• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ቴዲ አፍሮ ወደ አውሮፓ በረረ

December 20, 2014 02:13 am by Editor Leave a Comment

ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ዛሬ ምሽት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ተነስቶ ወደ ኦስሎ ኖርዌይ ጉዞውን ጀምሯል።

ኢትዮጵያዊው የፖፕ እና ሬጌ ሚዚቃ አቀንቃኝ በአውሮፓ ከተሞች የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማድረግ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው በወሩ መጀመርያ ላይ ነበር። ባለፈው ሃሙስ ዲሴምበር 4፣ 2014 ቦሌ አለም ዓቀፍ አውሮፕላን ጣብያ እንደደረሰ የደህንነት አካላት እንዳገቱት እና ፓስፖርቱንም እንደቀሙበት በልዩ ልዩ የዜና ምንጮች መዘገቡ ይታወሳል።

አርቲስቱ ለምን ወደ ውጭ እንዳይወጣ እንደታገደና ፓስፖርቱም ለምን እንደተቀማ እስካሁን በይፋ የተነገረ ነገር የለም። አንዳንድ የዜና ምንጮች ጉዳዩን ቀረጥ ካለመክፈል ክስ ጋር አያይዘው አቅርበውታል። ይህ መላ ምት ፍጹም ስህተት ነው። ምክንያቱም  ድምጻዊው በጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መርማሪ ቡድን ሙሉ ቀን ታስሮ ቢውልም ያለምንም ክስ ነበር የተለቀቀው።  ቴዲ አፍሮ በዚህ ጉዳይ ቢከሰስ እንኳን አገር ውስጥ ሲገባ  ታክስ ያልተከፈለበት መኪና መንዳት ፓስፖርት የሚያስነጥቅ ወንጀል አይደለም።  ቴዲ አፍሮ፣ የተጠቀሰውን ተሽከርካሪ የገዛው በሕጋዊ ደረሰኝ ቀረጥ ከፍሎ መሆኑን በወቅቱ ለፍርድ ቤቱ አስረድቶ ነበር የተለቀቀው።

በጉዞ እገዳው ሳብያ ሁለት የአውሮፓ ኮንሰርቶቹ ተሰርዘዋል። ቀድሞ አውሮፓ የገባው የቴዲ አፍሮ ማናጀር ዘካርያዝ ጌታቸው እና አቡጊዳ ባንድ ስራቸው እንዲተጓጎል ተደርጓል።  በአውሮፓ የቴዲ ኮንሰርት ፕሮሞተሮች ለአላስፈላጊ ወጪ ተዳርገዋል። የድምጻዊው አፍቃሪዎቹ ስሜት በእጅጉ ተጎድቷል።

ቴዲ አፍሮ ከጠበቆቹ እና ከስራ ባልደረቦቹ ጋር በመሆን ላለፉት አስራ አንድ ቀናት፤ ጉዳዩን ለማጣራት እና እልባት እንዲያገኝ ለማድረግ አቅሙ የሚፈቅደውን ሁሉ ሲጥር እንደነበርም ታውቋል።

ከሁለት ሳምንታት እንግልት በኋላ በትላንት ምሽት የገዛ ፖስፖርቱን አግኝቷል።

አርቲስቱ ከሃገር እንዳይወጣ መከልከል፣ ፓስፖርቱ መቀማትና እንዲጉላላ ማድረጉ በአብዛኛው ኢትዮያዊ ዘንድ ቁጣ ማስነሳቱን እና በገዥው ፓርቲ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ። በዚህ ከአንድ መንግስት በማይጠበቅ ድርጊት የተነሳ የገዢው ፓርቲ አባላት ሳይቀሩ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ተስተውለዋል።

ቴዲ አፍሮ በነገው እለት ማለትም ቅዳሜ – 20 ዲሴምበር 2014 ኦስሎ ላይ ዝግጅት አለው። ሌሊቱን ተጉዞ አድሮ ምሽቱን ይጫወታል። ባንዱም ኦስሎ ላይ በልዩ ዝግጅት ይጠብቃዋል። ከዚያም በሳምንቱ  ማለትም በ 27 ዲሴምበር 2014 በስዊድን ከተማ፤ በ 31 ዲሴምበር 2014  ፍራንክፈርት፤  በ 3 ጃንዋሪ 2015 በሎዛን-ስዊዘርላንድ የሙዚቃ ስራውን ያቀርባል።

ከዚያም በ ጃንዋሪ 10፤ 2015(ለኢትዮጵያ ገና) አምስተርዳም ላይ ልዩ ዝግጅቱን ይዞ ከአቡጊዳ ባንድ ጋር ይመለሳል። ከአምስተርዳም በኋላ ቀጣይ ስራዎቹ ፊንላንድ እና ዱባይ ናቸው።

በዘንድሮው የቴዲ አፍሮ አውሮፓ ኮንሰርቶች ከምንግዜውም የበለጠ  ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያውያን የሙዚቃ አፍቃሪዎች እንደሚገኙ ይገመታል።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule