• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽኦ

December 19, 2014 05:41 pm by Editor Leave a Comment

በቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ በአቶ ኦባንግ ሜቶ በተጠራው ስብስባ ላይ የመገኘት እድል አጋጥሞኝ ነበር:: በስብሰባው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎችና ከአሜሪካ ግዛቶች የተሰባሰቡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል::

የስብሰባው መሪ ሀሳብ “ስለ እያንዳንዳችን ከመናገር እያንዳንዳችን እንነጋገር” የሚል ድፍረትን፣ ግልፅነትን፣ መከባበርን፣ መነጋገር መቻልን ሃላፊነት በተሞላበት ስሜት ይቀርቡ በነበሩት አስተያየቶች የሚያረጋግጡ ከመሆናቸውም በላይ የተለየዩ የፖለቲካ አመለካከት፣ እምነት እንዲሁም የተለየዩ ብሄረሰቦች ዉሁድ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምጠው ያነሱዋቸው የነበሩት ሃሳቦች በጥንታዊት ኢትዮጵያና በአዲሲቱ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ ግራ ለተጋቡ ጥሩ አስተማሪ መድረክ ነበር::

ኢትዮጵያ የምትባል ጥንታዊት ሃገርን የሲኦል መገለጫ አድርገው ለሚስሉዋት የህወሃት ኢሃዴግ ደጋፊዎችና ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸው የፖለቲካ ሰአሊዎች ወይም ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ያላቸውን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቁርኝት በፖለቲካ ብሩሽ ለማጥፋት የሚንደፋደፉ ያሉትን ያህል አዲሲቱን ኢትዮጵያን በጎሪጥና በሃሳባቸው የተለየ ቅርፅ ሰጥተው ለሚባንኑትም ሁለቱም አካሄዳቸው ሃገራችንን መጉዳቱን የስብሰባው ተሳታፊዎች አማካይ መንገድ እንዳለ በማሳየት ለዚህም ብቸኛ መንገዱ እውነትን መጋፈጥና መነጋገር ብቻ እንደሆነ ያሰመሩበት ጉዳይ ነው::

ስለ ዲሞክራሲ ማውራትና በዲሞክራሲ ህይወት ውስጥ መኖር ያለውን ልዩነት በተሳታፊዎቹ አቀራረብና በመድረኩ አመራር ያለው የዳበረ የፖለቲካ ግንነት አመላካች ነበር::

ይህ ወቅቱ የጠየቀውና አብዛኛው መድረክ ያጣና የታፈነ ኢትዮጵያዊ ድምፅ በመሆኑ ወንድማችን ኦባንግና ሶሊዳሪቲ ይህን መድረክ በመክፈታቸው ከፍተኛ ምስጋናና ድጋፍ ሊደረግላቸው ይገባል:: ከተለያዩ ክፍለ አለማትና ከአሜሪካ ስቴቶች በስፍራው ተገኝታችሁ አሁን በሀገራችን የሚታየውን ችግር ለመፍታት የሚያስችሉ የበሰሉ ሃሳቦችን ላቀረባችሁ ምሁራን የሃይማኖት አባቶችና እናቶች ታላቅ አክብሮትና ምስጋና ይድረሳችሁ::

ኢትዮጵያውያን ዝርዝር ሂደቱን ክፍል 1፣ ክፍል 2 እና ክፍል 3 ከዚህ ማግኘት ትችላላችሁ::

በተለይም በዲያስፖራው የሚታየው ጫፍና ጫፍ ቆሞ በስልጣን ላይ ካለው አምባገነን የህወሃት ኢሃዴግ መንግስት ባልተናነሰ ሁኔታ ባለፉት አመታት ኢትዮጵያውያንን እየከፋፈሉ ያሉት ጥቂት የፖለቲካ ሃይሎችና በስመ ደጋፊነት የተሰለፍን ወገኖች አካሄድ ትግሉን ወደ ሁዋላ ከማስኬድ በስተቀር ያስገኘው ፋይዳ እንደሌለውና አሁንም መፍትሄው ድፍረትና የመቻቻል ፖለቲካ ብቻ እንደሆነ ከምንም በፊት ለእውነት እራስን ም ማስገዛት ተቀዳሚ ተግባር ና የፖለቲካው ወሳነ ሃይል ህዝብን ማእከል ያደረገ ትግል ብቻ መ ሆኑን ከዚህ ስብሰባ መገንዘብ ይቻላል::

ዲያስፖራው የኢትዮጵያን ፖለቲካ በአብዛኛው የሚገመግምበት መድረኩ የፓልቶክ ክፍሎች በመሆናቸው በአካል ተገናኝቶ በመነጋገርና በኮምፒዩተር ጀርባ ሃሳብንም ሆነ ልዩነትን ማስተናገድ ያላቸውን ልዩነት በመገንዘብ ለአካላዊ ግንኙነት ትኩረት በመስጠት መሰባሰቡ ያለውን ፋይዳ መገንዘቡ የወቅቱ ጥያቄ ይመስለኛል::

በፓልቶኮች የሚደረጉ ውይይቶች በአብዛኛዎቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉና ዲሞክራሲያዊ ባህርያቸውም እያደገ የመጣና የትግላቸውም ማእከል በሃገር ቤት ያለው ትግል መሆኑ የሚያበረታታ ሲሆን የሶሊዳሪትና የአቶ ኦባንግ አካሄድ ለዲያስፖራው ፖለቲካ መጎልበት አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተስፋ አለኝ::

Gishag70@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule