ያለ ስም፣ ስም – ስጡኝ ቅጡኝ፣ አስቀጡኝ፤ አግዙኝ፣ ወርውሩኝ፣ … በማጎሪያችሁ እሰሩት… እጀን፣ … በካቴናችሁ ‘ጠንዙት’ እግሬን፣ …. በእግር ብረታችሁ ቸንክሩት፣ ገንዙት፣ … ይደንዝዝላችሁ ሽባ ሆኘ ልቅር፣ ‘’ልሰንከልላችሁ’’:: ……… እንካችሁ …. ጀርባዬን መጫሚያ፣ መዳፌን፤ ግረፉት፣ አቃጥሉት፣ …. በኮረንቲ ገመድ የሰራ አከላቴ፣ ይክሰል፣ ይሁን ዓመድ:: ……… ዝረፉት … ሀብቴን ቤትና ንብረቴን፣ በምድር ያለኝን፤ ሰብስቡ፣ አከማቹት፣ ለዓለም ይሁናችሁ ለማይጠረቃው፣ ለከርስ ዓላማችሁ ለማፍረስ፣ ለመናድ፣ ለጥፋት ግባችሁ:: ……… እንካችሁ…… ደረቴን እንካችሁ…… ግ’ባሬን፤ ለታንክ፣ ለመትረጊስ፣ ለጥይታችሁ አፍስሱት ደሜን፣……. እስኪከረፋችሁ አድቅቁት አጥንቴን፣……. እስኪወጋችሁ::……. እንካችሁ……… እንካችሁ ሥጋ – ሰውነቴን፣ … [Read more...] about እኔ አማልሰጣችሁ፣ እናንተ እማትወስዱት! …
Literature
ጽፈኪን
ይድረስ — ለኃይለማርያም ደሳለኝ!
ለ’ክቡር’ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ለኢሕአዴግ ሊቀ-መንበር፣ ጠቅላይ ‘አዛዥ’ ለ"አግዓዚ" ጦር...፤ ይድረስ ለአቶ ኃይለማርያም! በስምዎ ባዘሏት ወላዲተ-አምላክ.. በወልድ በእየሱስ ክርስቶስ ስም ልያዝዎ፣ ኢትዮጵያን በጥይት አያቃጥሏት... እግዚአብሔር አባት ይቅር ይበልዎ! በደርግም ሆነ በወያኔ ዘመን ባገር ያሴሩ፣ እስከዛሬ ሕዝብን ሲያስጨፈጭፉ የኖሩ፣ “እግዚአብሔርን አናውቅም” ብለው የካዱ ነበሩ፤ እርስዎ ግን፣ ከቤተሰብዎ ጋር ማዕድ ሲጋሩ፣ የየዕለቱን ጸሎትዎን ሲያበስሩ፣ የአምላክን ስም ነጋ-መሸ እየጠሩ፣ ይመስለኝ ነበር በእምነት የከበሩ፤ ... ግና ከልብ እውነት ካልዘመሩ፣ ትዕዛዛዊ ቃላቱን ካልተገበሩ፣ እምኑ ላይ ነው ታዲያ አምልኮዎ? የአምላክን መሻት መፈጸምዎ? ከአረመኔዎች ጋር … [Read more...] about ይድረስ — ለኃይለማርያም ደሳለኝ!
እናት ሀገር!
“አንቺ እማማ ኢትዮጵያ አንቺ እናት ዓለም” ሎሬትሽ እያቆላመጠ ይነግርሽ እንደነበር በቀለም፤ እወቂበት ከእንግዲህ አብጂለት ፍቱን መላ፣ የሚሞትልሽ እንጂ የሚገልሽ ላይበላ፤ ህዋሳትሽ ይንቀሳቀስ ሰሜን-ደቡብ ምዕራብ-ምስራቅ፣ የአለላ ተምሳሌቱ የሕዝቦችሽ ህብረት ይድመቅ፤ ብድግ በይ ተራመጂ በእንፉቅቅ መዳኽሽ ያብቃ፣ የውብ ህይወት አዲስ ምዕራፍ በግዛትሽ ይገንባ! እናት አገር ባለታሪክ ተነሽ ቤትሽን አጽጂ፣ የተዝረከረከውን በፕሮፓጋንዳ ፈንጂ፣ በተከፈተው ጉድጓድ ይግባ ጠራርገሽ አስወግጂ። ዳግም እንዳትረቺም ባባይ-ጠንቋይ ጋጋታ፣ እጆችሽን ከምር ዘርጊ ወደ ፈጠረሽ ጌታ፣ አምላክሽ ካንቺው ነውና የእስላም የክርስቲያኑ፣ ፍጠኚ ታሪክ ይከወን ሳያልፍብሽ ዘመኑ። ‘ዳዊቶችሽ’ በጠጠር ‘ጎልያድን‘ ሲፋለሙ፣ የዝናሽን ውድ ዕሴት … [Read more...] about እናት ሀገር!
“እንዳትረግጡት…. የኢትዮጵያን ዐፈር – መሬት!”
‘ባካችሁ ......... ’ባካችሁ.......... እናንት በምድረ-ኢትዮጵያ ያላችሁ፤ "አትሂዱ …..በ'ግራችሁ..." ከቻላችሁ ..... "ብረሩ ክንፍአው’ታችሁ።” ግን……..አደራ……….. .......... አንዳትረገጡት ……. መሬቱን እንዳታዩት……… አፈሩን፤ ብታርሱት...... አትዘሩበት ብዘሩበት ........ አይበቅልበት፤........ ደምነውና - የትላንና- የዛሬ - የአሁን፣ ትኩስ…. የፈሰሰበት አጥንት ነውና ያልደረቀ፣ "አጸደ-ህይወት" የወደቀበት እናንተም ከእንግዲህ፣ ''ዐጽም - 'ርስቴ'' የማትሉት፤……….. ያውም … [Read more...] about “እንዳትረግጡት…. የኢትዮጵያን ዐፈር – መሬት!”
ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ወይም “ጉማሬው” ዋናተኛ
አቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ከተጫነባቸው በኋላ በUN ኢትዮጵያን ወክሎ የመቀመጥ ስልጣናቸው ቀረና ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ። እድገት ወይም ውርደት (promotion ወይም demotion) ሳንል፣ ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ እንላለን። አቶ ዠ የሃገሪቱ የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው ተሾሙ። እንግዲህ “ፕሬዚደንት” የሚለው ቃል እስካለ ድረስ፣ ሹመቱ፣ ማዕረጉ ትልቅ ነው ተብሎ እንዲታሰብ የአቶ ዠ መልካም ፈቃድ ነው እንላለን። የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙበት ጊዜ ደግሞ እንዳጋጣሚ ሆኑ የኦሎምፒክ ውድድር የተቃረበበት ጊዜ ነበር። ዠ አዲሱ ቢሮአቸው ሆነው አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው። ሃገራቸውን በኦሎምፒክ መወከል። የሃገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ በኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ ተገኝቶ ማውለብለብ...። እንዴት ያለ ድንቅ ሃሳብ ሲሉ አሰቡ አቶ ዠ። እንግዲህ መሰደብ፣ መዋረድ፣ መሰደድ፣ … [Read more...] about ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ወይም “ጉማሬው” ዋናተኛ
“መዝሙሩማ…”!
“መዝሙሩማ” መዝሙር ነው - የኅብረ-ዜማ ውጤት፣ ሕዝብን ያስተሳሰረ - የአንድነት ሰንሰለት፤ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ - ከደቡብ እስከ ሰሜን... ተዳርሶ በድንገት፣ በቅብብሎሽ ያስተጋባ - የነጻነት አዝማች ልደት! ደራሲውም ሕዝብ ነው - መሳሪያውም ባህላዊ፣ ዘረኞችን እሚያሸማቅቅ፣ ግፈኞችን እሚያርበደብድ... ኃያል ድምፅ ምትሃታዊ! “መዝሙሩማ” መዝሙር ነው - የብሩህ ዘመን ብስራት፣ በደም ቀለም የተጻፈ! - እሚዘመር በሕዝብ አንደበት! (ስማ! አቶ “ጌታቸው”!) . . . ከእንግዲህማ አትልፋ - ዘመንህን በከንቱ አትጨርስ፣ ክፋት ፕሮፓጋንዳህን - እሳት ባገር ከመለኮስ፣ ይልቁንስ ጠጋ በል -“ሕዝበ-መዝሙሩን” በደንብ አጥና፣ ያንተም መፃዒ ዕድል - በሕዝብ ድል እንዲቃና! እንጂማ!... መዝሙሩማ ኀብረ-መዝሙር … [Read more...] about “መዝሙሩማ…”!
ጀግና ውለጅ እባክሽ !
የምሁር መሃይም - ተባይ አላዋቂ፤ የመሃይም ኩፍስ - አስመሳይ አዋቂ፤ የጅብ ባለ ጊዜ - ታፋ መራጭ ከሽንጥ፤ ያንበሳ ልክስክስ - ልፋጭ የሚያላምጥ የቁራ ዕርግብ መሳይ - ሠላምን አብሳሪ፤ የፈረስ አዝጋሚ - የግመል ሰጋሪ፤ ንጹህ ሰው ታሳሪ - በፈጠራ ወንጀል፤ ፍርደ ገምድል ዳኛ - ፈራጅ በቂም በቀል፤ የባዕድ ባለቤት - የነባር ባይተዋር፤ ሥልጡን ሥራ ፈቶ - ሞያ ቢስ ሲገብር፤ ልማድ ሆኖ ቀረ - አቀርቅሮ መኖር፤ በተወሇድንባት በጦብያ ምድር :: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ጀግና ውለጅ እባክሽ !
ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!
ይድረስ ለእኛ-ከእኛ! - ከላይ ልጀምር ካ’ናቱ፣ በብረት ኃይል ተከቦ - ከተኮፈሰው በከንቱ፣ ይድረስልኝማ ለወያኔ - ለጊዜያዊው ባለጉልበቱ፤ … “ለሕዝባዊነት መጣሁ” ብሎ - ሕዝብን በጥይት መቁላት የለምና፣ አቆልቁለህ እየውማ - የምትሄድበትን ጎዳና! የጭካኔ መጠንህ ጫፍ ደረሰ - የውሸት ቋትህ ሞላ፣ የ’እውቀት‘ ገደብህ አበቃ - ከእንግዲህ ላይኖርህ የቀረ ‘መላ’፣ ከወደቁ ወዲያ መንፈራገጥ.. እንዳይሆን ለመላላጥ፣ ሳሩንም ላለመጋጥ.. መሬቱንም ላለመናጥ…፣ ከአውሬነት ባህል ተላቆ - ሰውነትን ይሻልና፣ ይድረስ! ይድረስ! እልሃለሁ፤ ይድረስ! እንደገና፤ ዛሬ እንኳን እንደማመጥ - ይቅርብህማ ወንድሜ፣ በግፍ ተሞልተህ ጉዞ - ላይሆንህ መልካም ዕድሜ፣ “አበቅቴ ውሉን ሳይስት” - የአመሻሽ ጀንበር ሳትጠልቅብህ፣ ቆም ብለህ ማሰብ ጀምር - እንደ “ጆቤ”ህ፣ እንደ … [Read more...] about ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!
አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)
‹‹ጥበበኛ በጥበብ እግር ይመላለሳል›› (ጠቢብ የሐውር በእግር ጥበብ) እንዲሉ፣ አባተ መኩሪያ ከግማሽ ምታመት በዘለለ በኢትዮጵያ ቴአትር ሕዋ ውስጥ በጥበብ ለጥበብ ኖሯል፡፡ ለቴአትር እስትንፋሱ ነበርም ይሉታል፡፡ በርሱ ጥበብ ያለፉት ሁሉ፡፡ በጥበብ የባተው አዘጋጅ፣ የውዝዋዜ አሠልጣኝ (ኬሪዮግራፈር)፣ ጸሐፌ ተውኔት፣ የፊልም አዘጋጅ የነበረው አባተ መኩሪያ በአገሪቱ የቴአትር ታሪክ ውስጥ ስማቸው በግዘፍ ከሚነሱትና አሻራቸውን ካሳረፉ በኩሮች አንዱ ነበር፡፡ በተለይ በተውኔት አዘጋጅነት ስመ ጥር ለመሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ተውኔቶችን ወጥ እና ትርጉሞች በማዘጋጀቱ ይጠቀሳል፡፡ ከታዋቂ ሥራዎቹ መካከል ሀሁ በስድስት ወር (1966) አቡጊዳ ቀይሶ (1971)፣ መልእክተ ወዛደር (1971)፣ የመንታ እናት (1971)፣ መቅድም (1972)፣ ጋሞ (1973)፣ አሉላ አባነጋ (1979) ይጠቀሳሉ፡፡ … [Read more...] about አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)
“ሰው አይደለም ! …” አለኝ
ገና ቁጭ እንዳልኩኝ ቀጥሮኝ እንዳገኘኝ እከሌ ጨርሶ «ሰው አይደለም!» አለኝ ምነው? ምን አ’ረገህ ? «ሰው አይደለም!» ስልህ እኮ! ምን አ’ረገህ? «ሰው አይደለም!» አልኩህ። ቢራችንን አዘን በዝምታ ቆየን እንደገና ደግሞ ሳሉን እየሳለ አንገቱን ነቅንቆ «ሰው አይደለም!» አለ። ሰው ይመስላል አልኩኝ ስሜቱን ልረዳ ፊቱን መረመርኩኝ ባ’ይኑ እየገረፈኝ አይምሰልህ! አለኝ ግንባሩ ታጠፈ ጥርሶቹን ነከሰ ጠረጴዛ መታ፣ ቢራችን ፈሰሰ ልጠራርግ መጥታ - ልጅት እያየችኝ በፊቷ ምልክት ምን ሆኗል? አለችኝ መዳፌን አሳየሁ፣ ከንፈሬን አስረዘምኩ እኔም ልክ እንደሷው በምልክት መለስኩ እሱ ግን ቀጠለ «ሰው አይደለም» ማለት «ሰው አይደለም!» አልኩኝ እኔም ተመቸሁት በቢራ ተራጨን በውስኪ ታጠብን ስሙን እያነሳን «ሰው አይደለም!» አልን። ልጅትም … [Read more...] about “ሰው አይደለም ! …” አለኝ