያላትን የበላይነት በማመልክት ባልታሰበ ሰዓት ጥቃት ለመፈጸም መዘጋጀቷን የሚያትቱም በርካታ ናቸው።

የግብጽ ፕሬዚዳንት ከተቃዋሚዎች ጋር ያደረጉትና ይፋ የተለቀቀው ቪዲዮ ላይ “ተቃዋሚዎችን በመርዳት ኢትዮጵያን ማተራመስ፣ ኢትዮጵያን መደብደብ ነው … ” በማለት ሲዝቱ የነበሩት ጽንፈኛ ጨምሮ የተለያዩ ባለስልጣናት የከረረ ቃላት ሲወረውሩ ሰንብተዋል። ኢትዮጵያም በበኩሏ የግብጽን አምባሳደር በማስጠራት ማብራሪያ እንዲሰጣትና በይፋ ይቅርታ እንድትጠይቅ ማዘዟን ይፋ አድርጋለች።

ግብጽ በችግር መተብተቧን፣ የሶማሌ መበታተንና፣ የሱዳን ሁለት አገር መሆን፣ የኤርትራ መሽመድመድ ኢትዮጵያን በቀጠናው ጉልበት ያላት አገር አድርጓታል የሚሉ ተንታኞች በበኩላቸው ግብጽ ወደ ጦርነት እንደማታመራ ሰፊ መከራከሪያ በማቅረብ ይናገራሉ። ከግድቡ ግንባታ ጀርባ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሚባሉ አገሮች እጅ እንዳለበትም የሚጠቁሙ ዘገባዎች በየፊናው ተሰራጭተዋል።

“ኤርትራ ተነፈሰች” የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች፣ አሁን በተፈጠረው ሁኔታ ግብጽ ተቃዋሚዎችን ለመርዳት ከተንቀሳቀሰች ኤርትራ ርዳታውን በማከፋፈልና ቀድሞውንም ቢሆን ኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነቷን የጠበቀች ጠንካራ አገር እንድትሆን ስለማትፈልግ በችግሩ ዙሪያ ቤንዚን ለማርከፍከፍ አጋጣሚው እንደሚመቻችላት ያስረዳሉ። የአረብ ሊግ የክብር አባል የሆነችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ጋር በተያያዘ በበርካታ ጉዳዮች የምትታማ አገር እንደሆነች የሚታወስ ነው።

ዘግይታ “እኔ ከግብጽ የተለየ አቋም ነው ያለኝ” በማለት የገለልተኛነት ስሜት እንዳላት ይፋ በማድረግ ለግብጽ የድጋፍ ጥሪ መልስ የሰጠችው ሱዳን እንደማትታመን የሚግለጹ ደግሞ “አቶ መለስ ደቡበን ሱዳን ላይ ሲከተሉ በነበረው አቋምና ደቡብ ሱዳን እንድትገነጠል በመናደረጓ ሱዳን አቂማለች” ይላሉ፡፡ እንደነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች ምንም ይሁን ምን በአገር ውስጥ ያለውን ችግር በውይይት በመፍታት ብሔራዊ አንድነትና ህብረትን ማጠናከሩ ለኢትዮጵያ እጅግ አስፈላጊዋ ነው። ስለዚህ “በር ይከፈት በአባይ ጉዳይ አገራዊ አቋም እንያዝ” የሚለው የአቶ ኦባንግ ብቻ ጥያቄ አይደለም።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Azieb says

    June 9, 2013 07:13 pm at 7:13 pm

    Because they wanted to use it in Abai Tigrai. And they were digging for the last 20 years.
    And they made it.

    Reply
  2. Minyewab says

    June 9, 2013 11:00 pm at 11:00 pm

    The Renaissance Dam is a Fake Project of TPLF regime

    The Renaissance Dam is another plot of TPLF to win the support of Ethiopian people. Yet again, in the same way TPLF won public support during the 1998 war with Eretria, the country it helped to create and as a result made Ethiopia the largest landlocked country in the world. You remember thousands celebrating in Meskel Square because TPLF falsely informed the Ethiopian people that Ethio-Eriterian Boundary commission decided Badme belonged to Ethiopia. That was a big lie we all caught by surprise when the truth came out. Don’t forget that war is not finished yet as TPLF arrogantly refused to accept the decision. Eritrea is only waiting for suitable time to reclaim Badme as per the boundary commission’s decision. There is armed struggle going on in every corner of the country and TPLF knows that its demise is the obvious reality that will come soon. So, its visionary leader planned how to keep TPLF in power for another decade and possibly more. The Renaissance Dam is just the kind of big project the unsuspecting and never learning Ethiopians fall for. What do they do? They swear to defend this fake project not realising that their government has only managed to raise 4% of the fund required for the completion of the dam. And the biggest lie of all is the regime is claiming, the dam will help to end the recurring hunger Ethiopians are suffering from. What a paradox. On one hand they say to Egypt that the dam is built to generate power, on the other hand they contradict this by saying it will raise millions out of hunger and poverty. I thought they said the dam was for generating power, not for irrigation! The true intention of TPLF is to kill two birds with one stone. One – Raise money from unsuspecting poor Ethiopians in the country and in the diaspora, two – win the support of the public in the name of national interest with some fake patriotism (patriotism, when it comes to Ethiopian national interest isn’t in the TPLF nature), and probably crush any dissent labelling them traitors. That will definitely ensure that TPLF will win the 2015 election again. That is The Grand Renaissance of TPLF in progress, not the dam. If the Ethiopians really want The Renaissance Dam to be a reality, first they have to get rid of TPLF. If you can’t see this, you have never known the evil genius in the TPLF leadership and you will all pay for your ignorance.

    Reply
  3. Finot says

    June 10, 2013 03:02 am at 3:02 am

    It is not Tana-Beles which was distructed. It was Gilgel-Beles.

    Reply
  4. koster says

    June 11, 2013 02:01 am at 2:01 am

    Ethiopians are already fighting the home grown fascists that is why thousands if not millions are languishing in Fascist torture chamber. 21 years of cheating is more than enough. We should learn from Badme and the next march should be to Menelik Palace to get rid the fascists not to Egypt or Eritrea. Tyrants use war to prolong their reign of Terror and should not loose Focus by all what woyane fabricates.

    Reply
  5. Sitotaw says

    December 15, 2016 06:20 pm at 6:20 pm

    Has our country, in its long history confronted an enemy worse than Woyane Tigres ? Is it conceivable that Tigres will ever be part of Ethiopia unless the Tigre folks who are spearheading the national destruction turn their guns on their leaders or force them to submit ?

    The Italian atrocities in which over a million Ethiopians were massacred during its invasion pales compared to what Woyane Tigres did. Not only have they perpetrated spates of genocide during their 25 years of terrorist tenure, but they have mortgaged or sold the future of our children too.

    Can these men and women ever escape justice?

    Reply
  6. Muluneh says

    February 8, 2024 11:41 am at 11:41 am

    እንባ ተናነቀኝ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule