• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት ግብጽ እና ለስልጣን ጸብ ጫሪው ህውሃት!

June 20, 2013 06:39 am by Editor 1 Comment

የአባይ ጉዳይ ለግብጽ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ነው። ዛፍ ላይ ሆነህ እንቅልፍ ይወስድሃል? ሸለብ እንኳን ያደርግሻል ዛፍ ላይ ሆነሽ? እነደዚያ ነው የአባይ ጉዳይ ለግብጽ። ይኽ እንቅልፍ ማጣት እና ስጋት ዛሬ የጀመረ አይደለም። ባጭሩ ልተርክ። ሪቻርድ ፓንክረስት በግብጽ የተገኙ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ክርስቶስ ከመወለዱ ከ3 ሺ አመቶች በፊት ጀመሮ የግብጽ ነጋዴዎች በእግራቸው የአባይን ወንዝ ዳርቻ ተከትለው እንዲሁም በቀይ ባህር በነፋስ በሚገፉ ጀልባዎች ዛሬ ኢትዮጵያ (ያኔ የፐንት ግዛት) በሚባለው ግዛት ውስጥ ከሚኖረው ህዝብ ጋር የንግድ ልውውጥ ማድረጋቸውን እና ግዛቱን ምድረ ታ-ኔትጄሩ (Land Ta-Netjeru) ማለትም “ምድረ አማልዕክት” እንደሚሉት እና “የመጀመሪያ አገራችን ነው” ይሉም እንደነበር የኢትዮጵያውያን ድንበር-መሬቶች (The Ethiopian Borderlands) በሚለው መጽሐፉ ዘርዘር አድርጎ ጽፏል። የቅርቡን ብንመለከት ደግሞ በተለይ ከ1813 ዓ. ም. ጀመሮ ግብጽ የኢትዮጵያ ባለቤትነቷን በጦርነት ለማረጋገጥ የዮሐንስን ኢትዮጵያ ከሱዳን ቀላቅላ ለመግዛት በአራት አቅጣጫዎች ወረራዎች ከፍታ ሳይሳካለት ወደ መጣችበት መመለሷን ተክለ ጻዲቅ መኩሪያ “ዐፄ ዮሐንስ እና የኢትዮጵያ አንድነት በሚለው መጽሐፉ በሰፊው ተርኳል። በኃይለስላሴ እና በደርግ ዘመንም ለኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች የጦር መሳሪያ እና ስልጠና በማቀነባበር፣ ገንዘብ በመለገስ፣ በመካከለኛው ምስራቅ አረብ አገሮችን በማስተባበር፣ የአማርኛ ስርጭት ሬዲዮ በመክፈት ድጋፍ ማድረጓን እናውቃለን። ህውሃት ከተጠቃሚዎቹ ተቃዋሚዎች ውስጥ አንዱ ነው። በአባይ ጉዳይ ከጥንት ጀምሮ ግብጽ ከስጋት ነፃ የሆነ እንቅልፍ የለታም። ዛሬም ሆነ ወደፊት ግብጽ የሰላሙን መንገድ ትታ የጸበኛነቱን መንገድ ከመረጠች እንቅልፍ አይኖራትም። ይኽን የግብጽ ጭነቀት እና ስጋት ህውሃት ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ ግንቦት 20 ቀን ጸብ ጫረ። ላብራራ።

የጥናቱን ውጤት ተቀበለችውም አልተቀበለችው ስለ አባይ ጉዳይ በጥናት ላይ የተሰማራው ኤክስፐርቶች ቡድን ሪፖርት እየጠበቀች ሳለች ድንገት ግንቦት 20 ቀን 2005 ዓ. ም. ህውሃት የአባይ ወንዝ የፍሰት አቅጣጫ መቀየሩን ሰበር ዜና ተሰራጨ። የኢትዮጵያ ሽብርተኛው ኢ.ት.ቭ. አስተጋባ። ዜናው ግብጽ ደረሰ። ከጥንት ጀምሮ የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት ግብጽ ተደናገጠች። አምባገነኑ ሞርሲ ከገበባት የውስጥ ችግር ለማምለጥ የህውሃትን ቁስቆሳ ተጠቀመ። አካራሪ የግብጽ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ጋበዞ ‘እኔ ሳልሞት ግብጽ አትጠማም’ አለ። ያጀቡት አክራሪዎችም ‘ግፋ’፣ ‘በርታ’፣ ‘አይዞህ ከጎንህ ነን’ አሉት። ይኽ  ምክክራቸው ዜና ሆኖ አደባባይ ወጣ። ህውሃት ሁካታውን ያልጫረ መስሎ ለኢትዮጵያ ህዝብ ግብጽ ልትወጋህ ነው የሚል ፕሮፖጋንዳ ጀመረ። የቀድሞ አባቶቻችን ድሎች ሳይቀሩ እየተጠቀሱ የቀረርቶ ድምጽ በአዲስ አበባ እየጎላ መጣ። አልባራዳይን የመሰሉት የግብጽ ዴሞክራሲ ኃይሎች የግብጽን መንግስት ወቀሱ። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎችም ቀረርቶው ገደብ ይበጅለት አሉ። የኢትዮ-ግብጽ የጦርነት ሁካታ አነሳሱ ይኽን ይመስል ነበር። ህውሃት የማያስፈልግ ጸብ ጭሯል።

ለመሆኑ ለምን የአባይ ወንዝ አቅጣጫ ግንቦት 20 ቀን ተቀየረ? ዜናውስ ለምን ግንቦት 20 ቀን አደባባይ ወጣ? ለዚኽ ጥያቄ አቶ በረከት ስሞዖን ሰኔ 7 ቀን ግድም 2005 የሰጠውን መግለጫ እንመልከት፥ የአባይ ወንዝ አቅጣጫ ግንቦት 20 ቀን የተቀየረው በአጋጣሚ እንጂ ህውሃት ሰልጣን ከጨበጠበት ቀን ጋር እንዲገጣጠም ሆን ተብሎ የተደረገ እንዳልሆነ ሊያስተባብል ሞክሯል። ይኽ የበረከት ስሞዖን ማስተባበያ በሽብርተኛው ኢ.ቲ.ቭ. እና በኢሳት ተዘግቧል። የአቶ በረከትን መቀላመድ ወደ ጎን አድርገን እውነቱን ሃቁን እንመልከት። የአባይ ወንዝ ፍሳሽ አቅጣጫ ግንቦት 20 ቀን እንዲቀየር ያስደረገው ህውሃት ነው። ዜናው ግብጽ እንዲደርስ ያደረገውም ህውሃት ነው። ግቡም ስልጣን ነው። ላብራራ!

1ኛ) የተለየ አሳቢ እና ከድኽነት ነፃ አውጪህ እኔ ህውሃት ነኝ የሚል መልዕክት ለኢትዮጵያ ህዝብ ለማስተላለፍ እንዲችል ሆን ብሎ የአባይ ፍሳሽ የተቀየረበትን ቀን ስልጣን ከጨበጠበት ግንቦት 20 ቀን ጋር አገጣጠመው። የዚኽ እርምጃ ፖለቲካዊ ግብ ህዝቡ እንዲያመልክበት እና ስልጣኑ እንዲጠናከር ነው። ግድብ መገንባት አይደለም ግቡ።

2ኛ) የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ለሆነባት ግብጽ የአባይ ፍሳሽ አቅጣጫ መቀየር ዜና የጦርነት ፖለቲካ ውስጥ እንደሚያስገባት ጠንቅቆ ስለሚያውቅ በምላሹ የኢትዮጵያን ህዝብ በአገር ወዳድነት ስሜት አሳውሮ በሚፈልገው የፖለቲካ አቅጣጫ ለማስጓዝ አስልቶ ነበር። የዚኽም ፖለቲካ ስሌት ግቡ የኢትዮጵያን ዴሞክራሲ ኃይሎች ለመምታት እና ስልጣኑን ለማጠናከር ነበር። በአገር ከሃዲነት እና በሽብርተኛነት ሽፋን። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች ፈጥነው ስላጋለጡት የኢትዮጵያን ህዝብ በአባይ ስሜት አሳውሮ የዴሞክራሲ ኃይሉን ለመምታት የሚያስችለው ጊዜ ሳያገኝ ቀረ። ከሸፈበት።

ግርማ ሞገስ
ግርማ ሞገስ

ህውሃት ከግድቡ ይልቅ ስልጣኑ እንደሚበልጥበት ለአንዲት ደቂቃ እንኳን መዘንጋት አያስፈልግም። ወደፊትም ሌሎች ጸቦች ሊጭር እና ከዚያ ግብጽ ልትወጋን ነው ይልሃል። የዴሞክራሲ ኃይሎች የነፃነት ሰላማዊ ትግላቸውን አጠናክረው በመቀጠል እራሳቸውን ከህውሃት ማጭበርበር እና ጥቃት መጠበቅ አለባቸው።

(girmamoges1@gmail.com)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    June 21, 2013 12:51 am at 12:51 am

    የአባይን ወንዝ የፍሰት አቅጣጫ ማስቀየስ ከተያዘለት ዕቅድ ሁለት ሳምንት ቀደም ብሎ ልክ ግንቦት ፳ቀን ዋለ!። ኢህአዴጋዊ ኢንጂነሪንግ…ዜናው ግብጽ እንዲደርስ ያደረገውም ህውሃት ልማታዊ መንግስት በድል ቀን ድል ለማብሠር የኢትዮጵያን ህዝብ በአገር ወዳድነት ስሜት አሳውሮ በሚፈልገው የፖለቲካ አቅጣጫ ለማስጓዝ አስልቶ ነበር።…
    ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም “አብረን እንዋኛለን?ወይንስ አብረን እንሰምጣለን ? ወያኔ ከዕርዳታ ሰጭ ሀገራት የሚያመልጥበት፣በአሜኒስቲ ኢንተርናሽናል የማይቀወቀስበት፣በአበዳሪ ሀገሮች ተግፃፅ የማይደረስበት…ዘመን ተሻጋሪ.. ትውልድ አምካኝ …ሀገር አጥፊ የሚመለምልበት ታላቁ የገቢ ማንጭ መብራት ሸጦ ነዳጅ እየቀዳ የጦር ኅይሉን የሚያጠናክረበት የሙስና ፋውንዴሽን በዚህ ግድብ መሳካት ብቻ ነው ብሎ በቁርጠኝነት ትውልዱን ለማጭበርበር ታጥቋል ።
    ዴያስፖራው: ቱል-ቱል ሲል
    ቦንደኞች ፡ጡል -ጡል
    አርቲስቱ :ብጉል- ቡጉል
    ሟቹ :ዊን ዊን
    ካድሬው :ቂን-ቂን
    ካይሮ ፡ ፊን -ፊን
    ብሔር ፡ ዝልል- ዝልል
    ኢንቨስተር :ውጥር- ውጥር
    የተገረምን :ጥርጥር- ጠርጠር
    ወያኔ ፡ሰጥቶ- መቀበል
    ያልገባን ፡ ዘራፍ – ዘራፍ
    ********ጦርነት በሌለበት ፡የወሬ ፈረስ ጫንን…በዝናብ አቧራ ላስነሳን..በተንገረበበ ቤት ጅብ ለጋበዝን…እናም ታዘብን!!?*****
    “እኛም አውቀናል ጉድጓድ ምሠናል አለች አሉ…(ግድበ መቃወም)እና ከእንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ከናዳ፣ ቻይና፣ ከዓረብ፣ እኩል ቦንድ ገዝቼ የባለቤትነት ሠርተፍኬት ይሰጥኝ ማለት ትልቅ ልዩነነት አለው በለው። አራት ነጥብ። ሁለቱ ሀገራት በመን ተስማሙ አንዱ ልግደልህ ሲለው ቆይቶ ሌላው አልሞትም እገልሃለው ሲል በሳምንት ውስጥ ተስማሙ? “ገዳይ መግደሉን እገልሃለሁ ግን ድምፅ በሌለው መሳሪያ ነው ሲለው…ሟች ለመሞት እስማማለሁ ግን ድምፅ የሌለውን መሳሪያ የመምረጥ ሙሉ መብቴ በባለሙያ አስጠንቼ የማቅረብ መብቴ ይጠበቅልኝ ቢቻል መሳሪያውን ላቅርብ (ሰጥቶ መቀበል)ይሁን ሲል ተስማማ።!! እሰይ በዓለም ለየት ያለ ፈጣን ከዊን ዊን፣ ቂን ቂን፣ ከዚያማ እግር ላይ ድፍት!…አቤት አቀባበል ተምች በለው!
    የዓባይ ጉዳይ እኛ ዜጎችም ያገባናል። ግልፅና ተጠያቂነት ይኑር ህዝብ የመጠየቅ፣ የማወቅ፣የማይሸራረፍ፣ የማይበረዝና የማይከለስ ሙሉ መብት አለው!!።
    *************************************************************
    የኢትዮዽያ መንግስት አቋም :
    (1) የግድቡ ግንባታ እንደማይቆም፣
    (2) ግድቡ ወደ ግብፅ የሚሄደው የውሃ መጠን እንደማይቀንስ (ይሄ እንኳ አቋም አይደለም ማብራርያ እንጂ)
    (3) ኢትዮዽያ የድሮ የውሃ አጠቃቀም ውል እንደማትቀበልና የዓባይ ዉሃ ለኤለክትሪክ ሃይል ማመንጫ የመጠቀም መብት እንዳላት ወዘተ …።
    (፬) ኢትዮዽያ ግን ጉዳዩ በሰለማዊ መንገድ ወይ በድርድር መፈታት እንዳለበት ትገልፃለች።
    ግብፅ ጉዳዩ ለመፍታት ያስቀመጠቻቸው የድርድር ነጥቦች:
    (፩) ድርድሩ እስኪካሄድና መፍትሔ እስኪገኝ ድረስ የግድቡ ግንባታ ‘መቆም’ እንዳለበት፣
    (፪) የግድቡ መጠን ከ74 ቢልዮን ኲቢክ ሜትር ወደ 14 ቢልዮን ኲቢክ ሜትር ዝቅ ማለት እንዳለበት (ይህንን ቅድምያ የሚሰጡት ነው)፣ከዛ በኋላም
    (፫) የግድቡ ዲዛይን በግብፅ ባለሞያዎች መፈተሽ እንዳለበት … ወዘተ ያስቀምጣሉ።
    (፬)ግብፅ (የውሃ ደህንነት) ለማስከበር ‘ማንኛውም ዓይነት መንገድ’ (የሃይል እርምጃ ወይ ጦርነት ጭምር መሆኑ ነው)
    ******************
    (ሀ) “… ቀደም ብሎ በነበረው ስምምነት መሰረት አለም አቀፉ የባለሙያዎች ፓናል ባቀረባቸው የወደፊት ሀሳቦች ላይ ሱዳንን በመጨመር የሶስትዮሽ ምክክር ለመቀጠል ተስማምተዋል”
    (ለ) “አለም አቀፍ የባለሙያዎች ፓናልን በተመለከተ ባስቀመጥነው አሰራር መሰረት የአጥኝ ቡድኑ ያወጣቸውን የወደፊት ሀሳቦች ለመተግበር ተስማምተዋል፡፡”
    (ሐ) “‘በዓባይ ጉዳይ በቀላሉ መስማማት የሚቻለው ቢያንስ አንደኛው ወገን ብሄራዊ ጥቅሙ አሳልፎ ሲሰጥ ብቻ ነው’
    **በግብፅ በዓባይ ጉዳይ ጥናት ያካሄዱና ብዙ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎችና ተቋማት መዓት ናቸው። በኢትዮዽያ አንድም ተቋም የለም። በግብፅ ብዙ ባለሙያዎች የፖለቲከኞች አማካሪዎች ናቸው። የኢትዮዽያ መንግስት ባለሙያዎች አያስተናግድም። በግብፅ ማንኛውም ፖሊሲ ጥናት መሰረት ያድረገ ነው። በኢትዮዽያ ሁሉም ነገር በደመ ነፍስ ነው።
    አሁም ሁለቱም ሀገሮች የተስማሙበት የቴክኒክና የፖለቲካ ድርድር ለግብፅ ትልቅ ድል ነው።አሁን የኢትዮዽያ መንግስት ማድረግ ያለበት ሁሉንም ኢትዮዽያውያን ባለሙያዎች እንዲሳተፉ መጋበዝ፣ ወቅታዊ መረጃዎች በግዜውና በአግባቡ ለህዝብ መስጠት፣ ግድቡ ለፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ብቻ አለማዋል ፤ የሀገር ጉዳይ ነውና የሁሉም ዜጎች ደህንነት ያለ አድልዎ ይጠብቅ፤ ሀገር የሚጠብቁና የሚገነቡ ዜጎች ናቸውና ፍትህም እንደተጠበቀ ሆኖ ያለ ዜጎች ደህንነትና ኅብርት እንኳን ግድብ ሀገርም አይኖርም !! ። በለው! በቸር ይግጠመን ከሀገረ ካናዳ
    (“የኢትዮጵያ አቋምና የአባይ ፖለቲካ” የተሰኛውን ጽሑፍ ያቀረቡትን ግለሰብ አደንቃለሁ ከምስጋና ጋር!)

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule