• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በፓኪስታን የ9 ወር ህጻን በመግደል ሙከራ ተከሰሰ

April 7, 2014 07:41 am by Editor 1 Comment

ባለፈው ሳምንት በፓኪስታን ላሆር ከሌሎች ቤተሰቦቹ ጋር የ9 ወር ህጻን በመግደል ሙከራ ተከስሶ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ ህጻኑ ከነጡጦው በፍርድ ቤት መዝገብ ላይ በአያቱ እርዳታ ጣቱን በቀለም አጥቅሶ ከፈረመ በኋላ ዳኛው ጊዜያዊ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ በማድረግ ለሚያዚያ 4 ቀጠሮ ሰጥተውታል፡፡

ህጻኑና ወደ25 የሚጠጉት ቤተሰቦቹ የተከሰሱት በፖሊስ ላይ ድንጋይ በመወርወርና የፖሊስ ኃይሎችን ለመግደል ሞክረዋል በሚል ነው፡፡ በላሆር የሚገኙ ነዋሪዎች የጋዝና የኤሌክትሪክ ክፍያ ባለመፈጸማቸው ውዝፍ ዕዳ ስለተጠራቀመባቸው የጋዝና የኤሌክትሪክ መስመሮቹን ለመቁረጥ የፖሊስ ኃይል ወደሥፍራው የዛሬ ሁለት ወር አካባቢ ተንቀሳቅሶ ነበር፡፡ በሁኔታው የተናደዱ የአካባቢው ነዋሪዎች በፖሊስ ቡድኑ ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ከማድረስ አልፎ የተወሰኑት ላይ ጉዳት አድርሰው ነበር፡፡

babyክስተቱን ለፍርድቤት በማቅረብ ክስ የመሰረተው የፖሊስ ኃይል በወቅቱ በጥቃቱ ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን 25 ግለሰቦችን ሲከስ ህጻኑን እና ቤተሰቦቹ አብሮ ለክስ አቅርቧል፡፡

ህጻኑም በአያቱ ታቅፎ ፍርድቤት በቀረበበት ወቅት በፍርድቤቱ መዝገብ ላይ በጣቱ ፈርሟል፡፡ ክሱን የተቃወመው የቤተሰቡ ጠበቃ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደተናገረው ፍርድቤቱ በተለይ በህጻኑ ላይ የተመሰረተውን ክስ ወዲያውኑ ውድቅ ማድረግ ነበረበት ብሏል፡፡ ይህንን አለማድረጉ በራሱ የፖሊስ ኃይላችንና የፍትህ አካላቶች ምን ያል ብቃት እንደሌላቸው የሚያጋልጥ ነው በማለት ተቃውሞውን ገልጾዋል፡፡

አብሮ ለፍርድ የቀረበው የህጻኑ አባት ፖሊስ የሃሰት ክስ እንደመሠረተባቸው በመጥቀስ የልጁን መከሰስ አጥብቆ ተቃውሟል፡፡ “እኛ በወቅቱ አንከፍልም ብለን የተቃወምነው ኤሌክትሪክ በሰፈራች ሳይኖር ወርሃዊ ክፍያ ፈጽሙ በመባላችን” ነው በማለት የክሱን ኢፍትሃዊነት አስረድቷል፡፡

ህጻኑ ከሌሎቹ ተከሳሾች ጋር በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ፍርድቤት እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ ዜናው ይፋ ከሆነ በኋላ በተለይ ህጻኑ ላይ ክስ እንዲመሠረት ያደረገው የፖሊስ አባል ከሥራው እንዲገለል ተደርጓል፡፡

ባለፈው ዓመት በተሻሻለው የፓኪስታን ሕግ መሠረት በወንጀል የሚከሰሱ የመነሻ ዕድሜ ከ7 ዓመት ወደ 12ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ይህንን ሕግ በመጻረር ዳኛው በህጻኑ ላይ ክሱ እንዲመሠረት መፍቀዳቸው የበርካታ ሚዲያዎች መወያያ ርዕስ ሆኗል፡፡

(ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ዜናውን ከተለያዩ ዓለምአቀፍ ምንጮች እንደዘገበው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. jarso says

    April 16, 2014 03:16 am at 3:16 am

    What is the big deal here ? we have witnessed in our very eyes while the woyane butchers killing thousands of children in Ethiopia and several of them thrown in jungle to be eaten by hungry hyenas .

    Reply

Leave a Reply to jarso Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule