• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መቶ ብር ከየት ወዴት?

July 23, 2015 08:49 am by Editor 2 Comments

ትናንት ኣመሻሽ ላይ፤ ከYohanes Molla ጋር ተቀጣጥረን ተገናኘን ፡፡ካልዲስ ገብተን እኔ ኣንድ ፍንጃል ቡና ሳዝዝ ፤ ዮሀንስ ሲያቀብጠው ኣንድ ቡና እና የባራክ ኦባማን ጆሮ የሚያህል ቦምቦሊኖ ኣዘዘ፡፡ በመጨረሻ ኣስተናጋጂቱ የእዳችንን ደረሰኝ ኣምጥታ ጠረጴዛው መሀል ላይ ኣኖረችው ፡፡እሱ እኔ እስክከፍል ሲጠብቅ እኔ እሱ ይከፍላል ብየ ስጠብቅ ካብ ለካብ እየተያየን በጣም እረጅም ጊዜ ተጎለትን፡፡

በመካከሉ የኢትዮጵያን ማህበራዊና ፖለቲካዊ ርእሰ ጉዳይ ጨርሰን “ፌንጣ ስንት እግር ኣላት? ስድስት ነው ኣራት?” በሚል ጉንጭ ኣልፋ ክርክር ተጠመድን፡፡ ወሬ ኣልቆብን ካጠገባችን ከተቀመጡ ተስተናጋጆች ወሬ እየተበደርን ስናወራ ቆየን፡፡ በመጨረሻ ካፌው ጭርር ብሎ ኣስተናጋጆች እንድንወጣላቸው እግራችን ስር መጥረጊያ ኣስገብተው ይጠርጉ ጀመር፡፡

ድንገት በብሄረሰቦች ላይ የሚነገረው ቀልድ እንዴት ኢ-ፍትሃዊነት እንደሆነ ኣንስቼ መከራከር ጀመርሁ፡፡በተለይም ጉራጌን እንደ ቋጣሪ ማየት መሰረት የለሽ መሆኑን ፤ እኔ የማውቃቸው ጉራጌ ጓደኞቼ ባጠቃላይ በጣም ለጋሶችና ኣባ መስጠቶች መሆናቸውን በመጥቀስ በስሜት ነድጄ ጠረጴዛ እየደበደብኩ ተናገርኩ፡፡ የሚቻል ከሆነ ጉራጌን እንደ ንፉግ የሚስሉ ኮሜድያን ባስቸኳይ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ኣሳሰብኩ፡፡

ወድያው ዮሀንስ ሞላ የኣባባሌን እውነተኝነት በተግባር ለማረጋገጥ ከኪሱ መቶ ብር መዥርጦ ሂሳቡን ዘጋው፡፡

ኣባቴ ከቅዱስ መጽሀፍ ኣንድ ምእራፍ ሳያነብ እንደማይተኛ እኔ ደግሞ ከ“ፍቅር እስከመቃብር” ኣንድ ኣንቀጽ ሳላነብ እንቅልፍ ኣይወስደኝም፡፡ከዮሀንስ ጋር ከተሰነባበትን በኋላ እቤቴ ገብቼ “ኣዲስ ኣበባ” የሚለውን ምእራፍ ገለጥሁ፡፡

ብዙዎቻችሁ እንደምታስታውሱት፤ በዛብህ ቦጋለ፤ ሰብለን ለመጥለፍ ያደረገው ሙከራ ከከሸፈበት በኋላ ከፊታውራሪ መሸሻ ቁጣ ሸሽቶ ኣዲስ ኣበባ ይገባል፡፡ እናም ሱልሉልታ ኣካባቢ ከሲራራ ነጋዴዎች ጋር ይወዳጃል፡፡ ኣንድ ቀን ከኒህ ወዳጆቹ ኣንዱ ከሆኑት ነጋድራስ ሁነኛው ጋር እያወራ ነው፡፡

“ኣዲስ ኣበባ የማውቀው ሰው የለኝም፡፡ ምን ማድረግ የሚሻለኝ ይመስልዎታል፡፡ እስኪ ይምከሩኝ ” ኣለ በዛብህ፡፡

“ገንዘብ ካለህ ኣትቸገርም፡፡ ገንዘብም የምታውቀው ሰውም ከሌለህ ነው ችግሩ! እስቲ ለማንኛውም ከኛ ጋር ጉለሌ ስፈርና ስራ እስክታገኝ የምትቆይበትን ስፍራ እንፈልጋለን” ኣሉ ነጋድራስ፡፡

“ገንዘብስ ከእናንተ ጋር ያገጣጠሙኝ ወዳጆች ኣዋጥተው የሰጡኝ ኣንድ መቶ ብር ኣለኝ“

”ኣንድ መቶ ብር ካለህማ፤ ማለፍያ ቤት ተከራይተህ፤ ማለፍያ ቀላቢ ቀጥረህ ብዙ ጊዜ ያቆይሃል . . . ገንዘብህ እንዳይጠፋብህ መጠንቀቅ ነው”(ፍቅር እስከመቃብር፤ ገጽ 434)ኣጀብ ነው!! ኣንድ ኢትዮጵያዊ በመቶ ብር ኣሪፍ ቤት ተከራይቶ ምግብ ኣብሳይ ሰራተኛ ቀጥሮ ለብዙ ጊዜ መኖር የሚችልበት ዘመን መኖሩን ሳስብ፤ በጊዜ መኪና ወደ ድሮ መመረሽ ያምረኛል፡፡ ኢትዮጵያ ከየት ወዴት የሚለውን ለማጥናት ኣቋራጩ መንገድ “መቶ ብር ከየት” ወዴት የሚለውን ማጥናት ኣይመስላችሁም?

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    July 24, 2015 07:33 pm at 7:33 pm

    “የወር ገቢያችሁ ከሶስት (፫፻ብር)በታች የሆናችሁ የድሃ ድሃ ነዋሪዎች!? ፀረ ልማት…
    ***ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች እንዲሁም የደሃ ድሃ ነዋሪዎች….ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝቦች!!ድሮ የተረሳችሁ፣ የተጨቆናችሁ፣ በአድሃሪው መንግስት ኩንታል ጤፍ በአምስት ብር እየገዛችሁ፣ በመቶ ብር ኣሪፍ ቤት ተከራይቶ ምግብ ኣብሳይ ሰራተኛ ቀጥሮ ወለድ አበድሮ ሠንጋ ጥሎ ጎረቤት አብልቶ ቅርጫት እንቁላል በሽልንግ ገዝቶ እየበላ የሀገሪቷን ኢኮኖሚ አፈርድሜ ያገባ የዋህና ጨዋ ድሃ ሕዝብ….ድህነትን ተረት ለማድረግ ብድርና ልመናን መዝራት ነው። ዕድሜ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት እንቁላል ዕንቁ ሆነ! እናንት የድሮ ሥርዓት ናፋቂዎች የድሮ መቶ ብር መቶ ብር አለ በለው!

    Reply
  2. Sanyii says

    July 25, 2015 09:44 am at 9:44 am

    Typical racist jokes by a nagtegna (be’ewuketu) on Guraghe. Amaran bilhna asteway adrgo lelawun ye’Ethiopia bheroch feri, yewah, mogn, etc adrgo yemesal yalefebetn technic newu be’ewuketu yetetekemewu. That is why I advocate English as Federal Working Language to make the playing field level for all Ethiopian nations and nationalities. Otherwise, keeping Amharic as it is right now will continue putting others at a disadvantage, including the Tigres (it is only a matter of time and they will be cast aside when their influence dwindle or come to an end soon.) So, my advise for the Tigrean Elites is to exaclty that while they can influence better which is now. By the way making English Federal Working Language will also help Amharic speakers as they will not be treated as an enemy when they go to other Ethiopian regions. Because I strongly believe that it is the language that is causing all these divide and replacing it with a neutral language is the best solution! Chigru ende Metmku Yohannes yemisemagn’n atahu.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule