• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መቶ ብር ከየት ወዴት?

July 23, 2015 08:49 am by Editor 2 Comments

ትናንት ኣመሻሽ ላይ፤ ከYohanes Molla ጋር ተቀጣጥረን ተገናኘን ፡፡ካልዲስ ገብተን እኔ ኣንድ ፍንጃል ቡና ሳዝዝ ፤ ዮሀንስ ሲያቀብጠው ኣንድ ቡና እና የባራክ ኦባማን ጆሮ የሚያህል ቦምቦሊኖ ኣዘዘ፡፡ በመጨረሻ ኣስተናጋጂቱ የእዳችንን ደረሰኝ ኣምጥታ ጠረጴዛው መሀል ላይ ኣኖረችው ፡፡እሱ እኔ እስክከፍል ሲጠብቅ እኔ እሱ ይከፍላል ብየ ስጠብቅ ካብ ለካብ እየተያየን በጣም እረጅም ጊዜ ተጎለትን፡፡

በመካከሉ የኢትዮጵያን ማህበራዊና ፖለቲካዊ ርእሰ ጉዳይ ጨርሰን “ፌንጣ ስንት እግር ኣላት? ስድስት ነው ኣራት?” በሚል ጉንጭ ኣልፋ ክርክር ተጠመድን፡፡ ወሬ ኣልቆብን ካጠገባችን ከተቀመጡ ተስተናጋጆች ወሬ እየተበደርን ስናወራ ቆየን፡፡ በመጨረሻ ካፌው ጭርር ብሎ ኣስተናጋጆች እንድንወጣላቸው እግራችን ስር መጥረጊያ ኣስገብተው ይጠርጉ ጀመር፡፡

ድንገት በብሄረሰቦች ላይ የሚነገረው ቀልድ እንዴት ኢ-ፍትሃዊነት እንደሆነ ኣንስቼ መከራከር ጀመርሁ፡፡በተለይም ጉራጌን እንደ ቋጣሪ ማየት መሰረት የለሽ መሆኑን ፤ እኔ የማውቃቸው ጉራጌ ጓደኞቼ ባጠቃላይ በጣም ለጋሶችና ኣባ መስጠቶች መሆናቸውን በመጥቀስ በስሜት ነድጄ ጠረጴዛ እየደበደብኩ ተናገርኩ፡፡ የሚቻል ከሆነ ጉራጌን እንደ ንፉግ የሚስሉ ኮሜድያን ባስቸኳይ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ኣሳሰብኩ፡፡

ወድያው ዮሀንስ ሞላ የኣባባሌን እውነተኝነት በተግባር ለማረጋገጥ ከኪሱ መቶ ብር መዥርጦ ሂሳቡን ዘጋው፡፡

ኣባቴ ከቅዱስ መጽሀፍ ኣንድ ምእራፍ ሳያነብ እንደማይተኛ እኔ ደግሞ ከ“ፍቅር እስከመቃብር” ኣንድ ኣንቀጽ ሳላነብ እንቅልፍ ኣይወስደኝም፡፡ከዮሀንስ ጋር ከተሰነባበትን በኋላ እቤቴ ገብቼ “ኣዲስ ኣበባ” የሚለውን ምእራፍ ገለጥሁ፡፡

ብዙዎቻችሁ እንደምታስታውሱት፤ በዛብህ ቦጋለ፤ ሰብለን ለመጥለፍ ያደረገው ሙከራ ከከሸፈበት በኋላ ከፊታውራሪ መሸሻ ቁጣ ሸሽቶ ኣዲስ ኣበባ ይገባል፡፡ እናም ሱልሉልታ ኣካባቢ ከሲራራ ነጋዴዎች ጋር ይወዳጃል፡፡ ኣንድ ቀን ከኒህ ወዳጆቹ ኣንዱ ከሆኑት ነጋድራስ ሁነኛው ጋር እያወራ ነው፡፡

“ኣዲስ ኣበባ የማውቀው ሰው የለኝም፡፡ ምን ማድረግ የሚሻለኝ ይመስልዎታል፡፡ እስኪ ይምከሩኝ ” ኣለ በዛብህ፡፡

“ገንዘብ ካለህ ኣትቸገርም፡፡ ገንዘብም የምታውቀው ሰውም ከሌለህ ነው ችግሩ! እስቲ ለማንኛውም ከኛ ጋር ጉለሌ ስፈርና ስራ እስክታገኝ የምትቆይበትን ስፍራ እንፈልጋለን” ኣሉ ነጋድራስ፡፡

“ገንዘብስ ከእናንተ ጋር ያገጣጠሙኝ ወዳጆች ኣዋጥተው የሰጡኝ ኣንድ መቶ ብር ኣለኝ“

”ኣንድ መቶ ብር ካለህማ፤ ማለፍያ ቤት ተከራይተህ፤ ማለፍያ ቀላቢ ቀጥረህ ብዙ ጊዜ ያቆይሃል . . . ገንዘብህ እንዳይጠፋብህ መጠንቀቅ ነው”(ፍቅር እስከመቃብር፤ ገጽ 434)ኣጀብ ነው!! ኣንድ ኢትዮጵያዊ በመቶ ብር ኣሪፍ ቤት ተከራይቶ ምግብ ኣብሳይ ሰራተኛ ቀጥሮ ለብዙ ጊዜ መኖር የሚችልበት ዘመን መኖሩን ሳስብ፤ በጊዜ መኪና ወደ ድሮ መመረሽ ያምረኛል፡፡ ኢትዮጵያ ከየት ወዴት የሚለውን ለማጥናት ኣቋራጩ መንገድ “መቶ ብር ከየት” ወዴት የሚለውን ማጥናት ኣይመስላችሁም?

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    July 24, 2015 07:33 pm at 7:33 pm

    “የወር ገቢያችሁ ከሶስት (፫፻ብር)በታች የሆናችሁ የድሃ ድሃ ነዋሪዎች!? ፀረ ልማት…
    ***ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች እንዲሁም የደሃ ድሃ ነዋሪዎች….ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝቦች!!ድሮ የተረሳችሁ፣ የተጨቆናችሁ፣ በአድሃሪው መንግስት ኩንታል ጤፍ በአምስት ብር እየገዛችሁ፣ በመቶ ብር ኣሪፍ ቤት ተከራይቶ ምግብ ኣብሳይ ሰራተኛ ቀጥሮ ወለድ አበድሮ ሠንጋ ጥሎ ጎረቤት አብልቶ ቅርጫት እንቁላል በሽልንግ ገዝቶ እየበላ የሀገሪቷን ኢኮኖሚ አፈርድሜ ያገባ የዋህና ጨዋ ድሃ ሕዝብ….ድህነትን ተረት ለማድረግ ብድርና ልመናን መዝራት ነው። ዕድሜ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት እንቁላል ዕንቁ ሆነ! እናንት የድሮ ሥርዓት ናፋቂዎች የድሮ መቶ ብር መቶ ብር አለ በለው!

    Reply
  2. Sanyii says

    July 25, 2015 09:44 am at 9:44 am

    Typical racist jokes by a nagtegna (be’ewuketu) on Guraghe. Amaran bilhna asteway adrgo lelawun ye’Ethiopia bheroch feri, yewah, mogn, etc adrgo yemesal yalefebetn technic newu be’ewuketu yetetekemewu. That is why I advocate English as Federal Working Language to make the playing field level for all Ethiopian nations and nationalities. Otherwise, keeping Amharic as it is right now will continue putting others at a disadvantage, including the Tigres (it is only a matter of time and they will be cast aside when their influence dwindle or come to an end soon.) So, my advise for the Tigrean Elites is to exaclty that while they can influence better which is now. By the way making English Federal Working Language will also help Amharic speakers as they will not be treated as an enemy when they go to other Ethiopian regions. Because I strongly believe that it is the language that is causing all these divide and replacing it with a neutral language is the best solution! Chigru ende Metmku Yohannes yemisemagn’n atahu.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule