• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በፓኪስታን የ9 ወር ህጻን በመግደል ሙከራ ተከሰሰ

April 7, 2014 07:41 am by Editor 1 Comment

ባለፈው ሳምንት በፓኪስታን ላሆር ከሌሎች ቤተሰቦቹ ጋር የ9 ወር ህጻን በመግደል ሙከራ ተከስሶ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ ህጻኑ ከነጡጦው በፍርድ ቤት መዝገብ ላይ በአያቱ እርዳታ ጣቱን በቀለም አጥቅሶ ከፈረመ በኋላ ዳኛው ጊዜያዊ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ በማድረግ ለሚያዚያ 4 ቀጠሮ ሰጥተውታል፡፡

ህጻኑና ወደ25 የሚጠጉት ቤተሰቦቹ የተከሰሱት በፖሊስ ላይ ድንጋይ በመወርወርና የፖሊስ ኃይሎችን ለመግደል ሞክረዋል በሚል ነው፡፡ በላሆር የሚገኙ ነዋሪዎች የጋዝና የኤሌክትሪክ ክፍያ ባለመፈጸማቸው ውዝፍ ዕዳ ስለተጠራቀመባቸው የጋዝና የኤሌክትሪክ መስመሮቹን ለመቁረጥ የፖሊስ ኃይል ወደሥፍራው የዛሬ ሁለት ወር አካባቢ ተንቀሳቅሶ ነበር፡፡ በሁኔታው የተናደዱ የአካባቢው ነዋሪዎች በፖሊስ ቡድኑ ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ከማድረስ አልፎ የተወሰኑት ላይ ጉዳት አድርሰው ነበር፡፡

babyክስተቱን ለፍርድቤት በማቅረብ ክስ የመሰረተው የፖሊስ ኃይል በወቅቱ በጥቃቱ ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን 25 ግለሰቦችን ሲከስ ህጻኑን እና ቤተሰቦቹ አብሮ ለክስ አቅርቧል፡፡

ህጻኑም በአያቱ ታቅፎ ፍርድቤት በቀረበበት ወቅት በፍርድቤቱ መዝገብ ላይ በጣቱ ፈርሟል፡፡ ክሱን የተቃወመው የቤተሰቡ ጠበቃ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደተናገረው ፍርድቤቱ በተለይ በህጻኑ ላይ የተመሰረተውን ክስ ወዲያውኑ ውድቅ ማድረግ ነበረበት ብሏል፡፡ ይህንን አለማድረጉ በራሱ የፖሊስ ኃይላችንና የፍትህ አካላቶች ምን ያል ብቃት እንደሌላቸው የሚያጋልጥ ነው በማለት ተቃውሞውን ገልጾዋል፡፡

አብሮ ለፍርድ የቀረበው የህጻኑ አባት ፖሊስ የሃሰት ክስ እንደመሠረተባቸው በመጥቀስ የልጁን መከሰስ አጥብቆ ተቃውሟል፡፡ “እኛ በወቅቱ አንከፍልም ብለን የተቃወምነው ኤሌክትሪክ በሰፈራች ሳይኖር ወርሃዊ ክፍያ ፈጽሙ በመባላችን” ነው በማለት የክሱን ኢፍትሃዊነት አስረድቷል፡፡

ህጻኑ ከሌሎቹ ተከሳሾች ጋር በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ፍርድቤት እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ ዜናው ይፋ ከሆነ በኋላ በተለይ ህጻኑ ላይ ክስ እንዲመሠረት ያደረገው የፖሊስ አባል ከሥራው እንዲገለል ተደርጓል፡፡

ባለፈው ዓመት በተሻሻለው የፓኪስታን ሕግ መሠረት በወንጀል የሚከሰሱ የመነሻ ዕድሜ ከ7 ዓመት ወደ 12ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ይህንን ሕግ በመጻረር ዳኛው በህጻኑ ላይ ክሱ እንዲመሠረት መፍቀዳቸው የበርካታ ሚዲያዎች መወያያ ርዕስ ሆኗል፡፡

(ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ዜናውን ከተለያዩ ዓለምአቀፍ ምንጮች እንደዘገበው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. jarso says

    April 16, 2014 03:16 am at 3:16 am

    What is the big deal here ? we have witnessed in our very eyes while the woyane butchers killing thousands of children in Ethiopia and several of them thrown in jungle to be eaten by hungry hyenas .

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule