የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ውስጥ የጥበቃ ሰራተኛ ናቸው፡፡ የሚኖሩት ከ10 አመት ልቻቸው ጋር ነው፡፡ ይህን ልጅ እሳቸው ብቻ ነው የሚያሳድጉት፡፡ ትናንት ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከታፈሱ ከሰዓታት በኋላ ስራ ውለው ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በደህንነቶች ታፈኑ፡፡ አቶ ቀኖ የጥበቃ ስራ ከመስራት ውጭ ሰልፉ አስተባባሪም ተሳታፊም አልነበሩም፡፡ ግን ታጥሮ ከሰነበተው የሰማያዊ ቢሮ የወጣ ሁሉ ሲለቀም ነበርና እሳቸውንም አፈኗቸው፡፡ ምን አልባትም ተደብድበው ይሆናል፡፡ ይህ ስርዓት እነ ይልቃልን፣ ብርሃኑን፣ አቤልን፣ በላይን፣ ጣይቱዎቹን . . . ሰማያዊን ብቻ አይደለም የሚፈራው፣ የሚያፍነው፣ የሚያፍሰው፣ የሚደበድበው፡፡ አቶ ቀኖንም የሆነ ነገር ያደርጋሉ ወይንም አድርገዋል በሚል (በራሱ ትርጉም) አፍኖ አስሯቸዋል፡፡ አሁን አቶ ቀኖ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ ይገኛሉ፡፡ … [Read more...] about “አሸባሪው” የ72 ዓመት አዛውንት
Archives for December 2014
ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት?
ወደ አውሮፓ የሚያስገባውን ቪዛ እና ትኬት ይዞ ከወዳጆቹ ጋር ጉዞውን ለመጀመር ወደ ቦሌ አለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ አቀና። እዚያው እንደደረሰ የተለመደው የፓስፖርትና ትኬት ቁጥጥር ተደረገ። ሁሉም የተሟላ ነበር። ቴዲ ሸኚዎቹን ተሰናብቶ ወደ ውስጥ ጋባ። እለተ ሐሙስ፣ ህዳር 28 ቀን 2007 ዓ.ም.። የአውሮፓው ኮንሰርት በፊንላንድ፣ ሄልሲንኪ ቅዳሜ፤ ህዳር 28 ቀን ይጀምራል። ፊንላንድና አካባቢው ያሉ የቴዲ አድናቂዎች ትኬት ቆርጠው አርቲስቱን በጉጉት እየተጠባበቁት ነው። የቴዲ አፍሮ ማናጀርም አቡጊዳ ባንድን ይዞ ሄልሲንኪ ላይ ለቅዳሜው ስራ በልምምድ ላይ ይገኛል። ቴዲን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተሰናብተው የተመለሱ ወዳጆቹ አውሮፓ ደውለው አርቲስቱን ሄልሲንኪ ላይ እንዲቀበሉት ተናግረው ነበር። ነገሩ እነሱ እንዳሰቡት ግን አልነበረም። ዘግየት ብሎ ሌላ ነገር መጣ። ሰዎቹ ቦሌ ላይ … [Read more...] about ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት?
Ethiopia: Making Reconciliation Work
The reconciliation dialogue needs to progress in parallel on two fronts: (1) among the several opposition groups; and, (2) between the government and oppositions. Allow me to be pragmatic by putting myself in the shoes of both the government and the opposition to deal with the reconciliation dialogue on the latter front. Since there is so much mistrust between the government and oppositions, tossing the word “reconciliation” around will not get us anywhere. It means different things for … [Read more...] about Ethiopia: Making Reconciliation Work
ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ
በዘመነ መሳፍንት ወቅት፤ ለስሙ በዙፋኑ ላይ የዘር ግንድ ያለውን ሰው አስቀምጠው፤ ራሳቸውን እንደራሴ በመሾም፤ ጉልበተኞች ያደረጉት ሁሉ ግልጽ ነው። የውጭ ሀገር መንግሥታት ደግሞ በወኪሎቻቸው አማካኝነት ፀረ-ኢትዮጵያ ሚና ተጫወቱ። በደንብ በዝርዝር የሚያስረዳ መዝገብ ግን አላገኘሁም። ከዚህም ከዚያም ለቃቅሜ የተገነዘብኩትን ይዣለሁ። የእስክንድርያውን የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በመጠቀም፤ ግብፅና ቱርክ በአንድ በኩል፣ በፖርቹጋሎች የተጀመረውን ግንኙነት በመጠቀም፤ የካቶሊክ ቤተክርስትያን በሌላ በኩል፣ በእንግሊዝና በፈረንሳይ በኩል ደግሞ የፕሮቴስታንትና የአድቬንቲስት ተቋሞች በማዕከላዊው የሀገራችን ክፍል ያላደረጉት ተንኮል የለም። የሁሉም ጥርቅም ጥረት፤ ክርስትናን ወይንም እስልምናን ተከትለው፤ የፈጣሪያቸውን ሥራ ለማስተማር ሳይሆን፤ ጠንካራ ኢትዮጵያ እንዳትኖር ለማድረግ ነበር። አባይን … [Read more...] about ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ
ግልጽ ደብዳቤ ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
የዱሮ ወዳጄ ሰላምታዬ ይድረሽ። እንደምታውቂው ከተያየን ከሁለት አስርት አመታት በላይ ሆኗል። እኔም ካገሬ ከወጣሁ 21 ዓመት አለፈኝ። በጤናና በምቾት እንደምትኖሪ እሰማለሁ። እግዚአብሄርም መንግስትም ጥሩውን ነገር ሁሉ አብዝቶ እንዲሰጥሽ ምኞቴ ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጓደኝነት ከምቀርባቸውና ከማከብራቸው ስዎች ውስጥ አንቺ አንዷ እንደነበርሽ ራስሽም ብዙ ሰዎችም ያውቃሉ። ከጊዜ ብዛትና በስልጣንም ርቀት ምክንያት ጓደኝነቴን ብትረሽውም አልፈርድብሽም። እኔ ግን ከሀገሬ ባለስልጣኖች አንዷ በመሆንሽ አልፎ አልፎም ቢሆን ስላንቺ የሚባለውን ከፉም ደግም እሰማለሁ። ብዙ ጊዜ ሰዎች ስላንቺ ክፉ ሲናግሩ ስሰማ የጓደኝነት ነገር እየሆነብኝ ደስ አይለኝም። ተሳክቶልኝ እንደሆን ባላውቅም ስላንቺ የማውቃቸውን በጎ ነገሮች በማንሳትም ልሟገት የሞከርኩበት ጊዜ ጥቂት አይደለም። ብዙ ሰዎች ያኔ 41 … [Read more...] about ግልጽ ደብዳቤ ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
በአዳር ሰልፉ ኢህአዴግ “ተሸብሯል”
* የከምባታ ጠንባሮ ዞን ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ተገለጸ * የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በፖሊስ ተከብቦ አደረ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በፖሊስ ተከብቦ ማደሩንና አባላት ከውጭ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ለአዳር ሰልፉ ቅስቀሳ ዝግጅት ቢሮ ያደሩ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አመራሮችና አባላቱ እራት በልተው ወደ ፓርቲው ጽ/ቤት ሲመለሱ ቢሮው በፖሊስ ተከብቦ እንዳገኙትና ወደ ውስጥ እንዳይገቡ እንደተከለከሉ በቦታው የነበሩት የፓርቲው አመራሮችና አባላት ገልጸዋል፡፡ አመራሮችና አባላቱ ፖሊስ ከ200 ሜትር ርቀት ውጭ ወደ ፖለቲካ ፓርቲ ጽ/ቤት መጠጋት እንደማይችል ቢከራከሩም ፖሊሶቹ “መመሪያ ተሰጥቶናል፤ አንሄድም!” ማለታቸው ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ከፖሊስ ጋር ሲከራከሩ የአካባቢው ህዝብ በመውጣቱ ፖሊሶቹ ፓርቲው ጽ/ቤት እንደራቁ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል … [Read more...] about በአዳር ሰልፉ ኢህአዴግ “ተሸብሯል”
የጣሊያን ፖሊስ ሰዉ አስተላላፊዎችን ያዘ
የጣሊያን ፖሊስ በሕገ-ወጥ መንግድ ወደ አዉሮጳ ያሸጋግራሉ በማለት የተጠረጠሩ 10 የኤርትራ ተወላጆችን በቁጥጥር ሥር አዋለ። የካታኒያ-ሲሲሊ ፖሊስ እንዳስታወቀዉ ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ስደተኞችን ወደ አዉሮጳ የሚያሸጋግር ሕብረ-ሐገራት መረብ መኖሩን የሚጠቁም መረጃ ከደረሰዉ በኋላ ባደረገዉ አሰሳ ነዉ። በፖሊስ መግለጫ መሠረት ስደተኞቹን የሚያሻግረዉ መረብ ኤርትራ፤ ሊቢያ፤ ሌሎች ሰሜን አፍሪቃ ሐገራት እና ኢጣሊያ ድረስ የተዘረጋ ነዉ። ለአሸገጋሪዎቹ ገንዘብ እየከፈሉ ወደ አዉሮጳ ለመግባት ሲሞክሩ በርካታ ስደተኞች ሜድትራንያን ባሕር ዉስጥ እየሰመጡ ሞተዋል። ፖሊስ ሰሞኑን የያዛቸዉን ተጠርጣሪ አሸጋጋሪዎች ካለፈዉ ግንቦት እስከ መስከረም ድረስ 23 የባሕር ላይ ጉዞዎችን አቀነባብረዋል በማለት ከሷቸዋል። ከተጓዦቹ ቢያንስ 240 ስደተኞች ሞተዋል። ከአስሩ ተጠርጣሪዎች ዘጠኙ ኅዳር 16 … [Read more...] about የጣሊያን ፖሊስ ሰዉ አስተላላፊዎችን ያዘ
ለለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
መልዕክቱን አባዝቶ ለሌሎች በማዳረስ ለ24 ሰዓቱ ሰልፍ ቅስቀሳ የበኩላችሁን እገዛ እንድታደርጉ ጥሪ እናስተላልፋለን! ያለመስዋዕትነት ድል የለም! … [Read more...] about ለለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
ዘመን ሞቷል – ኃይሉ አትበሉ
ማስታወሻው ጠፍቶ ምስሉ ተገርስሶ ወድቆ አካሉ ተሰርዞ ቃለ ውሉ ዘመን ሞቷል ኃይሉ አትበሉ። ታሪክ የለም አምልጦናል ዘመን ቆመን ሞቶብናል ሁሉም አልቆ ተጠቃሏል ጋሼ ኃይሉ ይዞት ሄዷል ለዘመን ነው እንባ ማፍሰስ ለታሪክ ነው ከል መልበስ ለጊዜ ነው ፊት መከስከስ ለጋሽ ኃይሉ ይብቃን ማልቀስ የዘመንን በሞት ማምለጥ የጊዜውን መገላበጥ ገና በፊት ጋሼ ኃይሉ ተናግሮታል በአፉ ሙሉ መጣ ብለን ሚሊኒየም በክብሩ ላይ ልንታደም ወዲያ ወዲህ ስንሯሯጥ ምድር ስንቀድ ሰማይ ስንፈልጥ ከረምንና አገር ወጥቶ ተበልቶና ተጠጥቶ ጋሼ ኃይሉ ብቻ ቀርቶ ምነው ጠፋህ? በዚህ በዓል አንተ ብቻ ብሎ ሲባል ያልኖርኩትን አላከብርም ይሄ በዓል የኔ አይደለም መች ኖሬ ነው የማከብረው የኔ ዘመን ሞቷል ተወው ብሎ ነበር መልስ የሰጠው ጋሼ ኃይሉ እንዲህ … [Read more...] about ዘመን ሞቷል – ኃይሉ አትበሉ
በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ
በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ከትላንት በስቲያ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡ ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡ በጠበቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ … [Read more...] about በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ