• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አምስተኛ ቀኑን ያሳለፈው የሕንጣሎ ወረዳ ተቃውሞ ቀጥሏል

January 20, 2020 08:45 am by Editor 1 Comment

የክልሉ መንግስት ምላሽ ቢጠየቅም ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም፤ ትላንት አምስተኛ ቀኑ አልፏል

በትግራይ ክልል የሕንጣሎ ወረዳ ነዋሪዎች በአዲሱ የአስተዳደር መዋቅር ሒዋነ ከምትባለው ወረዳ ጋር እንዲቀላቀሉ መደረጋቸውን ተቃውመዋል። “በአቅራቢያችን መተዳደር እንፈልጋለን” በማለትም ከመቀሌ ከተማ ወደሳምረ በሚወስደው ደንጎላት በሚባል አካባቢ መንገድ ዘግተው የክልሉ መንግስትን ምላሽ በመጠባበቅ አራተኛ ቀናቸውን ደፍነዋል።

ለመንገዱ መዘጋት ምክንያቱ የ“ወረዳችን ይመለስልን” ጥያቄ በማቅረብ ከህብረተሰቡ በተወከሉ ነዋሪዎች አማካኝነት ላለፉት ስድስት ወራት ያክል ወደክልል አስተዳደር ተመላልሰው ቢጠይቁም ምላሽ ባለማግኘታቸው ምክንያት የተነሳ መሆኑን ተናግረዋል።

አዲስ ዘመን ያናገራቸው የአካባቢው ነዋሪ አቶ መሀሪ ገብረ፤ “ህብረተሰቡ ሌላ ሃሳብ የለውም፣ ዓላማው ወደክልሉ ቢሮ በመመላለስ ላነሳው ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ነው” ብለዋል።

አራተኛ ቀኑን የደፈነው ከሕንጣሎ ከተማ ወደ ሳምረ የሚወስደው መንገድ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንደሌለውም ምንጮቻችን አረጋግጠውልናል።  

የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች በአካል ተገኝተው ህብረተሰቡን ማነጋገራቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ ህብረተሰቡ የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች እንደማይፈልግና ከክልል አስተዳደር አካላት በአካል ተገኝተው እንዲያናግሯቸው እንደሚፈልጉም ተናግረዋል። 

ከሕንጣሎ እስከ ሒዋነ እስከ 35 ኪሎ ሜትር ርቀት ስላለው የሚፈልጉትን አገልግሎት ለማግኘት ስለሚቸገሩና ሕንጣሎ ወደሒዋነ መቀላቀሉ ተገቢ ባለመሆኑ እንዲስተካከል ጠይቀዋል። ሕንጣሎ ወረዳ ተመልሷል በሚል ስያሜውን ይዞ በህንጣሎ ያሉትን እንደ ደንጎላት ሳምረ ያሉ ቀበሌዎችን ይዘው ወደሒዋነ ከተማ መቀላቀሉ ትክክል አይደለም ብለዋል። ወረዳው ሕንጣሎና በእዛ አካባቢ ያሉ ቀበሌዎች እንዲይዝም ጠይቀዋል።  

በአደረጃጀቱ ላይ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ህዝቡን እንዳላነጋገሩ የጠቆሙት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአካባቢው ነዋሪ፤ ከዚህ ይልቅ ከአንዳንድ የቀበሌው አመራሮች ጋር ብቻ ተነጋግረው መወሰናቸው ለቅሬታው መፈጠር ምክንያት መሆኑን ነግረውናል። 

የክልሉ መንግስት ሕዝቡ በአቅራቢያው እንዲተዳደር በሚል ባወጣው የከተማ አወቃቀር የስምንቱ ቀበሌ ወኪሎች ተውጣጥተው ከወረዳ እስከክልል ድረስ ጥያቄውን ቢያቀርቡም ምላሽ እንዳላገኙ ገልጸዋል።

በጉዳዮ ምላሽ ለማግኘት ወደ ትግራይ ክልል ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ጋር ደጋግመን ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም።

ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ሐዱሽ ካሱን በስልክ አግኝተናቸው በነዋሪዎቹ ቅሬታና ተቃውሞ ምላሽ እነዲሰጡ ጠይቀናቸው ጉዳዩን እንደማያውቁት አሳውቀውናል።

ጉዳዮን አጣርተው ሊነግሩን መልሰን እንድንደውል የገለጹልን ቢሆንም፤ ለህትመት እስስገባንበት ጊዜ ድረስ ደጋግመን ብንደውልም ስልካቸውን ሊያነሱልን አልቻሉም።

ምንጭ፤ ኢፕድ

አምዶም ገብረሥላሴ በፌስቡክ ገጹ “ሕንጣሎ 70 እንደርታ_እምቢተኝነት!” እንደገለጸው የሕንጣሎ ወረዳ ህዝብ ተቃውሞ መንገዱ እንደተዘጋ 5ተኛ ቀን_ኣልፈዋል። ሕንጣሎ ህዝብ 105 ሺህ ብዛት ኑዋሪ ያላት ወረዳ ናት።

የህወሓት መንግስት ለህዝባዊ ጥያቄው ቀና መልስ በመመለስ ፈንታ ለሰሓርቲና ሳምረ ወረዳ ህዝቦች “ዓረና” እንናንተን ለመጉዳት ብሎ ያዘጋጀው ተቀውሞ ነው” እያለ ቅስቀሳ እያካሄደበት ይገኛል።

ይሁን እንጂ ህዝቡ ሊሰማቸው ኣልታለም። በተለይ የሰሓርቲ ህዝብ “እኛም በዓረናነት ፈርጃቹ ስታንገላቱን ነበርና ኣናምናቹም” በማለት ራሱ እየመከታቸው ይገኛል።

ወዳጄ ሕንጣሎ ማለት ተራ ህዝብ እንዳይ መስልህ። በቀዳማይ ወያነ ትግል ውስጥ የኣምበሳ ድርሻ ያለውና ታጋዮቹ ባንዴራችን የኢትዮጵያ ባንዴራ! ራሳችን በራሳችን እናስተዳድራለን! ሁሉም ዜጋ እኩል ነው! ገረብ ዓረና ወያነ ትግራይ ብለው ያወጁበትና ቃልኪዳን የገቡበት ማይደርሁ የሚገኝበት ታሪካዊ ቦታ ናት።

ፍትሕ_ለሕንጣሎ_ህዝብ!

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የተምቤን ወጣት ወደ መቐለ የሚወስድ መንገድ ሊዘጋ ነው! ምክንያቱ በደርግ ግዜ የነበረ የተምቤን አውራጃ አስተዳደር መመለሰ አለበት የሚል ነው።

ተጨማሪ የጣንቋ አበርገለ ወረዳ ወጣቶችም በደርግ ግዜ የነበረ ወረዳችን ይመለስልን ተቃውሞ ወደ ሳምረ የሚወስድ መንግድ ሊዘጋ ነው።

ተመሳሳይ የውቅሮ ክልተ አውላዕሎ ወጣትም ከአድግራት ከተማ ወደ መቀለ የሚወስድ መንገድ ሊዘጋ ነው። ምክንያቱም  በደርግ ግዜ የነበረ የዞን አስተዳደራችን ይመለስልን ነው።

በመቀጠል የትግራይ ህዝብ ከስሜን እስከ ደቡብ ከምስራቅ እስከ  ምዕራብ ታላቅ ተቃውሞ ሊያሰማ ነው።
የትእምት ባለቤት ሊታወቅ ይገባል ነው!

የህወሃት ቀንደኛ ደጋፊና ተሟጋች የሆነው ዳንኤል ብርሃኔ የህንጣሎን ጉዳይ በማራከስ ይህንን በማለት በፌስቡክ ገጹ ጽፏል፤

“ሽረ አካባቢ ሁለት ቦታ መንገድ ተዘግቶ እንደነበር ሰምቻለሁ። አንዱ – ከሽረ በስተሰሜን ዓዲ ነብርኢድ ላይ ሲሆን፤ የወረዳ መሆን ጥያቄ ያላቸው ሲሆኑ፤ ለበኣል ወደሽረ ከተማ የሄደው ደብረጺዮን ሳያነጋግረን መሄድ የለበትም ብለው ነው።
ሁለተኛው – ከሽረ በስተደቡብ (ወደ አክሱም መስመር) ዓዲ ኢታይ አካባቢ ሲሆን መሳሪያ ጭነው ሊንቀሳቀሱ የነበሩ የመከላከያ መኪኖች እንዲቆሙና ወደካምፕ እንዲመለሱ ለማድረግ ነው።”

ይህንን በትግራይ የተነሳውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተከትሎ ለዳንኤልና ለሌሎች የህወሓት/ትህነግ አገልጋይ ሎሌዎች ለሆኑት የተሰጠው አስተያየት እንዲህ ይነበባል፤

“የዳንኤል ብርሃነ ምርጥ ውሸት! አንተ ቀዳዳ ያኔ ኦሮምያ ወይም አማራ ክልል ቢሆን በምስል አስደግፈህ የተደረገና ያልተደረገ አቀናብረህ ትፅፍ ነበር።ለምን ታድያ አሁን ልሳንህ ተዘጋ? ጌታህ ህወሓት ሲነካ የትግራይ ህዝብ ድምፅ ለማፈን ትሞክራለህ። አንተ ማትረባ በትእምት ገንዘብ የሰከርክ የህሊና እስረኛ። መቼ ነው አንተ የህዝብ ድምፅ የምትሆነው በእርግጠኛነት አንተና መሰሎችህ ዋጋቹን የምታገኙበት ሩቅ አይደለም። Habtom Berhe, Senait Mebrahtu, Alula Solom, G/ medhin G/her, Medhin G/sellase እናንተ ሁላቹ የማትረቡ የህወሓት አገልጋዮች ናችሁ። እስኪ እውነት አክቲቪስቶች ከሆናቹ የትግራይ ህዝብ ድምፅ አሰሙን። እስኪ የዓዲ ነብሪኢድ፣ ሕንጣሎ ተቃውሞዎችና መንገድ የመዝጋት እንቅስቃሴዎች ከነመፍትሔዎቻቸው አስቀምጡ እውነት የትግራይ ህዝብን ድምፅ ከሆናችሁ። ይህ በቅማንት ቢሆን ግን ትተለተሉ ነበር ምድረ ቱልቱላ ካድሬዎች። አሁንም ደግሜ ልንገራቹ እናንተና የናንተ ዓይነቶቹ የህዝብ ድምፅ የሚያፍኑ ዋጋቸውን ያገኛሉ። ልክ እንደ ህወሓት ተጠያቂዎች ናቸው።”

ሕዝባዊ እምቢተኝነቱ የጥምቀትን በዓል ምክንያት በማድረግ ረገብ ያለ ቢሆንም በቀጣይ ቀናት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መረጃዎች ይጠቁማሉ። ትህነግ/ህወሓትም ይህንን እምቢተኝነት መስበር እየሞከረች ሲሆን የምትወስደው እርምጃ የበለጥ እምቢተኝነቱን ወደሌላ ክፍል እንዳያዘዋውረው ፍርሃት እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, hintalo, Middle Column, tigray, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse Gebregzi says

    January 21, 2020 06:38 pm at 6:38 pm

    Peace based on the fear of God,remember Raesi Weldeslassie ruled from around these places.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ኢትዮጵያ ጨምሮ የቀይ ባሕር ሀገራት ቀጣናዊ ስጋቶች በመጨመራቸው የባሕር ትብብር ለማጠናከር ወሰኑ August 28, 2026 11:32 am
  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
Copyright © 2026 · Goolgule