ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ዛሬ ምሽት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ተነስቶ ወደ ኦስሎ ኖርዌይ ጉዞውን ጀምሯል። ኢትዮጵያዊው የፖፕ እና ሬጌ ሚዚቃ አቀንቃኝ በአውሮፓ ከተሞች የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማድረግ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው በወሩ መጀመርያ ላይ ነበር። ባለፈው ሃሙስ ዲሴምበር 4፣ 2014 ቦሌ አለም ዓቀፍ አውሮፕላን ጣብያ እንደደረሰ የደህንነት አካላት እንዳገቱት እና ፓስፖርቱንም እንደቀሙበት በልዩ ልዩ የዜና ምንጮች መዘገቡ ይታወሳል። አርቲስቱ ለምን ወደ ውጭ እንዳይወጣ እንደታገደና ፓስፖርቱም ለምን እንደተቀማ እስካሁን በይፋ የተነገረ ነገር የለም። አንዳንድ የዜና ምንጮች ጉዳዩን ቀረጥ ካለመክፈል ክስ ጋር አያይዘው አቅርበውታል። ይህ መላ ምት ፍጹም ስህተት ነው። ምክንያቱም ድምጻዊው በጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ … [Read more...] about ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ቴዲ አፍሮ ወደ አውሮፓ በረረ
Archives for December 2014
ድንቄም ጠቅላይ ሚኒስትር!
ብዙ ተብሏል። እኔም አንድ ነገር ልጨምርና ልገላገለው። “የጊዮርጊስን መገበሪያ የበላ ሲለፈልፍ ይኖራል” ነው የሚባለው? ተናግሮ ከሚያናግር ይሰውራችሁ! ውሀን ምን ነበር የሚያናግረው? ድንጋይ! የሰውም ድንጋይ እራስ አለ! ይቅርታ አንጀቴ አርሮ ነው! ሦስት መንግስታትን የማየት ዕድል አጋጥሞኛል። ተወልጄ፣ አድጌ፣ ተምሬ ለዩኒበርሲቲ የበቃኹት በንጉሠ ነገሥቱ ዘመነ መንግሥት ነበር። ዕውነቱን እንናገር ከተባለ፣ ንጉሡ ሲናገሩም ሆነ ሲራመዱ፣ የርዕሰ ብሔርነት ግርማ ሞገስ ነበራቸው። “በንጉሥ መገዛቱ ጊዜ ያለፈበት፣ ያረጀ ያፈጀ፣ ገበሬውን በገባርነት ጠፍንጎ የያዘ፣ አገሪቱ በዕድገት ወደፊት እንዳትራመድ ያገዳት፣ ኋላ ቀር የፊውዳል ሥርዓት ነውና ወደሶሻሊዝም እንለውጣት” የሚሉ ድምጾች ከተማረው ክፍል አካባቢ እያየሉ መጡና እኛንም እንደጎርፍ ይዘውን ነጎዱ። ተከተልናቸው። “መሬት ለአራሹ … [Read more...] about ድንቄም ጠቅላይ ሚኒስትር!
የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽኦ
በቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ በአቶ ኦባንግ ሜቶ በተጠራው ስብስባ ላይ የመገኘት እድል አጋጥሞኝ ነበር:: በስብሰባው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎችና ከአሜሪካ ግዛቶች የተሰባሰቡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል:: የስብሰባው መሪ ሀሳብ “ስለ እያንዳንዳችን ከመናገር እያንዳንዳችን እንነጋገር” የሚል ድፍረትን፣ ግልፅነትን፣ መከባበርን፣ መነጋገር መቻልን ሃላፊነት በተሞላበት ስሜት ይቀርቡ በነበሩት አስተያየቶች የሚያረጋግጡ ከመሆናቸውም በላይ የተለየዩ የፖለቲካ አመለካከት፣ እምነት እንዲሁም የተለየዩ ብሄረሰቦች ዉሁድ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምጠው ያነሱዋቸው የነበሩት ሃሳቦች በጥንታዊት ኢትዮጵያና በአዲሲቱ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ ግራ ለተጋቡ ጥሩ አስተማሪ መድረክ ነበር:: ኢትዮጵያ የምትባል ጥንታዊት ሃገርን የሲኦል መገለጫ አድርገው ለሚስሉዋት የህወሃት … [Read more...] about የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽኦ
ግፍና አፈና ዐመጽን ይወልዳሉ!
የዐመጸኛ አፍ ጥልቅ ጉድጓድ ነው (መ. ምሳሌ ም. 22፣ ቁ. 14) ሰብአዊ መበቶችን በመጣስ፣ ግፍ በመፈጸምና አፈናን በማጠናከር እደሜ የሚሸምት የአገዛዝ ሥርዓት የእያንዳንዱን ሰው መንፈሳዊና አካላዉ ጥንካሬ የማዳከም፣ ቅስምን የመስበርና ፍርሃትን የማንገስ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ሁሉ በብሶት የሚወለዱ፣ እምቢኝ ለግፈኞች፣ እምቢኝ ለአንባገነኖች፣ እምቢኝ ለነጻነቴ የሚሉ መንፈሰ ጠንካራ ጀግኖችንና ታጋዮችንም ይወልዳል:: የአለማችን ስመ ጥርና ዘመን የማይረሳቸው የነጻነት ታጋዮች እነ ማህተመ ጋንዲ፣ ማርቲን ሉተር ኪነግ፣ ማንዴላ፣ ኡንግ ሳን ሱ ኪ እና ሌሎችም ብዙዎች የፈለቁት በብሶት ከተሞላ፣ ጭቆና ካንገሸገሸውና በአፋኝ ሥርዓት ከታመቀ ማኅበረሰቡ ጉያ ነው:: አንድን ማኅበረሰብ በአፈሙዝ፣ በሕግና በገንዘብ ኃይል ጭፍሎቆና አፍኖ ማቆየት የሚቻለውም ለተወሰነ ጊዜ ብቻ መሆኑን … [Read more...] about ግፍና አፈና ዐመጽን ይወልዳሉ!
The Role of Civil Society Organization (CSOs) in the Upcoming Elections in Ethiopia
Fourth International Conference of Ethiopian Women in the Diaspora March 7, 2015 Washington DC, USA The Role of Civil Society Organization (CSOs) in the Upcoming Elections in Ethiopia Call for papers Civil society organizations (CSOs) flourished in Ethiopia from early 1990s to 2005 better than ever before. Some of these civil society organizations focused on service delivery, others on civil rights, gender equality and good governance, and still others on consciousness raising and … [Read more...] about The Role of Civil Society Organization (CSOs) in the Upcoming Elections in Ethiopia
ሱስ ትውልድና ሀገር!
በእኅታችን በሐና ላላንጎ ላይ ያ አደጋ በደረሰ ጊዜ ይሄንን ከባድ ዜና በለጠፉ ዋና ዋና ድረ ገጾች ላይ አንድ አስተያየት ሰጥቸ ነበር “ሆን ተብሎ በሱስ ትብትብ እንዲተበተብ ከተደረገ የዚህ አገዛዝ ትውልድ ከዚህ የተለየ ምን ይጠበቃል? እንደ ማኅበረሰብ ወንድም እኅቶቻችንን እናም ልጆቻችንን ከዚህ የሱስ ማጥ ውስጥ ካልታደግን በስተቀር ገና ከዚህ የከፋ ብዙ ነገርም ያሰማናል ያሳየናል” የሚል፡፡ አንዳንዶቹ የአገዛዙ ደጋፊዎች አጋጣሚውን ሆን ብየ ለፖለቲካ ፍጆታ ለመጠቀም የፈለኩ መስሏቸው አስተያየቴ ትክክል እንዳልሆነ ሲናገሩ አንዳንዶችም በመሳደብ ከአስተያየቴ ስር ምላሽ ሰጥተው ነበር፡፡ እኔ ግን ስም ለማጥፋትም አጋጣሚውን ለመጠቀምም አልነበረም፡፡ ያልኩት ነገር ለመሆኑ መረጃው ስለነበረኝ እንጅ፡፡ ወያኔ ፍጹም በደነቆረ አመክንዮና በጠላትነት ሰብእና ትውልዱን ሆን ብሎ በሱስ ማጥ … [Read more...] about ሱስ ትውልድና ሀገር!
የኢትዮጵያን ዲሞክራሲ ለመዉለድ ስንት ዘመን ይፈጃል?
የምርጫ ወግ ምርጫ ደርሷል አይደል? ለዛ መሆን አለበት በአንድ በኩል ኤብጭ ‘ምርጫ ቦርድ ለምርጫ አስፈፃሚዎች ስልጠና ሰጠ … ኮሮጆ አሰራጨ’… ሌሎች መገናኛ ብዙሃን ደግሞ ‘ምናምን የሚባል ፓርቲ ሰልፍ ጠራ’ … ‘የነእከሌ ፓርቲ ትየንተ ህዝብ በፖሊስ ሃይል በሃል ተበተነ’ ….. ዱዱዱዳ…እንዲያም እንዲህም የሚሉ ወሬዎች መስማት ከመሰንበቻዉ የተለመደ ሆኗል፡፡ (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የኢትዮጵያን ዲሞክራሲ ለመዉለድ ስንት ዘመን ይፈጃል?
አስገራሚው ትዕይንት “በተስፋዋ” የአረብ ምድር በሳውዲ!
* የሳውዲ መንግስት "ህገ ወጦችን" የማጽዳቱ ዘመቻ ቀጥሏል * ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎች ከሞት ጋር ተፋጠው እየተሰደዱ ነው * የሳውዲ መንግስት ማስጠንቀቂያና እርምጃ . . . የሳውዲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውንና ህጉ በማይፈቅደው መንገድ የመኖሪያ ፈቃዳቸው ካለው ሙያ ውጭ የሚሰሩ የማናቸውንም ሀገር ዜጎች በመላ ሀገሪቱ ለማጽዳት የተደራጀ ዘመቻ ከተጀመረ ወር ደፍኗል። በየቀኑ በመንግስትና በግል መገናኛ ብዙሃን የሚለቀቁት የማስጠንቀቂያ መረጃዎች ከበድ ከበድ ያሉ ናቸው። ዛሬ ማለዳ "ህገ ወጦችን ጠራርገን እናስወጣለን" ያሉትን የሰራተኛ ሚኒስትር አድል ፈቂን ይዞ የወጣው አረብ ኒውስ ሚኒስትሩ ሃገራቸው ለህገ ወጥ ሰራተኞች ቦታ እንደሌላት በአጽንኦት መጠቆማቸውን ያስረዳል። የሰራተኛ ሚኒስትሩ በማከልም መንግስት ህገ ወጦችን እግር በእግር እየተከታተለ በመያዝ … [Read more...] about አስገራሚው ትዕይንት “በተስፋዋ” የአረብ ምድር በሳውዲ!
STARTING THE CONVERSATION BETWEEN DIVERSE ETHIOPIANS IN MINNESOTA
SMNE FORUM SERIES II: MINNESOTA STARTING THE CONVERSATION BETWEEN DIVERSE ETHIOPIANS IN MINNESOTA CAN WE COLLECTIVELY OWN BOTH THE GOOD AND THE UGLY PARTS OF OUR PAST SO WE CAN BE FREE AT LAST FROM THE SHACKLES OF OPPRESSION? First of all, I would like to thanks Ato Girma Biru, all members and supporters of the SMNE in Minnesota for taking your time to organize this wonderful forum. Thank you for inviting me to speak to you on the topic of Starting the Conversation between Diverse … [Read more...] about STARTING THE CONVERSATION BETWEEN DIVERSE ETHIOPIANS IN MINNESOTA
መድረክ የሰላማዊ ሰልፉን አካሄደ
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እሁድ ዕለት ያቀደውን ሰላማዊ ሠልፍ በ37 መፈክሮች በማጀብ አካሂዶዋል፡፡ አብዛኛዎቹ መፈክሮች ምርጫን፣ ምርጫ ቦርድን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁኔታን፣ የአገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ የኑሮ ውድነት፣ የመሠረታዊ አገልግሎቶች መቆራረጥና መንግሥትን ከሃይማኖት ጣልቃ ገብነት እንዲወጣ የሚጠይቁ ነበር፡፡ ከመፈክሮቹ መካከልም "ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንጂ በአስመሳይ ፕሮፖጋንዳ፣ በኃይልና በተፅዕኖ አይገነባም"፣ "የአገራችን ችግሮች በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በሚገለጽ የሕዝብ ውሳኔ እንጂ በኃይል ዕርምጃ አይፈቱም"፣ "ከምርጫ በፊት የምርጫ ውድድር ሜዳው የሚስተካከልበት ውይይትና ድርድር ይካሄድ"፣ ወዘተ የሚሉ መፈክሮች ተካተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሕዝቡ በ1ለ5 መረብ አፈናና ቁጥጥር ከሚካሄድ የምርጫ ድምፅ አሰጣጥ … [Read more...] about መድረክ የሰላማዊ ሰልፉን አካሄደ