• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአባይ ግድብ ዲፕሎማሲ አጀንዳ!

June 21, 2013 07:17 am by Editor Leave a Comment

በአለም አቀፍ ደረጃ እንደ አባይ ግድብ አወዛጋቢ የሆኑ ጉዳዮች ተፈጻሚነት የሚያገኙት አለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ትግል በማድረግ አለም አቀፍ ደጋፊ ማብዛት ሲቻል ነው። የዲፕሎማሲ ትግል ደግሞ ሰላማዊ ትግል ትግል በመሆኑ ብስለት እንጂ ክፉ ቃል አይሻም። ቀረርቶ ደጋፊን አስበርግጎ እንደሚያርቅ እና ለባላንጣ የማጥቂያ ቀዳዳ እንደሚከፍት ግልጽ ነው። የሆነው ሆኖ ይኽን ጽሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ የህውሃት ውጭ ጉዳይ ቴዎድሮስ እና አቻው የግብጹ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰኔ 11 ግድም ዲፕሎማሲያዊ ውይይት አደረጉ ከተባለ በኋላ ቴዎድሮስ “አብረን እንዋኛለን ወይንም እንሰምጣለን” ማለቱን ካነበብኩ በኋላ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ኃይሎች ጋር ውይይት መክፈት ያስፈልጋል የሚል እምነት ስላደረብኝ ነው።

“አብረን እንዋኛለን ወይንም እንሰምጣለን” የሚለው የቴዎድሮስ አባባል “ግብጽ እና ኢትዮጵያ ላይፋቱ ተጋብተዋል” ከሚለው የአምባገነን መሰል አባባል ብዙም የራቀ አይደለም። ሁለቱም ህውሃታዊ አነጋገሮች ናቸው። ስሜት በመቀስቀስ ኢትዮጵያውያንን ለማስከተል እና ስልጣን ለማጠናከር። የቀድሞው የህውሃት ውጭ ጉዳይ ስዩም መስፍን በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ምን ሲል እንደነበር፣ በመጨረሻ ግን ጦርነቱ እና የባድመ ጉዳይ እንዴት እንዳከተመ እናስታውሳለን። ቴዎድሮስም ከስዩም መስፍን የተለየ አደለም። ትናንት ኤርትራን አስገነጠሉ። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትም አብረው ነበሩ። ዛሬም አብረው ናቸው። የሆነው ሆኖ የዲፕሎማሲ ትግል ‘አብረን እንዋኛለን ወይንም እንሰምጣለን” ከሚለው  አባባል ባሻገር እጅግ ሰፋ ያለ ነው። የዲፕሎማሲ ትግል ህግ፣ ፍትህ፣ ታሪክ፣ ሳይንስ፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ሰበዓዊ እና ግብረገባዊ አድማሶች ያሉት የትንታኔ፣ የክርክር፣ የማግባባት፣ የማሳመን ትግል ነው። በተጨማሪ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ከልብ መደረግም አለበት።

ከ1938 እስከ 1945 ዓ.ም.  በነበረው በዚያ በጨለማ ዘመን እንኳን እነ ሎሬንዞ እና አክሊሉ ኃብተ ወልድ ከአለም አቀፍ ህግ አማካሪያቸው ከስፔንሰር ጋር ሆነው ኤርትራን ከኢትዮጵያ ለመቀላቀል ባደረጉት ዲፕሎማሲያዊ ትግል የእነ ካናዳን፣ ህንድን፣ ኖርዌይን፣ ግሪክን እና ሌሎች በርካታ አገሮችን ድጋፍ ሊያገኙ የቻሉት ዲፕሎማሲያዊ ትግላቸው በሳል በመሆኑ ነበር። ከልባቸው ያደረጉትም ትግል ስለነበር ነው። በቅድሚያ በምርምር እና በጥናት የተመሰረተ በሳል የዲፕሎማሲ ትግል አጀንዳዎች በመቅረጻቸው ነበር። ዛሬ ጊዜውም እንደያኔ ጨለማ አይደለም። የኃያላን መንግስታት አስተሳሰብ ከቅኝ ገዥነት በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ተለወጧል። ዛሬ አፍሪካውያን በተባበሩት መንግስታት ከ50 በላይ መቀመጫ አላቸው። ያኔ እነ ሎሬንዞ እና አክሊሉ ኃብተ ወልድ በተባበሩት መንግስታት መድረክ ለኢትዮጵያ ከልባቸው ሲታገሉ መቀመጫ የነበራቸው እና የድጋፍ ድምጽ የሚሰጡዋቸው ኢትዮጵያ እና ላይቤሪያ ብቻ ነበሩ። ለፍትህ የሚደረግ የዲፕሎማሲ ትግል ከዚያ ከጨለማ ዘመን ይልቅ ዛሬ የማሸነፍ እድሉ ከፍተኛ ነው። ሆኖም ግን በሳል የዲፕሎማሲ ትግል አጀንዳዎች መቀመር እና ከልብ መታገል ያስፈልጋል።

ኢትዮጵያ የምታካሂደው የዲፕሎማሲ ትግል ከግብጽ ሳይንትስቶች፣ መሃንዲሶች፣ የህግ አዋቂዎች እና የዴሞክራሲ ኃይሎች ጋር ውይይት መክፈት ቢችል እና በአለም አቀፍ መድረክ ደግሞ የአፍሪካ ህብረትን፣ የተባበሩት መንግስታትን፣ የአሜሪካን፣ የአውሮፓን፣ የአለም ባንክን፣ የአይ.ኤም.ኤፍን ድጋፍ ማግኘት ቢችል ግንባታው ቀላል ይሆናል። ስለዚህ የዲፕሎማሲ ትግሉ ጥናት ላይ የተመሰረቱ አጀንዳዎች ሊኖሩት ይገባል።  የቀድሞ አባቶቻችንን ድሎች እየጠቀሱ እኛም እንደግመዋለን አይነት አኪያሄድ አይጠቅምም። የሚከተሉት የዲፕሎማሲ አጀንዳዎች ለኢትዮጵያ አባይ ግድብ ግንባታ ዲፕሎማሲ ትግል ሊያገለግሉ ይችላሉ የሚል እምነት አለኝ፥

አጀንዳ አንድ (1)፥ ግድቡ በሸለቋማ ቦታ ላይ በመገንባቱ በትነት የሚባክነውን ውሃ ዝቅተኛ ያደርጋል።

አጀንዳ ሁለት (2) በግድቡ የሚሰበሰበው ውሃ ቁልቁል ሲለቀቅ መዘውሮችን (Turbines) በመምታት ያመቀውን ኃይል (Energy) ወደ መዘውሮቹ ካስተላለፈ (እንዲሽከረከሩ በማድረግ) በኋላ የሚስፈነጠረው ውሃ ወደ ኢትዮጵያ ሳይሆን ወደ ሱዳን ስለሚፈስ ወደ ግብጽ የሚሄደው የአባይ ውሃ አይቀንስም።

አጀንዳ ሶስት (3)፥ ግድቡን ለመሙላት የሚያስፈልገው ውሃ በግብጽ ላይ ስጋት መፍጠር የለበትም። በበጋም ሆነ በክረምት ወደ ግብጽ የሚፈሰው የአባይ ውሃ ግብጽን አልፎ ሜድትራኒያን ባህር ስለሚገባ የኢትዮጵያ፣ የሱዳን እና የግብጽ ሳይንትስቶች እና መሃንዲሶች ከአለም እክስፐርቶች ጋር ሆነው ምን ያህል ውሃ ግድቡ ውስጥ እንዲቀር ማድረግ እንደሚቻል ማስላት ይችላሉ። ግድቡን ለመሙላት ከበጋ ይልቅ በክረምት ከፍ ያለ የውሃ ማስቀረት እንደሚቻል ግልጽ ነው።

አጀንዳ አራት (4)፥ ከአባይ ወንዝ ውሃ በተጨማሪ ከሱዳን የኤሌክትሪክ መስመሮች ጋር በመተሳሰር ግብጽ የምታገኘው ተጨማሪ ጠቀሜታ እንዳለም የግብጽ እና የአለም ህዝብ እንዲያውቅ ዲፕሎማሲያዊ ቅስቀሳ መደረግ አለበት። ለምሳሌ ግብጽ እና ጆርዳን የኤሊክትሪክ መስመራቸውን አስተሳስረዋል። የኤሌክትሪክ መስመሮቻቸውን ለማስተሳሰር በየብስ ከግብጽ ወደ ጆርዳን በመማዎች ማጓጓዝ ስላልቻሉ ከፍተኛ ወጪ አውጥተው መስመሩን በቀይ ባህር ወለል ስር ቀብረው የሁለቱን አገሮች የኤሌክትሪክ መስመሮች አስተሳስረው የኤሊክትሪክ ኃይል ይነጋገዳሉ። በቅርቡ ደግሞ ግብጽ ከሳውዲ ጋር ለማስተሳሰር ስምምነት ጨርሳለች። ግብጽ ለጆርዳን ከምተሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ የተወሰነው የኤሊክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ የሚፈሰው አባይ አስዋን ግድብ ላይ ከሚፈጥረው 2 ሺ አንድ መቶ ሜጋ ዋት መሆኑን አንባቢ ልብ ይበል።

አጀንዳ አምስት (5) ፥ የ 09 JUNE 2013 ሪፖርተር ጋዜጣ ከቀድሞ ዲፕሎማት አምባሳደር ኃይሉ ወልደ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገችው  ቆይታ የውሃ አጠቃቀምን አለም አቀፍ ህግ አስመልክታ ላቀረበችላቸው ጥያቄ አምባሳደሩ መልስ “በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስብሰባ ላይ በ101 የድምፅ ድጋፍ፣ በሦስት ተቃውሞና በ27 ድምፀ ተአቅቦ ያለፈው የውኃ ኮንቬንሽን የኢትዮጵያን አቋም የሚደግፍ ነው፡፡” ይህን ሁሉ የግብጽ ህዝብ እንዲያውቅ ይደረግ።

አጀንዳ ስድስት (6)፥ ግብጽ ከመቶ አመቶች በኋላ የህዝቤ ብዛት 3 መቶ ሚሊዮን ወይንም ከዚያ በላይ ሊሆን ይችላል ከሚል የተደበቀ ስሌት አባይ ይለቀቅልኝ ማለት እንደማትችል ግልጽ መሆን አለበት።

አጀንዳ ሰባት (7)፥ የቅኝ አገዛዝ ዘመንን ውል ኢትዮጵያ እንደማትቀበል በጠዋት ግልጽ መደረግ አለበት። የአባይ ውሃ ባለቤትነት እና የመጠቀም መብታችንን ለድርድር እንደማናቃረብ ህግን፣ ታሪክን፣ ፖለቲካን፣ ኢኮኖሚን እና ግብረገብነትን መሰረት ያደረጉ ትንታኔዎች ማቅረብ።

አጀንዳ ስምንት (8)፥ ግብጽ የሚገባው ነጭ አባይ 85% ያህሉን ውሃ የሚያገኘው ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን ከሚፈሱት ጥቁር አባይ (70%)፣ ተከዜ (5%) እና ባሮ (10%) ወንዞች ነው። እነዚህ ሶስት አውራ ወንዞች የሚፈጠሩት በኢትዮጵያ ከተለያዩ ቦታዎች ከሚነሱ በርካታ ገባር ወንዞች ነው። ግብጽ በጸበኛነት የምትቀጥል ከሆነ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ከየአካባቢው የሚነሱትን ትናንሽ ገባር ወንዞች አቅጣጫ ይቀይራል። ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን የሚፈሰው ውሃ መጠን እጅግ ዝቅ ይላል። ግብጽ በወታደራዊ ኃይል የባሮ ወንዝ ከሚገኝበት ደቡብ ምዕራብ ጀምሮ እስከ ሰሜን ምዕራብ ድረስ ሁልጊዜ መዋጋት አትችልም። ይኽን ሃቅ ግብጾች፣ አሜሪካ፣ አውሮፓ፣ የአለም ባንክ፣ አይ.ኤም.ኤፍ. ሁሉ እንዲገነዘቡት እና የግብጽ ጸበኛነት የማያዋጣ መሆኑ ወለል ብሎ እንዲታያቸው ማድረግ።

አጀንዳ ዘጠኝ (9)፥ ግብጽ ጦርነት ከመረጠችም ከምታገኘው ጥቅም ይልቅ የሚደርስባት ኪሳራ ብዙ ነው። ጦርነት ለማኪያሄድ የምታወጣው እና በጦርነት ጀማሪነት እንዲሁም ለደረሰችው ጉዳት የተባበሩት መንግስታት ይቀጣታል።

አጀንዳ አስር (10)፥ ኢትዮጵያ እራስዋን የመከላከል መብቷ የተከበረ መሆኑንም የዲፕሎማሲው ትግል ጨምሮ ይገልጻ።

እነኚህ አስር (10) አጀንዳዎች ቢተነተኑ ትልቅ ሰነድ እንደሚወጣቸው ግልጽ ነው። እነዚኽን አሳቦች ካለቀረርቶ ለግብጻውያንም ሆነ ለአለም ህዝብ ወዝ እና ቁርጣኛነት በግልጽ በሚታይበት አነጋገር በማቅረብ ቢያንስ የግብጽን የተወሰነውን የዴሞክራሲ ኃይል ድጋፍ ማግኘት እና አለም አቀፍ ደጋፊዎችን ብዛት ማሳደግ እንደሚቻልም ግልጽ ነው።

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች ዲፕሎማሲያዊ ትግላቸውን እንዴት ማኪያሄድ ይችላሉ? በብዙ መንገዶች ማኪያሄድ ይችላሉ። በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ምሁራን የሚዘጋጁ የበሰሉ የምርምር ጽሑፎችን እና የዲፕሎማሲ ትግሉን ሂደት ደረጃዎች እየተከታተሉ እነ አንድነት ፓርቲ፣ ሰማያዊዎች እና ሌሎች የዴሞክራሲ ኃይሎች የሚያወጧቸውን መግለጫዎች በየድረገጹ በማቅረብ። ድረገጾቹ ለግብጽ ዴሞክራሲ ኃይሎች፣ ለአሜሪካ፣ ለአውሮፓ ዲፕሎማቶች እና የቀድሞው የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ለነበረው ለነ መሐመድ አልባራዳይ አይነቱ የግብጽ ዴሞክራሲ ኃይሎች ተደራሽነት ቢኖራቸው ጥሩ ነው። የቀድሞው የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበረውን መሐመድ አልባራዳይ እና ሌሎች ግብጻውያንን በመጋበዝ ህዝብ ለህዝብ የሚሉ ጉባኤዎች በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አዘጋጅቶ መነጋገርም ይቻላል። ተደጋጋሚ ቢሆን ጥሩ ነው። በአለም ውስጥ የተሰራጩት ኢምባሲዎች ይኽን አይነቱን ዲፕሎማሲያዊ ቅስቀሳ ቀደም ብለው ማድረግ ነበረባቸው። ችግሩ ህውሃት (ቴዎድሮስ አድሃኖም እና ገብረ ክርስቶስ ) ያላዘዛዋቸውን አያደርጉም።

ስለዚህ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች በአባይ እና በአገራቸው ጉዳይ የዲፕሎማሲ ትግሉ ባለቤት መሆን አለባቸው። አንድ ነገር በግልጽ መታወቅ አለበት። የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ኃይሎች በራሳቸው አነሳሽነት መራመድ ካልጀመሩ ህውሃት የዲፕሎማሲ ትግል አጋር እንዲሆኑም ሆነ ወደፊት በሚደረጉ ምርጫዎች በነፃ ተፎካክረው ስልጣን እንዲጋሩት ወይንም አሸንፈውት አገር እንዲያስተዳድሩ ፍጹም አይፈልግም። የዴሞክራሲ ኃይሎች ከዳር ቆሞ ተመልካችነትን ከመረጡ የኢትዮጵያ ህዝብም በአባይ ጉዳይ ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ያለኝ ጠበቃ እና ጠባቂ ህውሃት ብቻ ነው የሚል አደገኛ እምነት ሊፈጠር ይችላል። የህውሃትም ፍላጎት የኢትዮጵያ ህዝብ በህውሃት ላይ እንዲያመልክ ማድረግ ነው። ስለዚኽ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች የአባይም ሆነ የኢትዮጵያ ባለቤትነታቸውን እና ሌሎች የሚጠበቁባቸውን ህዝብ የመምራት ግዴታዎች ለመወጣት ህውሃት የዘጋባቸውን በር እስኪከፍትላቸው መጠበቅ የለባቸውም። የመግለጫ ጋጋታም ህውሃት የዘጋውን በር አይከፍትልህም። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ሰራዊት ህውሃት የዘጋውን በር እራስህ ከፍተህ በአገርህ ጉዳይ በአቻነት መሳተፍ መጀመር አለብህ! በህዝብህም ዘንድ ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ መታወቅን እና ክብርን የሚያስገኝልህ ብሎም ፕሮግራምህን ተፈጻሚ ማድረግ የምትችለው እንደነዚህ አይነት ስራዎች ስትሰራ ብቻ ነው!

(girmamoges1@gmail.com)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule