• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!

August 11, 2016 04:01 am by Editor 1 Comment

ይድረስ ለእኛ-ከእኛ! – ከላይ ልጀምር ካ’ናቱ፣
በብረት ኃይል ተከቦ – ከተኮፈሰው በከንቱ፣
ይድረስልኝማ ለወያኔ – ለጊዜያዊው ባለጉልበቱ፤

… “ለሕዝባዊነት መጣሁ” ብሎ – ሕዝብን በጥይት መቁላት የለምና፣
አቆልቁለህ እየውማ – የምትሄድበትን ጎዳና!
የጭካኔ መጠንህ ጫፍ ደረሰ – የውሸት ቋትህ ሞላ፣
የ’እውቀት‘ ገደብህ አበቃ – ከእንግዲህ ላይኖርህ የቀረ ‘መላ’፣
ከወደቁ ወዲያ መንፈራገጥ.. እንዳይሆን ለመላላጥ፣
ሳሩንም ላለመጋጥ.. መሬቱንም ላለመናጥ…፣
ከአውሬነት ባህል ተላቆ – ሰውነትን ይሻልና፣
ይድረስ! ይድረስ! እልሃለሁ፤ ይድረስ! እንደገና፤
ዛሬ እንኳን እንደማመጥ – ይቅርብህማ ወንድሜ፣
በግፍ ተሞልተህ ጉዞ – ላይሆንህ መልካም ዕድሜ፣
“አበቅቴ ውሉን ሳይስት” – የአመሻሽ ጀንበር ሳትጠልቅብህ፣
ቆም ብለህ ማሰብ ጀምር – እንደ “ጆቤ”ህ፣ እንደ “ፃድቃን”ህ!

ይድረስ ለወንድማችን! የወገንህን ስቃይ ለምታራዝም፣
አውቀህም ሆነ፣ ሳታውቅ  – ለጥቃቅን ጥቅማ-ጥቅም፣
ለሀላፊና ጠፊ  – አብሮህ ለማይኖር  ቁስ፣
ህሊናህን ለምትዳርግ  – ለማይድን የጸጸት ውርስ፣
ለዘር ማንዘርህ ‘ለሚተርፍ‘ የስም ስብራት “ቅርስ”፤

ይድረስ ለእህታችን! የወገንሽን ጭንቅ ለምታበዢ፣
አውቀሽ እንደዘበት፣ ሳታውቂ  በስህተት ለምትናውዢ፣
በልጦ ለመገኘት፣  በምትከውኚው ድርጊት-ሃላፊ፣
የማያልፍ ክፉ ስም ተክለሽ  – ሳትጠቀሚ ለምታልፊ፣
የትውልድ እናት ሆነሽ  – የስምሽን ክብር ለምታጎድፊ፤

ይድረስ ለእኛ-ከእኛ!
ሕዝብ በመዶሻ ሲቀጠቀጥ፣ ምስማር ለምናቀብል ከንቱ፣
የዘረኝነት አጥሩን ሲያጥር፣ ማገር ለሆንን ለስርዓቱ፣
የጭቆና መረቡን ሲዘረጋ፣ እየተጋገዝን ለምንተበትብ፣
አስተዋጽዖ ለምናደርግ፣ ለከፋፍለህ ስልቱ ግብ፤
ለ”ልማታዊ መንግስት” ፌዝ፣ ለዘረኝነት “ፌዴራሊዝም”፤
ኃይል፣ ጉልበት ሆነን፣ እድሜውን ለምናራዝም፤

በ”ላም አለኝ በሰማይ..ቤት”፣ በአፓርትመንት ተስፋ፣
ዶላር ለምናፈስለት፣  ጨቋኝ እንዲደልብ፣ እንዲፋፋ፣

ይድረስ ለእኛ!
በመሃላ፣ በጩኸት..፣ ባደባባይ፣
“ክርስቲያን” ነኝ፣ “ሙስሊም” ነኝ ባይ፣
በማዕረግና ቅጽል ብዛት አይደለም እምነቱ፣
በቂምና በሸፍጥ አይደለም ስግደት፣ ጸሎቱ፤
መስጂድ፣ ቤተ-ክርስቲያን.. እምናምስ፣
የመለኮት ጸጋ ማደሪያውን እምናረክስ፣
በኢ-አማኝ መሰሪዎች ሴራ፣ ጽላተ-ታቦቱን እምንከስ፣
የእምነት መሰረተ-ስርዓቱን፣ ዶግማ-ቀኖና እምናፈርስ፣
መቅሰፍት መጥራት ነው በራስ፣ ቅስፈት መመኘት ነው ለሀገር፣
የዘላለም ዓለም እሳት፣ እማይበርድ የሲዖል ጣር፤

ይድረስ ለእኛ!
“መሬት እሰጣችኋለሁ..” ሲል፣ በካሬ ሜትር መትሮ፣
ከየት አምጥቶ? ብለን ብንጠይቅ፣ ባለቤቱን በግፍ አባሮ፤
ከጉልበተኞች ተጠግቶ — ተገን የሌለውን ደሀ ገፍቶ፣
የሚያለቅሱ ህጻናትን እምባ — በግፍ ረግጦ የተገነባ፣
በሞራል፣ በህግም፣ በኃይማኖት — ከቀማኛ ሌባ ተሻርኮ መብላት፣
ያስጠይቃል ጊዜው ሲደርስ  — ሀገር ለባለሀገሩ ሲመለስ፤
ከስማችንም፣ ከገንዘባችንም ሳንሆን በከንቱ እንዳንቀር፣
እናም ጎበዝ! እናስብበት፣ ጊዜው ሳያልፍ እንምከር።

ይድረስ ለእኛ!
ሳይማር ላስተማረን — ወርቅ፣ አልማዝ ላበደረን፣
ምላሻችን አይሁን ጠጠር  —  የበላንበትን ወጭት አንስበር፤
ለፍትህ፣..ለነጻነቱ፣ ሕዝብ የሚያደርገውን ወሳኝ ትግል፣
በአእምሮ ድህነት ተጠፍረን፣ ማገዝ እንኳን ባንችል፣
እኛ ከዋናው ጠላቱ ብሰን፣ ጉሮሮው ላይ አጥንት አንሰንቅር፤
የፈሪ ዱላችንን እንደታቀፍን፣ ባይሆን “መሃል እንስፈር”፤
የ”እሱ” ክፋት መች አነሰና፣ ሀገር እሚያቃጥል በሰበብ-አስባብ፣
ለእሳት ቤንዚን ከማቀበል፣ ከእኩይ ተግባር እንታቀብ፤
ማስጣል እንኳ ቢያቅተን፣ የጊዜ ምስጢር ዘማ፣
በ”ያባትህ ቤት ሲዘረፍ..” ብሂል፣ አገራችንን አናድማ!

ይድረስ ለእኛ!
አመንዣጊ ለሆንን እንደ ጌኛ፣
በሆዳችን ለምናስብ፣
ለማይመስለን በልተን እምንጠግብ፤
ከረሃብተኛ ጉሮሮ ነጥቀን፣  በጠኔ ከደከመ ጨቅላ፣
ህሊናችንን ሸፍነን፣ ሆዳችንን ለምንሞላ፣
በዛሬ ብቻ “አስረሽ-ምችው”፣ የትውልዱን ነገ ለምናጨልም፣
ትርፍራፊያችን እንኳ እንዳይቀር፣ በክፋት ለውሰን ለምናወድም፤

ይድረስ ለእኛ!
ውጭም ሆነ-ውስጥም ላለን፣
ለቅንጥብጣቢ ስጋ፣ እንደውሻ ለሚጣልልን፣
ከደሀ አፍ ተነጥቆ፣ ዳረጎት ለሚሰፈርልን፣
ለደረቅ ፍርፋሪ እንጀራ፣ ተበልቶም ለማያጠረቃ፣
በወገን ቁስል ላይ፣ እንጨት መስደድ ያብቃ!

ይድረስ  ለእኛ – ከእኛ!  – “እኛና -እናንተ” ሳንባባል፣
ይልቁንስ በጋራ እናፍልቅ ላገራችን መድኅን ፀበል!!

ነሐሴ 2008 ዓ/ም
(ኦገስት 2016)

(ይህ ግጥም ከሁለት ዓመታት በፊት የተሰራጨ ሲሆን፣ ጥቂት ስንኞች ተጨምረውበት ዳግም የቀረበ ነው።)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. tazabiw says

    August 13, 2016 07:31 pm at 7:31 pm

    Dear Getch
    i am very proud to know you and to call you my friend.
    i read it and it is true!!!
    we have to comeback to our senses and join the struggle to get rid of the Woyane Junta!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule