• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መዝገብ የማያውቃቸው 8.4 ሚሊዮን ህጻናት

August 10, 2020 06:18 pm by Editor Leave a Comment

ባለፉት 5 ዓመታት ከተወለዱ 10 ሚሊዮን ህጻናት ውስጥ 84 በመቶዎቹ ያልተመዘገቡ ናቸው ተባለ።

የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ባለፉት 5 ዓመታት የመዘገበው የውልደት ኩነት 16 በመቶ ብቻ መሆኑንና ይህም 84 በመቶ የሚሆኑት ተወላጆች በመንግስት ሰንድ ላይ ያልተመዘገቡ እና የማይታወቁ ናቸው ብሏል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙጀብ ጀማል ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ከአውሮፓውያኑ 2012 ጀምሮ  10 ሚሊየን ህፃናት ይወለዳሉ የሚል ግምት የነበረ ቢሆንም በወሳኝ ኩነት የተመዘገቡት ግን 2 ሚሊየን ያህሉ ብቻ ናቸው።

በዚህ መሀል ያልተመዘገቡትን 8 ሚሊየን ህፃናት ስለመወለዳቸው እና ስለመኖራቸው መንግስት እንደማያውቅ ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት።

በህገ መንግስቱ መሠረት ህፃናት እንደተወለዱ በ90 ቀናት ውስጥ መመዝገብ፣ ስም ማግኘት እና መታወቂያ አግኝተው ዜግነታቸው መታወቅ አለበት።

ይህ የውልደት ምዝገባ አልተከናወነም ማለት ደግሞ የህፃናቱን መብት አለማክበር ሲሆን ቤተሰብ ይህን የማድረግ ግዴታ አለበት ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ።

አሁን ላይ ባለው የአመዘጋገብ ስርዓት ህፃናት 5 ዓመት ሞልቷቸው ትምህርት ቤት በሚገቡ ወቅት በዘገየ የምዝገባ ሂደት የሚከናወንላቸው ቢሆንም 5 ዓመት እስኪሞላቸው ግን በመንግሥት አይታወቁም።

ህፃናት 5 ዓመት እስኪሞላቸው በመንግስት አይታወቁም ማለት ስለ ትምህርታቸው፣ ስለ ጤናቸው ሁኔታና በሌሎች ጉዳዮው ላይ መንግስት የሚያወጣው ፖሊስ በመላምት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ያደርገዋል ብለዋል።

በመሆኑም ወላጆች ይህን ሀላፊነት ወስደው በ90 ቀናት ውስጥ ህጻናትን ማስመዝገብ እንደሚኖርባቸው ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

የዓለም ባንክ በአንድ ወቅት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያላክተው በአፍሪካ ከ500 ሚሊየን በላይ ሰዎች በመንግሥት ሪከርድ ላይ አልተመዘገቡም።

በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ ከ18 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት በመንግስት ዶክመንት ላይ አልተመዘገቡም ወይም አይታወቁም ተብሏል።(ትግስት ዘላለም፤ ኢትዮ ኤፍ ኤም)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Social

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule