ወ/ሮ ገነት ዘውዴ (ዮዲት ጉዲት) ይቅርታ መሳደቤ አይደለም ሰው የሚያውቃቸው በዚህ ስም በመሆኑና የሚኮሩበትም በመሆኑ እንጅ፡፡ እናም ወ/ሮ ገነት በቅርቡ በሸገር የኤፍ ኤም ሬዲዮ (ነጋሪተ- ወግ) “የሸገር እንግዳ” በተባለው ዝግጅት እንግዳ ሆነው አዘጋጇ ጋዜጠኛ ወ/ሮ መዓዛ ሦስት ቅዳሜ አዋይተዋቸው ነበር፡፡ በዚያ ጨዋታቸው ወ/ሮ ገነት ከተናገሩት ብዙው ነገር ከንክኖኝ ከጊዜ አንጻር ባይሆን በጥቂቶቹ ላይ ጥቂት ነገር ለማለት አስቤ እየጫጫርኩ እያለሁ እንዲያውም በወ/ሮዋ በሐሰት ስማቸው ከጠፋ ወገኖችና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አንደኛው በጥሩ ምሁራዊ ተዋስኦ የተዋዛ ምላሽ ሰጥተው አሻሩልኝ፡፡ ይሁንና ወ/ሮዋ የተናገሩት አጉል ነገር በርካታ በመሆኑ ሁሉንም ለመዳሰስ ከጊዜና ከቦታ አንጻር የማይቻል በመሆኑ ዶክተሩ ለሁሉም አጉል ነገር መልስ ሳይሰጡ ቀሩ፡፡ እኔም እንማማርባቸው ዘንድ … [Read more...] about ወ/ሮ ገነት ዘውዴ እውን ነገሩ እንዲያ ነውን?
Archives for December 2014
የወያኔ ከንቱ ፈሊጥ! “ጅብን ሲወጉ በአሕያ ተጠግቶ ነው”
ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጅብ እንደሆነ አድርጎ ያስባል፡፡ ይታያቹህ! ከየትኛውም ሀገር ሕዝብ በተለየ መልኩ ታጋሹን፣ ቅኑን፣ ቅዱሱን፣ ስስት ስግብግብነት የሌለበትን፣ አስተዋዩን፣ እሱ እየተቸገረ እየተራበ እነሱን ያጠገበውን ያደለበውን ቸር ምስኪን ሕዝብ ጅብ ነው ብሎ ማሰቡ አይደንቃቹህም? ምን ይደረግ ድንቁርና ተጭኗቸው ይሄን አስከፊ ድንቁርናቸውን ገንዘባችን ብለው አጥብቀው ይዘውት በየት በኩል አስተውለው ይሄንን ማንነቱን ይረዱለት? እናም ጅብ ነው ብለው በማሰባቸው አሕያ እየፈለጉ እሱን በመጠጋት በእሱ በመከለል ሲዎጉት ቆይተዋ ሰሞኑንም በሰፊው ይሄንን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ወያኔ በዚህ በያዝነው በታሕሳስ ወር 2007ዓ.ም. ከታዋቂ ሰዎችና “ከከያኔያን (Artists)” ለ ሕዝብ ለሕዝብ አቅንኦተ ግንኙነት (Public diplomacy) እና ሕዝብን ለመደለል ተልእኮ በቻለው መጠን እሽ … [Read more...] about የወያኔ ከንቱ ፈሊጥ! “ጅብን ሲወጉ በአሕያ ተጠግቶ ነው”
ለጠ/ሚ/ሩ ጥሪ – የኦባንግ ጥሪ
“ዕርቅ ብቸኛ አማራጭ ነው” በሚል እምነታቸው ሁሉንም ወገኖች ነጻ ለሚያወጣ ትግል ራሳቸውን የሰጡት ኦባንግ ሜቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጥሪ የመልስ ጥሪ አሰሙ፡፡ ከአቶ ሃይለማርያም የሰሙትን የእንነጋገር ጥሪ በአዎንታዊነቱ ተመልክተውታል፡፡ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ይህንን የተናገሩት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ያቀረቡትን “ለጋራ አገራችን በጋራ እንወያይ የሚል ጥሪ ማቅረብ ግን እፈልጋለሁ” ማለታቸውን ተከትሎ ነው፡፡ ከሁሉም ፓርቲዎች ጋር በተናጠል መወያየት አንደማይቻል የገለጹት ሃይለማርያም፤ በሦስት ደረጃዎች የመደቧቸውን የተቃዋሚ ፓርቲዎች ባወገዙበት መግለጫቸው ማገባደጃ ላይ የእንነጋገር ጥሪ አሰምተዋል፡፡ በግልጽ ተለይቶ ያልቀረበው የእንነጋገር ጥሪ ለአኢጋን … [Read more...] about ለጠ/ሚ/ሩ ጥሪ – የኦባንግ ጥሪ
“መንግሥት ከደላሎች ጋር አይደራደርም” ኃይለማርያም
ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት መንግስት በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፉሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በኢትዮጵያውያን ላይ የተከሰተውን ስቃይ እና በደል ተከትሎ ለስራ ወደ አረብ ሀገራት በሚደረግ ጉዞ ላይ እገዳ መጣሉ ይታወሳል። በተለይ ያለአንዳች የህይወት ዋስትና ወደ ተጠቀሱት ሃገራት በኮንትራት የሚሄድ ሰራተኞችን ከገጠር እስከ ከተማ በዘለቀ ድለላ ህጋዊ ፈቃድ አግኝተው ዜጎችን እያጋዙ የነበሩ የአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ባለቤት ቢሮዎች መዘጋታቸው አይዘነጋም። ዘግይቶም ቢሆን መንግስት በወቅቱ ወሰደ በተባለው እርምጃ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ህይወት ከአስከፊው የአረብ ዓለም ስቃይ መታደግ ቢችልም ከግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎቻችንን ህይወት ስላለበት ሁኔታ የተጠቀሱትን የኤጀንሲ ባለቤቶች በህግ ለመሞገት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ቴድሮስ አድሃኖም የገቡትን ቃል … [Read more...] about “መንግሥት ከደላሎች ጋር አይደራደርም” ኃይለማርያም
በ5 ዓመቱ ሕፃን ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት የፈፀመው በ20 ዓመት እሥራት ተቀጣ
አስራ ሦስት ዓመት ባልሞላው ሕፃን ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ፈፅሟል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተበት የ23 ዓመቱ ወጣት ሳሙኤል መርዕድ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ20 ዓመት እሥራት እንዲቀጣ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ከትናንት በስቲያ ታህሳስ 13 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈበት። ዐቃቤ ሕግ ለፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት በየካቲት 06 ቀን 2006 ዓ.ም ባቀረበው ክስ ላይ እንደዘረዘረው፤ የ23 ዓመቱ ወጣት ከእርሱ ጋር አንድ አይነት ፆታ ባለውና ዕድሜው ከ13 ዓመት በታች በሆነው ታዳጊ ልጅ ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት ለማድረስ አስቦ ተንቀሳቅሷል ይላል። በዚህም መሠረት በጥቅምት 24 ቀን 2006 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 8፡00 ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 01/02/03 ክልል ልዩ ቦታው ጌሾ ተራ ተብሎ … [Read more...] about በ5 ዓመቱ ሕፃን ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት የፈፀመው በ20 ዓመት እሥራት ተቀጣ
ጀግና!
ማን ነው እሱ አንበሳ ፤ ክህደትን ከሀዲ በመላ ምርኮ ጣይ ፤ የሐበሻ ጋንዲ ታሪክ ሠሪ አርበኛ ፤ ልበ ሙሉ ጀግና ምርጥ ብርቅ ዜጋ ፤ ኮስታራ ቆፍጣና በንስር ክንፎቹ ፤ አየር ላየር ሔዶ ሽው ባይ እንደ ነፋስ ፤ ዱብ እንደ በረዶ ምርኮን በዓይነት ይዞ ፤ ጠፍንጎ ቀፍድዶ መቸ ይህ ብቻ ነው ፤ ቆራጡ ሳተና ከእኛ ጋር የሆኑ ፤ አሉን ብዙ ገና እውነት መሰላቹህ? ፤ ቢመስል ደናና ምንም እንዳልከፋው ፤ ቢታይ ብሎ ዘና ልክ እንደተመቸው ፤ ቢስቅ በገናና ሀገር ሕዝብ የጠላ ፤ ከጦር ማን አለና ለማን ሲል ገባና ፤ አይደል ለጅል ዝና ለእናት ሀገሩ እንጅ ፤ ላለበት አደራ ለወገኑ እንጅ ፤ ሊያድን ከመከራ አይደለም ለቡድን ፤ ለጎጥ ለደንባራ ለጠባብ ጥርቅም ፤ ለቅጥረኛ ጎራ ከነ አካይስት በቀር ፤ ከነ ሕልመ … [Read more...] about ጀግና!
አገሬ!
የኔነት መለያ ~ የናት ያባቴ አገር ~ የተወለድኩባት፣ ስረ መሰረቴ ~ ቅርንጫፍ ሀረጌ ~ እትብቴ ያለባት፣ ተስፋዬ : ውጥነኔ ~ ህልሜ ሚፈታባት፣ ሀገሬ የኔ ናት~ ፣ ሀገሬ እርስቴ ናት~። አፈሩን ፈጭቼ ፣ ውሀ ተራጥቼ ፣ ዘልዬ ቦርቄ ~ ያደኩበት መንደር ፣ በሀሳብ በርሬ ~ በምናብ ከንፌ~ የማርፍባት ሰፈር ፣ የማንነቴ ምንጭ ~ መመኪያ አገሬ፣ አድባሬ አውጋሬ ፣ የዘወትር ህልሜ ~ የድካሜ እፎይታ ~ ማረፊያዬ ጎጆዬ፣ የትም የትም ዞሬ ~ ማሳረጊያ ቤቴ ~ አንገት ማስገቢያዬ፣ አገሬ እማማዬ ። ቀየሩት ይሉኛል ~ አፈረሱት አሉኝ ~ ለወጡት ባዱኛ፣ የኛ ሰፈርማ ፣ ሜዳው ሸንተሩ ~ መቦረቂያ መስኩ ~ አሁን የት አለና፣ ተሸጠ ለሌላ ~ የነሱን ኪስ ሞላ። ይህው በቀደም ለት ፣ ደውዬ ልጠይቅ ~ የወዳጅ ደህንነት፣ ስልኩ ጠርቶ ጠርቶ ~ "• • … [Read more...] about አገሬ!
“የድሆች መናጢነት የሚመጣው ሰነፍ ስለሆኑ አይደለም” አዳም ረታ
". . . ፖለቲካ ለሀገር ማሰብ ነው፡፡ ፖለቲካ መታደል ከተጨመረበት ለአገርና ውስጥዋ ለሚኖረው ለሕዝብ መልካም ለመስራት መጣር ነው፡፡ ከራስ በላይ ነፋስ በሚባለው ነገር አላምንም፡፡ ከራስ በላይ ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ሰፈር፣ ወረዳ፣ አውራጃ ክፍለሀገርና አገር አሉ፡፡ የቻለበትም አህጉርና አለምን በልቦናው ይከታል፡፡ "የአገራችን አንድ የሚታይ ማንም የሚያወራበት ፀባይዋ በደሃና በተራራ የተሞላች መሆኗ ነው፡፡ አንድ ሰው በሀገሩ ደሃ መሆን የለበትም:: ቢያንስ መሰረታዊ ፍላጎቶቹና መብቶቹ መጠበቅ አለባቸው፡፡ የድሆች መናጢነት የሚመጣው ሰነፍ ስለሆኑ አይደለም፡፡ የለፉበት ውጤት በጥቂት ማንአለብኝ ባዮች ስለሚዘረፍ ነው፡፡ "እነዚህም ዘራፊዎች ዝርፊያቸውን ያለሀሳብ ለማካሄድ ማስፈራራትንና ራሳቸው ያወጡትን ህግ ይጠቀማሉ፡፡ ድሆች ወይም ጭቁኖች መብታቸውን ለማስከበር የሚነሱት ከወደቁበት … [Read more...] about “የድሆች መናጢነት የሚመጣው ሰነፍ ስለሆኑ አይደለም” አዳም ረታ
ኢህአዴግ በባህር ዳር ግድያ ፈጸመ!
በእምነት ቦታ ይገባኛል ነዋሪዎች ባሰሙት ጥያቄ ኢህአዴግ የጥይት መልስ ሰጠ፡፡ ድርጊቱን በምስል በማያያዝ በተለያዩ ማኅበራዊ ገጾች ያሰራጩት ክፍሎች አዛውንትና መነኮሳት ሳይቀሩ መደብደባቸውንና መቁሰላቸውን በምስል አስደግፈው አመልክተዋል፡፡ አኻዙ በትክክለኛው ባይታወቅም አምስት የሚደርሱ ሰዎች ሕይወታቸው እንዳለፈ በማኅበራዊ ገጾች የተበተኑት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አንዳንድ የድረገጽ ዜናዎችም በአኻዝ ከመለያየት በስተቀር የግድያውንና የድብደባውን መጠን በመግለጽ ዜናቸውን አስፍረዋል፡፡ ድርጊቱን የፈጸመው ኢህአዴግ ስለሞቱትና ስለተደበደቡት መነኮሳትና አዛውንት እንዲሁም ሌሎች ወገኖች ይህንን መረጃ እስካጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ ይፋዊ ማስተባበያ አልሰጠም፡፡ ይልቁንም ከሁለት ሳምንት በፊት ኢህአዴግ የፌዴራል ምክት ሚ/ሩን በፖሊስ ፕሮግራም በማቅረብ የፌስቡክ ዜናዎችን አትመኑ በማለት … [Read more...] about ኢህአዴግ በባህር ዳር ግድያ ፈጸመ!
ሃናን በመድፈር የተጠረጠሩት ክስ ተመሰረተባቸው
በ16 ዓመቷ ታዳጊ ሃና ላላንጎ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በመፈፀም ለሞት አብቅተዋታል በተባሉ አምስት ተጠርጣሪዎች ላይ የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ክስ መሰረተባቸው። ዐቃቤ ሕግ ትናንት ማክሰኞ ታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ ሁለት ሲሆን፤ ለአካለመጠን ያልደረሰችን ሴት በአሰቃቂ ሁኔታ መድፈር እና ከባድ የሰው መግደል ወንጀል የሚሉት ክሶች ተጠቅሶባቸዋል። ከትናንት በስቲያ ሜክሲኮ በሚገኘው በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የነበረውን የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ያጠናቀቀው ይህ ጉዳይ ከዚህ በኋላም በልደታ ፍርድ ቤት መታየቱን ይቀጥላል። በመሆኑም በዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ዝርዝር ውስጥ ስማቸው የተጠቀሰው አምስቱ ተጠርጣሪዎች 1ኛ ተከሳሽ ሳምሶን ስለሺ ሙያ ሹፌር፣ 2ኛ ተከሳሽ በዛብህ ገ/ማርያም ሾፌር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቃሉ ገ/መድህን … [Read more...] about ሃናን በመድፈር የተጠረጠሩት ክስ ተመሰረተባቸው