• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በፓኪስታን የ9 ወር ህጻን በመግደል ሙከራ ተከሰሰ

April 7, 2014 07:41 am by Editor 1 Comment

ባለፈው ሳምንት በፓኪስታን ላሆር ከሌሎች ቤተሰቦቹ ጋር የ9 ወር ህጻን በመግደል ሙከራ ተከስሶ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ ህጻኑ ከነጡጦው በፍርድ ቤት መዝገብ ላይ በአያቱ እርዳታ ጣቱን በቀለም አጥቅሶ ከፈረመ በኋላ ዳኛው ጊዜያዊ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ በማድረግ ለሚያዚያ 4 ቀጠሮ ሰጥተውታል፡፡

ህጻኑና ወደ25 የሚጠጉት ቤተሰቦቹ የተከሰሱት በፖሊስ ላይ ድንጋይ በመወርወርና የፖሊስ ኃይሎችን ለመግደል ሞክረዋል በሚል ነው፡፡ በላሆር የሚገኙ ነዋሪዎች የጋዝና የኤሌክትሪክ ክፍያ ባለመፈጸማቸው ውዝፍ ዕዳ ስለተጠራቀመባቸው የጋዝና የኤሌክትሪክ መስመሮቹን ለመቁረጥ የፖሊስ ኃይል ወደሥፍራው የዛሬ ሁለት ወር አካባቢ ተንቀሳቅሶ ነበር፡፡ በሁኔታው የተናደዱ የአካባቢው ነዋሪዎች በፖሊስ ቡድኑ ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ከማድረስ አልፎ የተወሰኑት ላይ ጉዳት አድርሰው ነበር፡፡

babyክስተቱን ለፍርድቤት በማቅረብ ክስ የመሰረተው የፖሊስ ኃይል በወቅቱ በጥቃቱ ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን 25 ግለሰቦችን ሲከስ ህጻኑን እና ቤተሰቦቹ አብሮ ለክስ አቅርቧል፡፡

ህጻኑም በአያቱ ታቅፎ ፍርድቤት በቀረበበት ወቅት በፍርድቤቱ መዝገብ ላይ በጣቱ ፈርሟል፡፡ ክሱን የተቃወመው የቤተሰቡ ጠበቃ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደተናገረው ፍርድቤቱ በተለይ በህጻኑ ላይ የተመሰረተውን ክስ ወዲያውኑ ውድቅ ማድረግ ነበረበት ብሏል፡፡ ይህንን አለማድረጉ በራሱ የፖሊስ ኃይላችንና የፍትህ አካላቶች ምን ያል ብቃት እንደሌላቸው የሚያጋልጥ ነው በማለት ተቃውሞውን ገልጾዋል፡፡

አብሮ ለፍርድ የቀረበው የህጻኑ አባት ፖሊስ የሃሰት ክስ እንደመሠረተባቸው በመጥቀስ የልጁን መከሰስ አጥብቆ ተቃውሟል፡፡ “እኛ በወቅቱ አንከፍልም ብለን የተቃወምነው ኤሌክትሪክ በሰፈራች ሳይኖር ወርሃዊ ክፍያ ፈጽሙ በመባላችን” ነው በማለት የክሱን ኢፍትሃዊነት አስረድቷል፡፡

ህጻኑ ከሌሎቹ ተከሳሾች ጋር በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ፍርድቤት እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ ዜናው ይፋ ከሆነ በኋላ በተለይ ህጻኑ ላይ ክስ እንዲመሠረት ያደረገው የፖሊስ አባል ከሥራው እንዲገለል ተደርጓል፡፡

ባለፈው ዓመት በተሻሻለው የፓኪስታን ሕግ መሠረት በወንጀል የሚከሰሱ የመነሻ ዕድሜ ከ7 ዓመት ወደ 12ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ይህንን ሕግ በመጻረር ዳኛው በህጻኑ ላይ ክሱ እንዲመሠረት መፍቀዳቸው የበርካታ ሚዲያዎች መወያያ ርዕስ ሆኗል፡፡

(ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ዜናውን ከተለያዩ ዓለምአቀፍ ምንጮች እንደዘገበው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. jarso says

    April 16, 2014 03:16 am at 3:16 am

    What is the big deal here ? we have witnessed in our very eyes while the woyane butchers killing thousands of children in Ethiopia and several of them thrown in jungle to be eaten by hungry hyenas .

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule