• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መነሻው ከትግራይ የሆነ 180 ሺህ ብር በላይ ሃሰተኛ የብር ኖት ንብ ባንክ ሊቀየር ሲል ተያዘ

September 24, 2020 04:02 pm by Editor Leave a Comment

ከ180 ሺህ ብር በላይ ሀሰተኛ ገንዘብ ኖቶችን ወደ ንብ ባንክ ወስደው ሊቀይሩ የነበሩ ሁለት ግለሰቦች ዛሬ በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ሁለቱ ግለሰቦች በሕጋዊ ባንክ ስም ተመሳስሎ በተሰራ እና ወደፊት በሚጣራ ቲተር በመጠቀም ከ180 ሺህ ብር በላይ ሃሰተኛ ገንዘብ ወደ ንብ ባንክ ወስደው ሊቀይሩ ሲሉ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ግለሰቦቹ የያዙትን ሃሰተኛ ብር ንብ ባንክ ካዛንቺስ ቅርጫፍ ካሉ ሰራተኞች ጋር 40 ከመቶ ለባንክ 60 ከመቶ ለራሳቸው ለማዋል ስምምነት አድርገው ከመኪናቸው አወጥተው ብሩን ሊመነዝሩ ሲሉ በባንኩ ጥቆማ በተደረገ ክትትል በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገልጿል።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የፋይንስና ንግድ ነክ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ አበበ ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ጋር በተደረገ ክትትል ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ከዚያም ባለፈ በቱሉ ዲምቱ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተደረገ ፍተሻ ተመሳሳይ መጠን ያለው ሃሰተኛ ብር መያዙን ረዳት ኮሚሸነር ብርሃኑ ተናገረዋል።

በአሁኑ ወቅት ግለሰቦቹ በቁጥጥር ሥር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ ይገኛልም ነው ያሉት።

ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ አያይዘውም ባንኮችም ሆኑ ህብረተሰቡ ከአዲሱ ብር ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚታዩ ማንኛውንም ህገወጥ እንቅስቃሴ ለጸጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡ አሳሰበዋል። (ታሪክ አዱኛ፤ ፋና – ኤፍ.ቢ.ሲ)

ከሌላ ሦስተኛ ወገን ለማረጋገጥ ባይቻልም ሁለቱ ግለሰቦች ይዘውት የነበረው ብር በቡና ኢንተርናሽናል ባንክ መቀሌ ሞሚና ቅርጫፍ በታተመ እና እናት ባንክ አዲሃቂ ቅርጫፍ በታተመ ማሸጊያ የተጠቀለለ እንደነበር በማኅበራዊ ሚዲያ ዜና ከሚያሰራጩ የተገኘው ዘገባ ያመለክታል። (ፎቶው ለማሳያነት የቀረበ እንጂ የተያዘው አይደለም)

ተጨማሪ፥ ይህንን ዜና ካተምን በኋላ የፌዴራል ፖሊስ በርግጥ ገንዘቡ የመጣው ከትግራይ ክልል መሆኑን ይኸውም ከቡና ኢንተርናሽናል ባንክ መቀሌ ሞሚና ቅርጫፍ በታተመ እና እናት ባንክ አዲሃቂ ቅርጫፍ በታተመ ማሸጊያ የተጠቀለለ እንደነበር በፌስቡክ ገጹ መዘገቡን አረጋግጠናል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: fake birr, new birr notes, new currency

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule