• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ

December 7, 2014 02:31 am by Editor Leave a Comment

በዘመነ መሳፍንት ወቅት፤ ለስሙ በዙፋኑ ላይ የዘር ግንድ ያለውን ሰው አስቀምጠው፤ ራሳቸውን እንደራሴ በመሾም፤ ጉልበተኞች ያደረጉት ሁሉ ግልጽ ነው። የውጭ ሀገር መንግሥታት ደግሞ በወኪሎቻቸው አማካኝነት ፀረ-ኢትዮጵያ ሚና ተጫወቱ። በደንብ በዝርዝር የሚያስረዳ መዝገብ ግን አላገኘሁም። ከዚህም ከዚያም ለቃቅሜ የተገነዘብኩትን ይዣለሁ። የእስክንድርያውን የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በመጠቀም፤ ግብፅና ቱርክ በአንድ በኩል፣ በፖርቹጋሎች የተጀመረውን ግንኙነት በመጠቀም፤ የካቶሊክ ቤተክርስትያን በሌላ በኩል፣ በእንግሊዝና በፈረንሳይ በኩል ደግሞ የፕሮቴስታንትና የአድቬንቲስት ተቋሞች በማዕከላዊው የሀገራችን ክፍል ያላደረጉት ተንኮል የለም። የሁሉም ጥርቅም ጥረት፤ ክርስትናን ወይንም እስልምናን ተከትለው፤ የፈጣሪያቸውን ሥራ ለማስተማር ሳይሆን፤ ጠንካራ ኢትዮጵያ እንዳትኖር ለማድረግ ነበር። አባይን እንዳትገድብ፣ ለቅኝ ግዛት ተቀናቃኝ እንዳትሆን፣ የጥቁር መንግሥት ሆና ለባሪያ ንግዳቸው እምቢተኝነት መመኪይ እንዳትሆን ነበር። ማዕከላዊ ጥንካሬው እየበረታ የሄደው የኢትዮጵያ መንግሥት፤ በክልሉ ያሉትን ዜጎች እያስተዳደረና ኢትዮጵያዊነትን እያጎለበት በሄደ ጊዜ፤ ለረጅም ዘመን በኢትዮጵያዊ መንግሥታት ሥር የነበሩ ክልሎችን አምጡ ማለቱና፤ የአውሮፓዊያንን የቅኝ ግዛት በአካባቢው ለማስፋፋት መሯሯጥ የሚገታ መሆኑ ሁሉንም አስጋ። እናም ይህ የውጪ ያላባራ ተንኮል፤ ሀገራችን ባሉት ባላባቶች ውስጥ፤ ያላቋረጠ የመጠፋፋት መናኮርን አፋፋመ። አንድና ሁለት ጠመንጃዎች ካስርና ሃያ ጥይቶች ጋር በመጸሐፍ ቅዱስ በመጠቅለልና በማቀበል ቆስቋሾቹ እያራገቡት፤ ግለቱ እየጨመረ፤ አንድ ጳጳስ በመላክ ውስጡን እያመሱ፤ ትርምሱ እያደገ፤ በሀገራችን ውስጥ የጎጥ ገዥዎች አየሉ። በዚያ ጊዜ የተተከለው መርዝ አሁንም እያመረቀዘ፤ ጥዝጠዛውና ግማቱ እኛን አፍኖናል። እንዴት? ይህን ነው የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛ። አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

ከፍጻሜ መንግሥት አንስቶ አፄ ቴዎድሮስ እስከተነሱበት ድረስ፤ ዘመነ መሳፍንት እየተባለ የሚጠራው የታሪካችን ወቅት፤ ምን ያህል የሀገራችን ዕድገት ወደ ኋላ እንዲጎተት እንዳደረገው በሰፊው የተመዘገበ ነው። ይህ ዘመን፤ ለረጅም ጊዜ፤ እየተዋጉም ሆነ አባት ለልጁ እያወረሰ፤ ተከታታይነት የነበረውን የማዕከላዊ መንግሥት ሕልውና ከጥያቄ ውስጥ አስገባው። እኔስ ከማን አንሳለሁ በማለት፤ ወገኖቹንና ነፍጥ በማሰባሰብ፤ ያካባቢው ገዥ እኔ ነኝነት ነገሠ። በዳር ዳር በሚባሉ አካባቢዎች የሚገኙት ዜጎች ከማዕከላዊው መንግሥት የነበራቸው ግንኙነት ላላ። ትግራይ፣ ወሎ፣ ወልቃይት፣ ላስታ፣ የጁ፣ ስሜን፣ ሸዋ፣ ጎጃም፣ ቋራ፣ ከፋ፣ ሐረር፣ ኦጋዴን፣ ሞያሌ፣ የሚባሉት ክፍሎች፤ የየራሳቸው ጉልበተኞች እንደራሴዎች ሆኑባቸው። ሲደክሙ ለጉልበተኛው እየገበሩ፣ ሲጎለብቱ ራሳቸው እያስገበሩ፤ መንግሥታዊ ተግባር የሚባለውን ረስተው፤ ነፍጥ መሰብሰብንና ለሚቀጥለው ውጊያ መዘጋጀትን፤ የሕልውናቸው አውታር አደረጉት። ትብብር ማለት፤ እኔን ነገ እስከጠቀመኝና እሱን ወግቼ እስካቸነፍኩት ድረስ በሚለው ስልት ተለወጠ። እንግዲህ ይህ የውስጡ ሀገራዊ አስተዳደሩ ነበር። መቼም ይህ ለሁላችን ግልጽ ነው። ታሪክ መመርመር ሳይሆን ያለንበትን መመርመሩ በቂ ማስረጃ ነው። የውጪ ጣልቃ ገቦች ለዚህ ሂደት ምን ያህል ተጠያቂነት አላቸው? አሁን ላለንበትስ? እንግዲህ እዚህ ላይ ነው የዘመነ መሳፍንት ቅርሳችን እና የፖለቲካ መሪዎቻችን ተወራራሽነት በግልጽ የሚታየው። አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

አፄ ቴዎድሮስ ለዘመነ መሳፍንት ፍጻሜ ከሠጡት ይሄው ከአንድ መቶ ሃምሳ ዓመት በላይ ሆኖታል። ዘመኑን እንጂ አብሮን ያለውን አመለካከቱን ማለቴ አይደለም። በአእምሯችን ያንን የታሪካችንን ወቅት ብናስወግደውና ተከታታይነቱን የጠበቀ የኢትዮጵያ መንግሥት ቢኖር ኖሮ የሚለውን አስተባቅተን፤ አሁን ሀገራችን ልትደርስበት የምትችልበትን ብናጤን፤ አሁን ካለንበት ምን ያህል ይለይ ነበር? መቼም የታሪክ ሂደት በሰዎች እቅድና ፍላጎት እንደማይመራ ዕውቅ ነው። ታልሞና ተቀምሮ የሚነደፍና የሚገፋ እንዳልሆነ ስቼ አይደለም። ነገር ግን ትልሙን በመዘርጋት ዕይታ ለመፍጠር ስል ነው። የተደናቀፈው ሁሉ ቢስተካከል፤ የት ልንደርስ እንችል እንደነበር መገመቱ ቀላል ነው። በአኳያው ደግሞ፤ ከዚያ ትምህርት ወስደን፤ የያኔውን ወቅት ስህተት አለመሥራቱ፤ የኛ ታሪካዊ ግዴታ ነው። እንደያኔዎቹ አሁንም ያንኑ ሆኖ መገኘት፤ ጅልነት ነው። ጅልነቱም በቀላሉ ሲመነዘር ነው። ከዚያ ለከፋ ስድብ ራስን ማሰለፉ አልጥም ስላለኝ ነው። እንደያኔዎቹ የየራሳችን ቦታ ባንይዝም፤ በትካቸው ድርጅቶች አሉን። እናም የየድርጅቶቻችን ንጉሥች አሉን። ዙፋኑንም ለማንም ላለማውረስ፤ ለሚነሳው ተቀናቃኝ የስድብ ውርጅብን በመቆለል ትንንሽ ሌሎች ድርጅቶች እየተፈጠሩ፤ ተደላድለው በመቀመጥ ዓመታትን ያስቆጠሩ ስንት ንጉሦች አሉን? እንግዲህ ቦታውና በዙፋኑ የተቀመጠው ንጉሥ፤ በድርጅት ተተክቷል። እንደራሴዎች የሆኑት ያሁኖቹ የድርጅቶቻችን መሪዎች ናቸው። ሀገር ማለት፣ ወገን ማለት፣ ታሪክ ማለት፣ ድርጅት ሆኗል። በቃ አለቀ በቃ! የኔ ድርጅት ያቸንፍ! አለያ ገደል ግቡ ተብለናል። ተሳስቼ ይሆን? አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

የያኔዎቹ ባላጋራቸውን እያብጠለጠሉ ለውጭ መንግሥታት አቤቱታ በማቅረብ ይለምኑ ነበር። አሁን ደግሞ ሌላውን ታግይ ድርጅት መኮነን፣ ሰላማዊ ሰልፍ በውጭ ሀገሮች ማድረግና መታገያ እንዲሆነን የበጎረቤት ሀገር መጠጋቱን ሙያችን ብለነዋል። ድንቄም! አለች ጎረቤቴ! አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

(አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ)
እሁድ ታህሣሥ ፳ ፱ ቀን ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህረት (12/7/2014)

ተጨማሪ ጽሁፎችን በአቶ አንዱ ዓለም ተፈራ ብሎግ ላይ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule